Hlina Bank-ህሊና ባንክ

Hlina Bank-ህሊና ባንክ At Menelik II Hospital Hlina Bank will provide customer satisfaction with a variety of support services through compassionate and efficient service.

✍️ ጓደኝነት የሰው ልጅ ከሌላው መጣበቅ የመፈልግ ተፈጥሮአዊ መገለጫ፣ ከራስ ሲሸሹ የሚያገኙት መጠጊያ፣ ከአብሮ መኖር ጭቆና የአፍታ ነጻነት ማግኛ፣ ብሶትን በቀልድ ማምለጫ፣ ችግርን በድጋፍ ...
08/06/2022

✍️ ጓደኝነት የሰው ልጅ ከሌላው መጣበቅ የመፈልግ ተፈጥሮአዊ መገለጫ፣ ከራስ ሲሸሹ የሚያገኙት መጠጊያ፣ ከአብሮ መኖር ጭቆና የአፍታ ነጻነት ማግኛ፣ ብሶትን በቀልድ ማምለጫ፣ ችግርን በድጋፍ መውጫ መሆኑን ለማወቅ የኚህ አራት ሴቶች ጓደኝነት ጥሩ ምስክር ነው።
“አየሽ እዚህ ደሳሳ ሻይ ቤት እስጥ መምጣት ከተቀበልሽ የሚያፈስ ሽንት ቤት ያለበት ሆስፒታል ውስጥ ኢንፌክሽንን ማከም ይቻላል ከአልሽ የሚያፈስ ክፍል ውስጥ አስተምራለው ከአልሽ ሰባራ ወምበሩን ተቀምጠሽበታል ማለት ነው”…”ሰባራ ወንበሩን መጸየፍሽ ጥሩ ነው። ባትጸየፊው ነው ሊደንቅ የሚገባው ካልተጸየፍሺው ልቀይሪው አትሞክሪም።”ህክምና መታደል ነው። ቤትኛውም አጋጣሚ ከታመመ ሰው ፊት ስትቆሙ ምን ያህል የታደላቹ መሆናችሁን አትርሱ የታመማቹት እናንተ ባለመሆናቹ ብቻ ሳይሆን ለመፍትሄ የተመረጣችሁ እናተ በመሆናቹ”

“ህክምና መታደል ነው። ሰው የደበቀውን ሚስጥሩን፣ ህመሙን፣ ብሶቱን ፣ጭንቀቱንና ደስታውን ከማንኛውም በላይ ህይወቱን አሳልፎ በጃቹ ውስጥ የሚያኖርበት ስለሆነ”

“ህክምና እዳም ነው። በእምነት የተቀበሉትን የሰው ህይወት በአግባቡ የመንከባከብና የመጠበቅ ሲሆን በተሻለ አሊያም በነበረበት መልክ ማቆየትና መመለስ ስለሆነ”

“ህክምና መስዋትም ነው። ጎዳኝ ብለህ የማትሸሸው ከፋኝ ብለህ የማትተወው ተቸገርኩ ብለህ የማትሸጠው ምክኒያት የለሽ መሰዋት ነው። ንጹህ መሰዋትነት በጎ ስለሆነ ብቻ የምታደርገው”

“ህክምና መጠራትና መመረጥ ነው። በሰው መኖርና አለመኖር መሃል ከውልደት እስከሞት በደስታና በመከራ በተሞላ ህይወት ወስጥ የፈጣሪን የመፍጠር የማኖር የማሳመም የማጥፋት ፍላጎት ተባባሪ መሆን።

በእናት ሆድ ውስጥ ጥጋብ ነው፤ ረሀብ የለም፡፡ በእናት ሆድ ውስጥ ሙቀት ነው፤ ብርድ የለም፡፡ ከሁሉም በላይ ግን በእናት ሆድ ውስጥ ጣዕር የለም፡፡ መስራትም የለም፡፡ በምቾት መንፈላሰስ እና በለስላሳ ውሀ ውስጥ መንሳፈፍ ነው፡፡ ይህ ሁሉ ድሎት በተወለድንበት ቅፅበት ይለወጣል፡፡ መተንፈስ ግድ ይላል፡፡ ረሀብን ለማስታገስ መጥባት እንጀምራለን፡፡ ይበርደናል፤ ሙቀት ለማግኘት ከሌላው እንጠጋለን፡፡ ለመኖር፡፡ አለበለዚያ መኖር የለም፡፡ መታፈን፣ በረሀብ አለንጋ መቆላትና በብርድ ቆርፍዶ መሞት የፍርሀታችን ሁሉ መነሻ ይሆናሉ፡፡ በእናታችን ማህፀን የምናውቀው መኖርን ብቻነው፡፡ መወለድ አለመኖርን አመላካች ነው፡፡”
✍️ ዶ/ር ዳዊት ወንድምአገኝ አለመኖር
"መልካም የጓደኝነት ቀን♥"

