Ethiopian health today

Ethiopian health today Ethiopian Health Today is for awareness creation: health, education,foreign relation,Aid organizations,and professional development.

በትራፊክ አደጋ የ12 ሰዎች ህይወት አለፈ: "አስተውላችሁ አሽከርክሩ"በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን፣ ደሴ ዙሪያ ወረዳ ላይ ከባድ የትራፊክ አደጋ ደረሰ። የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ 59 ሰዎ...
26/09/2025

በትራፊክ አደጋ የ12 ሰዎች ህይወት አለፈ: "አስተውላችሁ አሽከርክሩ"

በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን፣ ደሴ ዙሪያ ወረዳ ላይ ከባድ የትራፊክ አደጋ ደረሰ። የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ 59 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ ተገልብጦ 12 ሰዎች ሞተዋል።

አደጋው የደረሰው ዛሬ ከመካነ ሰላም ተነስቶ ሲጓዝ በነበረው አውቶቡስ ላይ ሲሆን፣ አደጋው የደረሰበት ቦታ “ዳባ መግለቢያ” ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ነው።

ከሟቾች በተጨማሪ 49 ሰዎች ላይ ከባድና
ቀላል ጉዳት ደርሷል።

ወዲያውኑ የደሴ ዙሪያ ወረዳ የፀጥታ አካላት አምቡላንስና ክሬን ይዘው ወደ ስፍራው በመድረስ ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች ወደ ሆስፒታል በማጓጓዝ ላይ ይገኛሉ።

ፖሊስ የአደጋውን መንስኤ ለማጣራት ምርመራውን እንደቀጠለበት አስታውቋል።

©️አሕዱ ቴሌቪዥን

ነብስ ይማር ወገኖቻችን 😭

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

25/09/2025

ጤናን ስታስቡ ፋርማሲን አስታወሱ🤔
መልካም የፋርማሲዎችቀን።

25/09/2025

''Think Health, Think Pharmacist'' Happy World Pharmacy day.

On this World Pharmacists Day, celebrated under the inspiring theme “Think Health, Think Pharmacist”, we are reminded of...
25/09/2025

On this World Pharmacists Day, celebrated under the inspiring theme “Think Health, Think Pharmacist”, we are reminded of the vital role pharmacists play in safeguarding the health of our communities.

Pharmacists are more than dispensers of medicines—we are trusted healthcare professionals, educators, and advocates for the rational and safe use of medicines. In Ethiopia, where access to quality healthcare is both a challenge and a priority, pharmacists stand at the frontline, ensuring that the right medicine reaches the right patient at the right time, promoting antimicrobial stewardship to combat resistance, supporting maternal and child health through safe prescribing and medication use, and guiding patients with compassion, knowledge, and integrity.

As the Mekelle Branch of the Ethiopian Pharmaceutical Association, we reaffirm our commitment to advancing pharmacy services, strengthening evidence-based healthcare, and working hand in hand with other professionals to build a healthier world.

Today, let us celebrate the dedication, expertise, and resilience of pharmacists everywhere. When we say “Think Health, Think Pharmacist”, we are not only recognizing our profession—we are affirming that pharmacists are essential partners in achieving universal health coverage and a stronger healthcare system for all.

Happy World Pharmacists Day!

Berhane Yohannes
Chairperson, Ethiopian Pharmaceutical Association, Mekelle Branch Office

ድሪባ በቀለ ይባላል  የአንስተዥያ ባለሞያ ነው ሆስፒታል ውስጥ በሚከፈለው  ደሞዝ በቀን ሶስት ግዜ መብላት አልቻለም እንደሚትመለከቱት ብስኩት እየጠበሰ ራሱን እያስተዳደረ ይገኛል Inem an...
25/09/2025

ድሪባ በቀለ ይባላል የአንስተዥያ ባለሞያ ነው
ሆስፒታል ውስጥ በሚከፈለው ደሞዝ በቀን ሶስት ግዜ መብላት አልቻለም
እንደሚትመለከቱት ብስኩት እየጠበሰ ራሱን እያስተዳደረ ይገኛል
Inem anesthetist negn! Primary Hospital iyeseraw new. Demose Le betasebe albeka silagn be tirf sa'ate biskut tebishe iyenorkugn new. Lela awach sira lemasirat manesha birr hataw. Kensira lemasirat rasu,ye muya sa'ate ayfekdagnim!biyans be demose ke bank bidir bimachach noro bizu sirawoch mesirat yichal neber.
hakim

