Woba Ari Worda Health Office page 2012

Woba Ari Worda Health Office page 2012 Boyka

እንኳን ለስቅለተ ዓርብ በዓል በሰላም አደረሳችሁ/አደረሰን! የዎባ ኣሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት  ኃላፊ አቶ ነዋይ ማትዮስ ለጌታችና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለትና ትንሳኤ በዓል አስመል...
10/04/2026

እንኳን ለስቅለተ ዓርብ በዓል በሰላም አደረሳችሁ/አደረሰን!
የዎባ ኣሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ነዋይ ማትዮስ ለጌታችና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለትና ትንሳኤ በዓል አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

ሚያዝያ 2/2018 ዓ.ም (ከዎአወጤጽ/ቤት)

ከዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት አቶ ነዋይ ማትዮስ ለመላው ኢትዮጵያዊያን በሀገር ውስጥና በውጭ ለሚገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለስቅለተ ዓርብ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል

በሀገራችን ብሎም በመላው ዓለም የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ አክብሮት የሚታሰበው የስቅለት በዓል፤ የፍቅር፣ የትህትና እና የራስን ጥቅም አሳልፎ የመስጠት ታላቅ ተምሳሌት ነው።

ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆች ሲል በፈቃዱ የተቀበለው መከራና የከፈለው መስዋዕትነት ለሁላችንም ይቅርታን፣ ሰላምንና መተሳሰብን የሚያስተምር ነው።

የጌታ ስቅለት የፍቅር ሁሉ ጥግ እና ለሌሎች የመኖር ጥበብ የታየበት ዕለት ነው። ይህ የሕመም፣ የጸሎትና የይቅርታ ዕለት ለሀገራችን እና ለዓለም ሰላምን፣ ለልባችን ቅንነትን የሚያድል ይሁን።

በድጋሚ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የበዓል ጊዜ እንዲሆንላችሁ እንመኛለን።

መልካም በዓል!

ዳንኤል ገበየሁ ከዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት

ዎባ አሪ ወረዳ   ጤና ጽ/ቤት ከኢ/ ኦ/ ተ /ቤ/ክ/የል/ክ/ተ/ኮሚሽን  በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የክትባት ፕሮጀክት  የ6 ወረ የጋራ  አፈጻጸም  ግምገማ  ተጀመረ ።   ቦይካ _ ጥር  12...
21/01/2026

ዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ከኢ/ ኦ/ ተ /ቤ/ክ/የል/ክ/ተ/ኮሚሽን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የክትባት ፕሮጀክት የ6 ወረ የጋራ አፈጻጸም ግምገማ ተጀመረ ።

ቦይካ _ ጥር 12/2018 ዓ.ም
(ዎአወጤጽ/ቤት)
።።።።። ቦይካ ።።

ዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ከኢ/ ኦ/ ተ /ቤ/ክ/የል/ክ/ተ/ኮሚሽን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የክትባት ፕሮጀክት የ6 ወር የጋራ አፈጻጸም ግምገማ መድረኩ መጀመሩን አስታወቀ።

‎ የእለቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ ምልክት ያሰተላለፊ የዎባ ኣሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፍ የሆኑት አቶ ነዋይ ማትዮስ ለታዳሚዎች የ2018 ዓ/ም የ6 ወር አፈፃፀም ግምግማ ላይ እንኳን ደህና መጣችሁ ምልክት አስተላልፏል።

የእለቱን መድረክ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዎባ ኣሪ ወረዳ የብልጽግና ፖርቲ ጽ/ቤት ዋና ኃላፍና የመንግሥት ተጠሪ ክቡር አቶ አበል ሹሊ ስሆኑ ክትባት መደበኛ የጤና ባለሙያው ተግባር ስለሆኔ ሁሉም ህፃናት ክትባት ማግኘት እንድችሉ በሁሉም ክትባት ጣቢያ በክፍለ ጊዜ መከተብ እንደምገባቸው ገልፀዋሉ። አቶ አበል ሹሊ Zero-dose(ክትባት ሳያገኙ አመት ያለፈባቸው) ህፃናትን በትኩረት ተፈልጎ ክትባት እንድያኙ ለማስቻል እንደምደግፉ ገልፀዋሉ።

የ EOC-DICAC project TA አቶ ማረዬ አልታዬ የproject ተግባር እስከ አሁን በወረዳው የፈፀመውን እና በዘመቻ እና በ zero-dose ላይ በትኩረት የተሠሩ ርፖርትን አቅርበዋሉ።

በመቀጠል የጤና ጽ/ቤት የእናቶችና ህፃናት ሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ይሁን ታሪኩ የወረዳውን የ 2018 ዓ/ም 6 ወር የክትባት አፈፃፀም ያቀረቡ ስሆን እንደ ወረዳ የክትባት አፈፃፀሙ ጥሩ እንደሆነ ጠቅሰው ቀጣይ Hard to reach area ያሉ ህፃናትን ተደራሽ ለማድረግ ባለድርሻ አካላት ልዩ ትኩረት መስጠት እንዳለባቸው ገልፀዋሉ።