06/06/2022
03/06/2022

የሰው ልጅ የነፍሱን ጥያቄ የሚመልስበት አግባብ እንደየመልኩ የተለያየ ነው፤ የህሌናው ጥያቄና መልሱ ግን ተመሳሳይ ነው።

በዳግማዊ ምኒልክ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከግንቦት 19–22 ቀን  2014 ዓ/ም ሲሰጥ የነበረው የMCC እና Infection Prevention and Safety ስልጠና በአማራ ሁ...
30/05/2022

በዳግማዊ ምኒልክ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከግንቦት 19–22 ቀን 2014 ዓ/ም ሲሰጥ የነበረው የMCC እና Infection Prevention and Safety ስልጠና በአማራ ሁኔታ ከተጠናቀቀ በኃላ ሆስፒታሉን ፅዱና አረንጓዴ ለማድረግ ድንቅ ስራ ተሰርቷል።

ስልጠናውን የተካፈሉ የፅዳትና ጉልበት ሰራተኞችም በዚህ ልክ የምንደገፍ ከሆነ ተቋማችን ለማንኛውም ተገልጋይ ምቹ ይሆን ዘንድ የሚጠበቅብንን የበኩላችንን ጥረት እንደርጋለንም ብለው በፍቅር አሳልፈናል።

"ከህሊናችን በተሰጠን ሁሉ ፀጋ በማገልገል የህሊና ባንክ ክምችቶቻችንን በማብዛት የደንበኞቻችንንም ሳቅ አብረን እንሳቅ።"
8:42 AM May 30,2022

Overview Evidence based Care(EBC) and System Bottleneck Focused Reform (SBFR) For senior Physicians, DDT Heads, Case Tea...
26/05/2022

Overview Evidence based Care(EBC) and System Bottleneck Focused Reform (SBFR) For senior Physicians, DDT Heads, Case Team Leader Of Menelik II Comprehensive Specialized Hospital.

17/05/2022

"ከህሊናችን በተሰጠን ፀጋ በብቃትና በርህራሄ በማገልገል የህሊና ባንክ ክምችቶቻችንን እናብዛ!!!"

 #ከፍተኛ የደም ግፊት 'ዝምተኛ ገዳይ' ይባላል ምክንያቱም  #ከፍተኛ የደም ግፊት ያለባቸው ሰዎች የግንዛቤ እጥረት አለባቸው።  ይህ የማስጠንቀቂያ ምልክቶች እና ምልክቶች አለመኖር ወይም ስ...
17/05/2022

#ከፍተኛ የደም ግፊት 'ዝምተኛ ገዳይ' ይባላል ምክንያቱም #ከፍተኛ የደም ግፊት ያለባቸው ሰዎች የግንዛቤ እጥረት አለባቸው። ይህ የማስጠንቀቂያ ምልክቶች እና ምልክቶች አለመኖር ወይም ስለ ተመሳሳይ እውቀት ማነስ ውጤት ነው። ስለዚህ የእርስዎን # የደም ግፊት በየጊዜው ይለኩ።

የዓለም የደም ግፊት ቀን 2022፥ "'የደም ግፊትዎን በትክክል ይለኩ፣ ይቆጣጠሩት፣ ረጅም ዕድሜ ይኑርዎት'" የዘንድሮው መሪ ሃሳብ በአለም አቀፍ ደረጃ ዝቅተኛ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን በ...
17/05/2022

የዓለም የደም ግፊት ቀን 2022፥

"'የደም ግፊትዎን በትክክል ይለኩ፣ ይቆጣጠሩት፣ ረጅም ዕድሜ ይኑርዎት'"

የዘንድሮው መሪ ሃሳብ በአለም አቀፍ ደረጃ ዝቅተኛ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን በተለይም ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ያላቸውን አካባቢዎች መዋጋት እና ትክክለኛ የደም ግፊት መለኪያ ዘዴዎች ላይ ያተኩራል።

ከፍተኛ የደም ግፊት ያለ ምክንያት ሳይሆን ዝም ገዳይ ይባላል። ብዙ ጊዜ የደም ግፊት ምልክቶች አይታዩም እና ምንም እንኳን አንዳንድ ምልክቶች ቢኖሩብዎትም፣ እንደ መደበኛ ድካም፣ የስራ ጫና ወይም ጉልበት በመተው ወዲያውኑ እርምጃ አይወስዱም። የደም ግፊት ጉዳዮችን ችላ ማለት ገዳይ ሊሆን ይችላል እና በከፋ ሁኔታ የልብ ድካም፣ የልብ ድካም፣ የደም ማነስ፣ የደም መፍሰስ ችግር፣ የማስታወስ ችግር ወይም የመርሳት በሽታ ሊያስከትል ይችላል። የደም ግፊትን በየጊዜው መከታተል ከከባድ በሽታዎች ለመዳን ቁልፍ ነው.