የዎባ አሪ ወረዳ የፖርቲ ጽ/ቤት የፖሊትካ ዘረፍ ኃላፍና የመንገስት ተጠሪ የሆኑት አቶ ስዩም ዳርጋንሶ እንደተናገሩት በክትባት ልንከላከላቸው የምቻሉ በሽታዎችን በወረዳችን ውስጥ ያሉ ህፃናትን በትክክል በማስከተብ መታደግ እንደምንችል ገልፀዋሉ።

በስተመጨረሻ ከባለድርሻ አካላት የተነሱ ሀሳቦችና ጥያቀዎች ማነቆዎችና ላይ በጋራ ውይይት በማድረግ መድረኩ ተጠናቋል።


የ ዎአወጤጽ/ቤት ኮሙዩኒኬሽን
ጥር 12/2018 ዓ.ም
ቦይካ

ዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት  እየተሰጠ ያለው የኦንኮሰርኪያስስ በሽታ ማጥፊያ መድኃኒት እደላ ሰባት ቀን አፈጻጸም ፣ ጤና መድህንና  ለቀጣይ ስምርት  ላይ ኦርኒተሽን ጭምር በመሰጠት በወረዳ ...
16/01/2026

ዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት እየተሰጠ ያለው የኦንኮሰርኪያስስ በሽታ ማጥፊያ መድኃኒት እደላ ሰባት ቀን አፈጻጸም ፣ ጤና መድህንና ለቀጣይ ስምርት ላይ ኦርኒተሽን ጭምር በመሰጠት በወረዳ ኮማንድ ፖስት መገምገሙ ተገለጸ ።

ቦይካ_ጥር 8/2018(ዎአወጤጽ/ቤትኮ/ሽን)

በጥቁር ዝንብ አማካኝነት የሚከሰተውን የኦንኮሰርኪያስስ በሽታን ለማጥፋት የሚያስችል የመድኃኒት እደላ ከተጀመረ ሰባተኛው ቀን አፈጻጸም ጤና መደህን በኮማንድ ፖስት ተገምግሟል። አፈጻጸማቸው በቀበሌ ደርጃ ቀርቦ አስተያየት ተሰጥቶባቸዋል ።

1ቦይካ ከቀን ዕቅድ 100% ከአጠቃላይ 84%
2 ድራምረ ከቀን ዕቅድ 99% ከአጠቃላይ 83 %
3 ማለትር ከቀን ዕቅድ 85 % ከአጠቃላይ 71%
4 ዘመር ከቀን ዕቅድ 98% ከአጠቃላይ 82%
5 ውልሸር ታቅዶ 100% ከአጠቃላይ 84 %
6 የዳምር ታቅዶ 98% ከአጠቃላይ 82 %
7 ሻማምር ታቅዶ 100% ከአጠቃላይ 84 %
8 አይዳምር ከተማ ታቅዶ 98% ከአጠቃላይ 83%
9 አይዳምር ዙሪያ ታቅዶ 98 % ከአጠቃላይ 83 %
10 ኦልዳምር ታቅዶ 95% ከአጠቃላይ 80%
11 ፋኢ ታቅዶ 99% ከአጠቃላይ 84%
12 ሎፌት ታቅዶ 99% ከአጠቃላይ 84%
አጠቃላይ እንደ ወረዳ ድምር ከቀን ዕቅድ 97% ከአጠቃላይ 82% መድረስ ተችሏል ።
።።።።።።።።። ጤና መድህን ።።።።።።።።።
✍️✍️✍️✍️ እድሳት ✍️✍️✍️✍️✍️
እድሳት ከፍተኛ እቅድ 1730 ክንውን 85 ሽፋን 5%
እድሳት መካከለኛ እቅድ 2653 ክንውን 539 ሽፋን 21%
መከፈል የማይችሉት እቅድ 1384 ክንውን 254 ሽፋንነት 18.35%
✍️✍️✍️✍️✍️አድስ አባል ማፍራት ✍️✍️✍️✍️✍️✍️
አድስ ከፍተኛ እቅድ 1,821 ክንውን 2 ሽፋን 0
አድስ መካከለኛ እቅድ 2792 ክንውን 28 ሽፋን 1%
መከፈል የማይችል እቅድ 1457 ክንውን 0 ሽፋን 0%
።።።። አጠቃላይ የአባላት ምጣኔ ።።።።።
እቅድ 11836 ክንውን 918 ሽፋን 7.76
✍️✍️✍️የተሰበሰበ ገንዘብ 931,554 ✍️✍️✍️
ኦሞ ባንክ የገባ 409,014
በእጅ ያለ 522,540

የአፈፃፀም ግምገማውን ያጠቃለሉት የዎባ አሪ ረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ነዋይ ማትዮስ ሲሆኑ ከቀረበው ሪፖርት አንጻር ኦንኮሰርክያስስ አፈጻጸም ጥሩ ቢሆንም ቀጣይም ላይ የጤና መድህንና ሌሎች የስምርት አካል በማድረግ ቀናቶች ባለው ውሰጥ ተጠናክሮ እንድቀጥል ጭምር ገልጸዋል ።

የመረጃ ምንጭ( የዎአወጤጽ/ቤትኮ/ሽ)

የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና

የዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ነዋይ ማትዮስ  የገና በዓልን በማስመልከት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።     ታህሳስ፦ 28 /201...
06/01/2026

የዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ነዋይ ማትዮስ የገና በዓልን በማስመልከት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

ታህሳስ፦ 28 /2018 ዓ.ም (የዎአወጤጽ/ቤት)

የዎባ አሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፍ አቶ ነዋይ ማትዮስ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን የእንኳን አደረሳችሁ አስተላልፍ ።
ይኸውም :-

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!

የገና በዓል ፍቅርን፣ አንድነትን፣ መተሳሰብን፣ መዋደድንና ህብረትን እንዲሁም ለሌሎች መኖርን በተግባር የምናሳይበት ነው ።

በዓሉ ጌታችንና መድኃታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን ለማዳን ወደ ምድር የመጣበትና ለሰው ልጆች ታላቅ የምስራች የተበሰረበት በዓል በመሆኑ ለመላው ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በሰላም አደረሳችሁ!አደረሰን!

የዘንድሮውን የገና በዓል የምናከብረው በብዙ ተስፋና የመጪዉን ብሩህ ዘመን አሻግረን እያየን ነው።

የዘንድሮው የገና በዓል ስናከብር በዓመቱ የህዳር ወር መጀመሪያ ሳምንት የማርበርግ ቫይረስ በሽታና ወባ ለአካባቢያችን የጤና ስጋት ሆኖ የተከሰተበት ዓመት ቢሆንም፤ በሽታውን በመከላከለና ለመቆጣጠር ከጤና ሚኒስቴር ጀምሮ እስከ ወረዳ ያሉ ከፍተኛ አመራሮች፥ የጤና ባለሙያዎች፥ ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞችንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እያበረከቱት ባለው ታላቅ ተጋድሎ ተስፋ ሰጭ ውጤቶችን እያየን ስለሆነ ላበረከቱት አስተዋጽዖ ሁሉ ልባዊ ምስጋናየን እያቀረብኩ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም የገና በዓል እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ፤ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ! አደረሰን ለማለትም እወዳለሁ ።

ህዝበ ክርስታያኑም የጌታችንና መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል ደስታውን ሲያጣጥም ለሰው ልጅ ደስታ መነሻና መድረሻ የሆነውን ሰብዓዊነት በመሆኑ፣ አቅመ ደካሞችንና በተለያየ ምክንያት የተቸገሩትን ወገኖችን ሁሉ አቅም በፈቀደ መጠን በመደገፍ በዓሉን በአብሮነት እንዲያከብር ጥሪየን አስተላልፋለሁ፡፡

በዓሉ የተጣላ የሚታረቅበት፣ በዙሪያችን የተከሰተው የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ስጋት ተወግዶ የህዝባችን ሙሉ ጤና የሚነግስበት፣ ፍቅርና ሰላም እንዲሆን ያለኝን መልካም ምኞት በድጋሚ መግለጽ እወዳለሁ።

በመጨረሻም በዓሉን ስናከብር የገጠመን የማርበርግ ቫይረስ በሽታ እስኪወገድ ድረስ የጤና ባለሙያዎች የሚያወጧቸውን የጥንቃቄ የውብሐመር ጤና ጣቢያው እንድንከተል አደራ ማለት እፈልጋለሁ!!

ለህዝበ ክርስቲያን በሙሉ መልካም በዓል እመኛለሁ!!!


የዎአወጤጽ/ቤት ኮሚንከሼን
ታህሳስ፦ 28 /2018 ዓ.ም

የተቀናጀ የአራተኛው ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ  በዎባ አሪ ወረዳ   ኦርኒቴሽን ወይም ስልጠና ለባለድረሻ አካላት  መሥጠቱ ተጀመረ ። ‎የተቀናጀ የአራተኛው ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክ...
11/12/2025

የተቀናጀ የአራተኛው ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻ በዎባ አሪ ወረዳ ኦርኒቴሽን ወይም ስልጠና ለባለድረሻ አካላት መሥጠቱ ተጀመረ ።
‎የተቀናጀ የአራተኛው ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ኦሬንተሽን ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ምልክት ያሰተላለፊ የዎባ ኣሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የኃላፍ ተወካይ አቶ ስማቸው አሽናፍ ምልክታቸው አስተላልፏል ።


ቦይካ _ ታህሳስ 2/2018 ዓ.ም
(ዎአወጤጽ/ቤት)