በዓለም ዙሪያ 1.13 ቢሊዮን ሰዎች በከፍተኛ የደም ግፊት ይሰቃያሉ እና በሽታው ከሴቶች ይልቅ በወንዶች ላይ የተለመደ ነው።

ስለሆነም በዛሬው እለት ታካሜን ማዕከል ያደረገ የቅድመ መከላከልና መቆጣጠር ተቀዳሚ መመሪያው ነውና በሆስፒታላችን ዳግማዊ ምኒልክ ኮምፕሬሄንሲብ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከ300 በላይ ታካሚዎችን የቅድመ ልየታ ከተደረገላቸው ውስጥ 20ዎቹ ያልታወቀ ከፍተኛ የደም ግፊት ሲገኝባቸው፤ 7 ተገልጋዮች ደግሞ ለከፍተኛ የስኳር መጨመር በልየታ ስራ የተገኙ ሲሆን ወደ መደበኞ የህክምና ክትትል እንዲጀምሩ የማድረግ ስራ ተሰርቶ አለም አቀፍ ከፍተኛ የደም ግፊት ቀንን በዚህ ሁኔታ ተከብሮ ውሏል።

"ከህሊናችን በተሰጠን ፀጋ በብቃትና በርህራሄ በማገልገል የህሊና ባንክ ክምችቶቻችንን እናብዛ!!!"

ደሣለኝ መልካሙ
MCC ተጠሪ

Hypertension is called the ‘silent killer’ because most people with   lack awareness. This is an outcome of the absence ...
17/05/2022

Hypertension is called the ‘silent killer’ because most people with lack awareness. This is an outcome of the absence of warning signs & symptoms or lack of knowledge about the same. So, measure your regularly.
And what better day to start doing it than ?!
Start it today!


https://t.me/MinilikMCCHlina

Hypertension is called the ‘silent killer’ because most people with   lack awareness. This is an outcome of the absence ...
16/05/2022

Hypertension is called the ‘silent killer’ because most people with lack awareness. This is an outcome of the absence of warning signs & symptoms or lack of knowledge about the same. So, measure your regularly.
And what better day to start doing it than ?! Start it today!


https://t.me/MinilikMCCHlina

ጤና ይስጥልኝ!በሽታዎች ማለትም ከስኳር ፤በከፍተኛ ደም ግፊት ምክንያት ከሚመጣ የልብ እና ደምስር ህመም ፤ ከሚጥል እና ከአስም በሽታ አቅራቢያዎ በሚገኝ ጤና ተቋም በመሄድ የጤና ምርመራ በማ...
16/05/2022

ጤና ይስጥልኝ!
በሽታዎች ማለትም ከስኳር ፤በከፍተኛ ደም ግፊት ምክንያት ከሚመጣ የልብ እና ደምስር ህመም ፤ ከሚጥል እና ከአስም በሽታ አቅራቢያዎ በሚገኝ ጤና ተቋም በመሄድ የጤና ምርመራ በማድረግ ጤናዎን ይጠብቁ ፤ የሐኪም ምክሮቹን በአግባቡ ይተግብሩ ጤና ለራስ ነውና!!

አካላዊ እንቅስቃሴ በየእለቱ ማድረግ ፤ አትክልትና ፍራፍሬን አዘውትሮ በበቂ መጠን መመገብ፣ ክብደትን ከቁመት መጠን ጋር የተመጣጠነ ማድረግ ፟ ረጅም እድሜ ከነ ሙሉ ጤንነቶ እንዲኖሩ ይረዳዎታል፡፡

ልብ ይበሉ የጨው፣ስኳር እና ቅባት መጠንን ከተገቢው በላይ መጠቀም ፣ ትምባሆ ማጨስና ከመጠን ያለፈ የአልኮል መጠጦችን መጠቀም ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች በከፍተኛ ሁኔታ ያጋልጦታል!!
የአኗኗር ዘይቤአቸንን በመለወጥ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን አንከላከል !!!!

ሲል ይህን መልክት ያቀረበሎት ሄልዝ ሊሚትድ እና ኖቫርቲስ ቢዝነስ ፈንዲንግ ፣ ከጤና ሚኒስቴርና ከዳግማዊ ምኒልክ ኮምሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጋር በመተባበር የቀረበ መርሃ ግብር ነው፡፡

ዓለም አቀፍ የደም ግፊት ቀንን ስለጤንነትዎ ደህንነት በማቀድ ዋሉ።
https://t.me/MinilikMCCHlina

Address

Addis Ababa
@ምኒልክሆስፒታል

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hlina Bank-ህሊና ባንክ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Hlina Bank-ህሊና ባንክ:

Share