‎የተቀናጀ የአራተኛው ዙር የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ኦሬንተሽን ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ምልክት ያሰተላለፊ የዎባ ኣሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የኃላፍ ተወካይ የሆኑት አቶ ስማቸው አሽናፍ ምልክታቸው አስተላልፏል ።

ስልጠናው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዕለቱ ክብር እንግዳ የዎባ አሪ ወረዳ ብልጽግና ፖርቲ ጽ/ቤት ኃለፍና የመንግስት ዋና ተጠሪ የሆኑት አቶ አበል ሹሊ ለሠልጣኞች ቁልፍ መልዕክት ካስተላለፉ በኃላ የተቀናጀ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ዘመቻውን ለማከናወን ሁሉም ከሚመለከታቸው የህብረተሰብ ክፍል ጋር በመቀናጀት ለስከታማነቱ እንድዘጋጁና በትኩረት በታቀደው መሠረት እንድከናወን ጥሪ አቅርበዋል።

ከታህሳስ 3_6 በሚካሄደው ዘመቻ ከ10,261 በላይ ለሚሆኑ ህፃናት በወረዳው የተቀናጀ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ለመስጠት መታቀዱን አመላክተዋል።

የፖሊዮ (የልጅነት ልምሻ) በሽታ በዓይን በማይታይ የፖሊዮ ቫይረስ አማካኝነት የሚተላለፍ ሲሆን በዓይነ ምድር በተበከለ ምግብ ወይም ውሃ አማካኝነት ከበሽተኛው ወደ ጤነኛ ሰው የሚተላለፍና የነርቭ ሥርዓትን በማጥቃት የእጅ፣ የእግር መዛል ወይም መዝለፍለፍ፥ ዘላቂ የሆነ ሽባነት እና ሞትን ልያስከትል የሚችል በሽታ በመሆኑ ወላጆች ልጆቻቸውን በማስከተብ የወላጅነት ግዴታቸውን እንድወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

ከተቀናጀ የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ጎን ለጎን የማርበርግ ቫይረስ አሰሳ እና ሊየታ፣ ከወሊድ ጋር በተያያዘ የሽንትና የሰገራ መቆጣጠር ችግር ወይም ፊስቱላ የገጠማቸውን እናቶች መለየት፣ የሥርዓተ ምግብ ችግር ያለባቸዉን ህፃናት ልየታ፣ ከአንድ ዓመት በታች ሆነዉ ክትባት ያላገኙ ህፃናት መለየትና መከተብ እንድሁም ሌሎች የጤና ዘርፍ ሥራዎች በተቀናጀ መልኩ የሚከናወኑ መሆኑን የየበኩላቸውን/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አበል ሹሊ ገልጸዋል ።

በመድረኩ ላይ የተለያዩ ሠነዶች እንደምቀረቡና ከሁሉም ቀበሌያት የጤና ጽ/ቤት ማኔጀመንት የጤና ጣቢያ ባለሙያዎች የቀበለው ጤና ኤክስቴንሽን የቀበለው በጎ መልክተኞች እና ጥሪ የተደረገላቸው የዕለቱ የወረዳው አመራሮች ተሳትፈውበታል ።

የ ዎአወጤጽ/ቤት ኮሙዩኒኬሽን
ታህሳስ 2/2018 ዓ.ም
ቦይካ

15/11/2025

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምንነት፣ መተላለፊያ መንገዶችና መከላከያ ዘዴዎች

‎🔴 #አስቸኳይ  #ጥንቃቄ መልዕክት‼️‎‎በአሁኑ ወቅት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተከሰተውን የሄሞራጂክ ፊቨር (Hemorrhagic Fever) አስመልክቶ ከጤና ሚኒስቴርና ከኢትዮጵያ የሕብረተሰ...
13/11/2025

‎🔴 #አስቸኳይ #ጥንቃቄ መልዕክት‼️

‎በአሁኑ ወቅት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተከሰተውን የሄሞራጂክ ፊቨር (Hemorrhagic Fever) አስመልክቶ ከጤና ሚኒስቴርና ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የተሰጠ ጋዜጣዊመግለጫ

‎የጤና ሚኒሰቴር፥ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና ከክልል ጤና ቢሮዎች ጋር በመተባበር የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎችን እንዳይከሰቱ የመከላከል እና ከተከሰቱም በአፋጣኝ የማረጋገጥና የተቀናጀ የቅኝትና የምላሽ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

‎በአሁኑ ወቅት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ ከተማ ምንነቱ በመረጋገጥ ላይ ያለ የሄሞራጂክ ፊቨር (Hemorrከagic Fever) በሽታ መከሰቱን የቅኝት መረጃዎች ያመለከቱ ሲሆን እስከአሁን ድረስ ስምንት ሰዎች (08) በበሽታው የተጠረጠሩ መሆኑ ታውቋል።

‎በዚህም መሰረት የጤና ሚኒሰቴር ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር በመሆን በደቡብኢትዮጵያ ክልል የተመዘገበውን ይህንን የበሽታ መንስኤ ለማወቅ እና ተጨማሪ ስርጭትን ለመግታት እንዲሁም ለመቆጣጠር ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድን ወደ ቦታው በመላክ የመስከ ግምማዎች እና የላብራቶሪ ምርመራዎችን እያከናወነ ሲሆን በተጨማሪም የማህበረሰብ ቅኝት፣የንክኪ ልየታ፡የቤት ለቤት ልየታ እንዲሁም የህክምና አገልግሎት አሰጣጥን እያጠናከረ ይገኛል።

‎በመሆኑምመላዉ ሕብረተሰባችንና የሚመለከታቸዉ የባለድርሻ አካላት ሚኒስቴር መስሪያቤቱ ሌላ ተጨማሪ መግለጫ እስከሚሰጥ፣ድረስ፤ ለመከላከል የሚከተሉትን ምከረ-ሃሳቦች እና ጥንቃቄዎች ተግባራዊ እንዲያደርጉ እናሳስባለን፡፡

‎ #በአፍ፣አፍንጫ እና ሌሎች የሰውነት ክፍሎች የመድማት፣ትኩሳት፣ማስቀመጥ እና ማስመለስ

‎ #ምልከት ሲኖር ወደ ህከምና፣ተቋማትና መሄድና በወቅቱ የላቦራቶሪ ምርመራ ማድረግ፣ምልክት ከታየበት ማንኛዉም ሰዉ ጋር ንከኪ በሚኖርበት ጊዜ ራስን የመከላከያ ዘዴዎችን መጠቀም፣

‎ #ሁልጊዜ እጅን በሳኒታይዘር ወይም በውሃና በሳሙና በመታጠብ ማጽዳት፣

‎ #ማንኛውም ጤና ተቋም በታካሚዎች ልየታ አካባቢ ልዩ ትኩረት በመስጠት የሻይራል ሄሞሬጅክ ፊሸር (ViralHemmoragic Fever) መሰል በሸታ መለየት፣ መመርመር፣ማከም እና ሪፖርት ማድረግ ያስፈልጋል።

‎ተጨማሪ መረጃዎችን ወደ 8335 እና 952 ነጻ የስልክ መስመሮች በመደወል ማግኘት ይቻላል።

‎ዶ/ር መቅደስ ዳባ
‎የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር
‎ህዳር 03/2018 ዓ.ም
‎አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

  ምንድን ነው?‎‎ይህ በሽታ በቫይረስ የሚከሰት ከባድ የበሽታ ቡድን ነው ። በሽታው በመሰረቱ የደም መፍሰስን ወይም የደም መርጋትን በሰውነት ውስጥ የሚያመጣ ነው ። በርካታ የሰውነት አካላት...
13/11/2025

ምንድን ነው?

‎ይህ በሽታ በቫይረስ የሚከሰት ከባድ የበሽታ ቡድን ነው ። በሽታው በመሰረቱ የደም መፍሰስን ወይም የደም መርጋትን በሰውነት ውስጥ የሚያመጣ ነው ። በርካታ የሰውነት አካላትን በማጥቃት እና በሰውነት ውስጥ ያሉ የደም ሥሮችን የሚጎዳ ፣ በተለያዩ ቫይረሶች የሚመጣ በሽታ ነው።

#‎የበሺታው_መንስኤ እና የቫይረስ ዓይነት

‎. Ebola and ,Rift Valley Fever (RVF) & Yellow Fever ተብሎ የሚከፈል ሲሆን እንደ #ኢቦላቫይረስ ፣ #ደንጉ እና #የለውፊቨር የተባሉ ቫይርሶች የበሺታው መንስኤ ሲሆኑ #በትንኝ ንክሻም የሚመጡ ናቸው ።

‎ በሽታው ስሙ እንደሚያመለክተው በተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ደም እንዲፈስ በማድረግ ለሞት የሚዳርግ ህክምና አልባ አደገኛ በሺታ ነው።

‎በተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ደም መድማት እና መፍስሥ ከተከሰተ የበሽታው ከባድ ደረጃ ምልክት ነው።

‎በሽታው እንዴት ይተላለፋል?

‎1· ከተያዙ እንስሳት ጋር በመነካካት፡ በእንስሳት (ለምሳሌ አይጥ) ፣ ሽንት፣ ምራቅ ፣ ወይም ሌሎች ከሰውነት የሚለቀቁ ፈሳሾች በሚነካኩበት ጊዜ።
‎2· በነፍሳት ንክሻ፡
‎3· ከሰው ወደ ሰው፡ ከተያዘ ሰው የሚገኘው ደም፣ ምራቅ፣ የሰውነት ፈሳሾች ወይም ሌሎች ክምችቶች በቀጥታ በሚነካኩበት ጊዜ። ይህ ለበሽታው ከባዱ እና ዋነኛው ዓይነት የመተላለፊያ መንገድ ነው።



‎ምልክቶቹ በድንገት ሊታዩ እና በፍጥነት ሊባባሱ ይችላሉ። አንድ ሰው በቫይረሱ በተጠቃ ከ 2-21 ቀናት ውስጥ ምልክቶቹ መታየት ይጀምራሉ

‎መጀመሪያ ላይ የሚታዩ ምልክቶች
‎ምልክቶቹን በሁለት ከፍሎ ማየት የሚቻል ሲሆን
‎የመጀመሪው ቀለል ያሉ ምልክቶች እና የመጨረሻው አደገኛ //አስጊ ደረጃ ላይ ሲደርስ የሚታዩ ናቸው


‎· ከፍተኛ የሰውነት ሙቀት (ትኩሳት)
‎· ድካም እና የመዛል ስሜት
‎· የጡንቻ፣ የአጥንት ህመም እና ቁርጥማት
‎· ራስ ምታት
‎· የጉሮሮ ህመም

‎ (በሽታው እየተባባሰ ሲሄድ)፡

‎· በቆዳ ስር ደም መውጣት
‎. ከአፍ፣ አፍንጫ፣ ከዓይን ወይም ከጆሮ ደም መፍሰስ።
‎· የጭንቅላት አዕምሮ መናጋት ፣ መደንገጥ፣
‎. ራስን መሳት ኮማ ውስጥ መግባት)
‎· የኩላሊት እና የጉበት መጎዳት እና ስራ ማቆም
‎· ከፍተኛ ድካም እና ሾክ/Shock
‎· የበርካታ አካላት አለመሥራት

‎እንዴት መከላከል ይቻላል ?

‎በሽታው በትንኝ ንክሻ አማካኝነት የሚተላለፍ በመሆኑ ነፍሶን ከሞት መታደግ ስለሆነ በአግባቡ ይጠቀሙት ። ከታማሚ ሰው ጋር ያልዎትን ንክክ መከላከል እና
‎አፋጣኝ አስፈላጊ የህክምና እርዳታ ማግኘት አስፈላጉ ሆኖ ፣በሺታውን ሙሉበሙሉ ማዳን የሚችል ህክምና የለም ፣
‎መከላከል ብቸኛው ቁልፍ መንገድ ነው !

‎ የሚከተሉትን ማድረግ ያስፈልግዎታል !!

‎1. እጆችዎን በንፅህና ይታጠቡ፡ በሳሙና እና በንጹህ ውሃ ዘወትር ማጠብ አስፈላጊ ነው።
‎2. ከሌሎች ሰዎች (ክምችቶች) ራስዎን ይጠብቁ፡ ከሰዎች ደም፣ ምራቅ ወይም ሌሎች ከሰውነት የሚለቀቁ ፈሳሾች ንክኪዎች ራስዎን ይጠብቁ። ይህ ለቤተሰብ አባላት እና በተለይም ለህክምና ባለሙያዎች እጂግ አስፈላጊ ነው።
‎ብዙ የህክምና/ጤ ና ባለሙያዎች ህይወታቸውን የሚያጡበት ወረርሺኝ ነው።
‎3. ከእንስሳት ይራቁ፣ አይጦችን እና ሌሎች እንስሳት ከቤትዎ አርቀው ያቆዩ። የሚታወቁ የእንስሳት ክምችቶች ባሉበት ስፍራ ጥንቃቄ አይለይዎት
‎4.ከ ነፍሳት ይጠበቁ ፣ አጎበር መጠቀም፡ ነፍሳት እና ወረርሽኙ ወደተከሰተበት ቦታ ፈጽሞ አይሂዱ ፣ ደገኛ ነው ፣ የመተላለፍ እድሉ አደገኛ ነው። ለህክምና ባለሙያዎች መከላከያ ይጠቀሙ እና ሙሉ አካላትዎን የሚደብቁ ልብሶች ይልበሱ

የአጥንት መሳሳት ምንድን ነው?👉በሕክምናው ኦስቲዮፖሮሲስ(Osteoporosis) ይባላል👉የአጥንት የሚነራል ክምችት (Bone mineral density) በእጅጉ በመቀንሱ ምክንያት የሰውነታችን ...
01/08/2025

የአጥንት መሳሳት ምንድን ነው?

👉በሕክምናው ኦስቲዮፖሮሲስ(Osteoporosis) ይባላል

👉የአጥንት የሚነራል ክምችት (Bone mineral density) በእጅጉ በመቀንሱ ምክንያት የሰውነታችን የአጥንት በመሳሳቱ ምክንያት ይከሰታል።

👉አጥንቶቻችን በየጊዜው ራሳቸውን የሚገነቡ ሲሆን ነገር ግን አዲስ አጥንት መተካት ሳይችል ሲቀር የአጥንት መሳሳት ይከሰታል ።

✅️ማንን ያጠቃል?

👉የአጥንት መሳሳት ሴቶችም ወንዶችም ላይ ሊከሰት ይችላል

👉በተለይም እድሜያቸው ገፋ ያሉ ሴቶች ላይ እና ከማረጥ በዃላ (post menopause) ፣ የኢስትሮጅን ሆርሞን (Estrogen hormone) እየቀነሰ ስለሚሄድ ለዚህ ችግር ይጋለጣሉ

👉ወንዶች ላይ ደግሞ የቴስቴስትሮን ሆርሞን (testesretone hormone) ማነስ መንስኤ ሊሆኑ።

👉ለአጥንት መሳሳት የሚያጋልጡን ተጨማሪ ነገሮችስ?

-የተመጣጠነ ምግብ እጥረት (Malnutrition)

-መድሀኒቶች ለምሳሌ Corticosteroid የምንላቸው በተለይ አሁን አሁን ሴቶች ክብደት ለመጨመር እያሉ እየተጠቀሟቸው በመሆኑ አደጋ እንዳላቸው ሊታወቅ ይገባል

-ለቀላሉም ለከባዱም ህመም በተደጋጋሚ የምንወስዳቸው ማስታገሻዎች ፣ ለአስም የሚወሰዱ, በተጨማሪ የሚጥል በሽታ መድሀኒቶች:የካንሰር ሕክምና መድኃኒቶች :PPI የሚባሉ የጨጓራ መድሃኒት ለረጅም ጊዜ ከተወሰደ ወዘተ

-ሲጋራ ማጨስ ፣ አልኮል መጠጥ

-የኩላሊት ፣ የጉበት ችግር ፣ የአንጀት መቆጣት እንዲሁም ሌሎች Autoimmune diseases ችግሮች

✅️ምልክቶቹስ?

👉በብዛት የአጥንት መሳሳት ስበራት እስኪኖር ድረስ ምልክት ላያሳይ ይችላል።

👉ምልክት የሚያሳይ ከሆነ አጥንት አካባቢ የህመም ስሜት ፣ የቁመት መቀነስ

👉በመውደቅ ወይም በግጭት አንዳንዴ ጎንበስ ስንል እንኳን የአጥንት መሰበር በተለይም የጀርባ አከርካሪት እና የዳሌ አጥንት ስብራት ሊያጋጥም ይችላል

👉የሰውነት መጉበጥ

✅️እንዴት መከላከል እንችላለን?

-በቂ የሆነ የፀሀይ ብርሀን ማግኘት ለአጥንት ጥንካሬ በጣም ወሳኝ የሆነውን ቪታሚን D እንድናገኝ ይረዳል

-በካልሽየም የበለፀጉ ምግቦችን መመገብ ለምሳሌ ወተት እና የወተት ተዋፅኦ ፣ የአሳ ምርቶች እንዲሁም

-በቂ የአካል በቃት እንቅስቃሴ ማድረግ

-ተመጣጣኝ የሰውነት ክብደት እንዲኖረን ማድረግ

-ቡና እና ጨው አለማብዛት ምክንያቱም ካልሽየም በብዛት በሽንት እንዲወጣ ስለሚያደርጉ

✅️የአጥንት መሳሳት መኖሩ እንዴት ይረጋገጣል?

-የአጥንት ሚንራል ክምችት በcentral dual-energy x-ray absorbitometry (DXA) ታይቶ መረጋገጥ ይችላል።

✅️ህክምናውስ?

-ከሁሉም በላይ ይሄ ችግር ያለባቸው ሰዎች ስብራት እንዳይከሰት ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው

-አጥንት እንዲጠነክር እና የስብራት ተጋላጭነት አንዲቀንስ የሚያደርጉ መድሀኒቶች መስጠት

- የአጥንትን የሚነራል ክምችት ሙሉ በሙሉ መመለስ ባይቻልም በተወሰነ መለኩ መመለስ ይችላል።

-ያረጡ ሴቶች ላይኤስትሮጅን ሆርሞን (Estrogen) የመተካት ህክምና

-ስብራት ካለ ስብራቱን መጠገን ነገር ግን በእድሜ ገፋ ያሉ ሰዎች ስብራት ከተከሰተ በዃላ መጠገን እና ወደነበረበት መመለስ ጊዜ የሚወስድ እና ትንሽ ከበድ ስለሚል መጠንቀቅ ይገባል።

  | እርግዝና ሊፈጠር የሚችልባቸውን ቀናት ታውቂያለሽ?🚻ሰላም ውድ የገፃችን ተከታታዮች በዛሬዉ ፅሁፌ ይዤላችሁ የቀረብኩት የወር አበባን መሠረት ያደረገ እርግዝና ሊፈጠርና ላይፈጠር የሚችሉባ...
30/07/2025

| እርግዝና ሊፈጠር የሚችልባቸውን ቀናት ታውቂያለሽ?

🚻ሰላም ውድ የገፃችን ተከታታዮች በዛሬዉ ፅሁፌ ይዤላችሁ የቀረብኩት የወር አበባን መሠረት ያደረገ እርግዝና ሊፈጠርና ላይፈጠር የሚችሉባቸውን ቀናት ለይተን ለማወቅ የሚረዳ ግንዛቤ ለመፍጠር ነዉ::

ይህ መረጃ ሁለት ጥቅሞች አሉት አሉት:: እነርሱም እርግዝናን ለመከላከል ወይንም እርግዝናን ለመፍጠር ይጠቅማል::

🚫 እርግዝናን ለመከላከያነት እንድትጠቀሙበት አንመክርም:: በማወቅ ደረጃ ብቻ ቢሆንና ወደ ተግባሩ ለመሄድ አደጋ እንዳለው ከወዲሁ እንድትገነዘቡ ስንል መልዕክታችንን እናስተላልፋለን፡፡ ምክንያቱም ጥናቶች እንደሚያሳዩት ይህን እርግዝና መከላከያ መንገድ ከተጠቀሙ 100 ሴቶች ዉስጥ እስከ 30 የሚሆኑት ሊያረግዙ ይችላሉ::

✅ነገር ግን በተቃራኒዉ ማርገዝ ለሚፈልጉ ይህንን መንገድ ቢጠቀሙበት ጥሩ እንደሆነ እንመክራለን::

🚻በትክክል እርግዝና ሊፈጠርበት የሚችሉት ቀናት ኦቪውሌሽን (እንቁላል የምትለቀቅበት ለማለት ነዉ) ከተከሰተ በሗላ ነዉ፡፡ ኦቪውሌሽን (Ovulation) የሚከሰትበት ቀን አንዲት ሴት ልጅ የወር አበባ ካየችበት የመጀመሪያ ቀን ጀምሮ በመቁጠር በ14ኛው ቀን አካባቢ ይከሰታል፡፡ ስለዚህ ከፍተኛ የማርገዝ ዕድል የሚኖርባቸው ቀኖች የወር አበባ በኋላ ባሉ ከ8-10 ቀኖች ነው (የወር አበባዎ ለመቆም ከ4-6 ቀኖች የሚፈጅበት ከሆነ)፡፡ ነገር ግን ረዘም ያለ የወር አበባ ጊዜ ካለዎት ኦቪውሌሽን የሚከሰትበትም ጊዜ ስለሚረዝም የወር አበባዎን አማካኝ እርዝመት ማወቅ አለብዎት፡፡ ይህንን ለማወቅ ቢያንስ ከ6-12 ወር ያለዉን የቀናት እርዝመት በአማካይ በመዉሰድ ነዉ::

✅የሚከተለው መረጃ ከወር አበባ በኋላ እርግዝና የሚፈጠርባቸውን ቀኖች የሚያሳይ ሲሆን መሰረት ያደረገው በየ 28 ቀን የወር አበባዋን ለምታይ ሴት ብቻ ነው፡፡

💠ከቀን 1-5 (የወር አበባ ከፈሰሰበት የመጀመሪያ ቀን ጀምሮ እስከ አምስተኛው ቀን) = የወር አበባ መፍሰሻ ጊዜ (Menstrual Bleeding time) ነው::

💠ከቀን 6-9 = በንጽጽር እርግዝና የማይፈጠርበት ጊዜ (Relatively Infertile) ነው፡፡

💠ከቀን 10-12 = በንጽጽር በነዚህ ቀኖች እርግዝና ሊፈጠር የሚችልበት ጊዜ (Relatively Fertile) ነዉ::

💠ከቀን 13-15 = በነዚህ ቀኖች ከሌሎቹ ቀናት በተሻለ እርግዝና የሚፈጠርበት ጊዜ (Most Fertile) ነዉ::

💠ከቀን 16-19 = በንጽጽር በነዚህ ቀኖች እርግዝና ሊፈጠር የሚችልበት ጊዜ (Relatively Fertile) ነዉ::

💠ከቀን 20-28 = በነዚህ ቀኖች እርግዝና የማይፈጠርበት ጊዜ (Infertile) ነዉ:

✔ #ማስታወሻ
🌐ትክክለኛው የኦቪውሌሽን ጊዜ የሴት እንቁላል የወንድ የዘር ፍሬን ዝግጁ ሁኖ የሚጠብቅበት ጊዜ ሲሆን ይህም ጊዜ ከ 12 – 24 ሠዓት ብቻ ይረዝማል፡፡ ምክንያቱም የወንድ የዘር ፍሬ ከግብረ ሥጋ ግንኙነት በኋላ በሴት ሰውነት ውስጥ እስከ ሶስት (3) ቀናቶች ብቻ መቆየት ይችላል:: ነገር ግን የሴቶች ዕንቁላል ደግሞ ከ 12 ሰአት እስከ 24 ሰአት ብቻ ነዉ ሊቆይ የሚችለዉ፡፡ ስለዚህ ሊያረግዙባቸው የሚችሉ እስከ አምስት(5) የሚደርሱ ቀኖች አሉ ማለት ነው፡፡

መልካም ጤንነት!!

┄✽┄
እባክዎን ለወዳጅዎ ያካፍሉ!

Address

SNNPRG Jinka
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woba Ari Worda Health Office page 2012 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share