   #ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የኒውክሌር ምህንድስና ትምህርት በዘንድሮው ዓመት መስጠት እንደሚጀምር ገለፀየባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በዘንድሮ የትምህርት ዘመን የኒውክሌር ምህንድ...
25/09/2025


#ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የኒውክሌር ምህንድስና ትምህርት በዘንድሮው ዓመት መስጠት እንደሚጀምር ገለፀ

የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በዘንድሮ የትምህርት ዘመን የኒውክሌር ምህንድስና ትምህርትን በሁለተኛ ዲግሪ መስጠት እንደሚጀምር አስታወቀ።

የኢንስቲትዩቱ የድህረ ምረቃ መርሃ ግብር ዲን ዜናማርቆስ ባንቴ (ዶ/ር) ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በአዲሱ የትምህርት ዘመን የኒውክሌር ምህንድስና ትምህርት በሁለተኛ ዲግሪ ሊሰጥ ነው።

በሀገሪቷ የኒውክሌር ቴክኖሎጂን እንደ አንድ አማራጭ የኃይል ምንጭ አድርጎ የመጠቀም ዕቅድ በመኖሩ ፕሮግራሙን መስጠት ማስፈለጉ ለኢፕድ ገልጸዋል።

ዩኒቨርሲቲዉ ትምህርቱን መከታተል የሚፈልጉ ተማሪዎችን እየመዘገበ ሲሆን ለዚህ ትምህርት ብቁ የሚሆኑትም ከዚህ ቀደም በኬሚካል ኢንጅነሪንግ፣ በመካኒካል ኢንጂነሪንግ፣ በኬሚስትሪ፣ በፊዚክስ እና በተመሳሳይ የትምህርት ዘርፎች የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸዉ መሆናቸዉን ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው እ.ኤ.አ 2022 የኒውክሌር ምህንድስና ተማሪዎችን መቀበል መጀመሩን አውስተው፤ ተማሪዎቹም ከመንግስት መሥሪያ ቤቶች የተውጣጡ ሲሆን የመመረቂያ ጊዜያቸው እየተቃረበ መሆኑንም ተናግረዋል።

ባሳለፍነው ዓመት ሚያዚያ ወር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ አባል ሀገራት በኒውኩለር ኢንጂነሪግ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም እንድትሰጥ በአለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ (IAEA) መመረጧን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ማስታወቁን ተከትሎ ነው።

በኢትዮጵያ ለሀገር ውስጥና ለአፍሪካ አባል ሀገራት የኒኩለር ሳይንስና ቴክኖሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም እንዲሰጥ ስምምነት ላይ የተደረሰው፤ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ አለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ (IAEA)፣ በ #ቻይና መንግስት የቺንጓ ዩኒቨርሲቲ፣ እንዲሁም የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ባደረጉት የምክክር መድረክ ነው ተብሏል።
Standard

አትሌት ሸዋረግ  አለን አማረ አረፈች   | አትሌቷ ትላት በአዲስ አበባ ዙሪያ በልምምድ እያለች ነው የድካም ስሜት ተሰምቷት ወደ ሆክፒታል ተወሰዳ  እንዳረፈች ነው የደረሰኝ መረጃ የሚጠቁመው...
25/09/2025

አትሌት ሸዋረግ አለን አማረ አረፈች

| አትሌቷ ትላት በአዲስ አበባ ዙሪያ በልምምድ እያለች ነው የድካም ስሜት ተሰምቷት ወደ ሆክፒታል ተወሰዳ እንዳረፈች ነው የደረሰኝ መረጃ የሚጠቁመው ።

ኑሮዋን በላቲን አሜሪካ ሜክስኮ ያደረገችው ፤ አለሽኝ የ2025 የሲውድን ስቶኮልም ማራቶን አሸናፊ ስትሆን ለልምምድ አዲስ አበባ መጥታ ነው ህይወቷ ያለፈው።

አትሌቷ የቀድሞ አትሌት አለነ አማረ ልጅ ስትሆን የቀድሞ አትሌት አለነ አማረ ደግሞ ኑሮውን በአሜሪካ ኒዮርክ ካደረገ ከ25 አመት በላይ ሆኖቷል።

Shewarge Alene, our 2025 Stockholm Marathon champion.

Mexico City Marathon - 2012 & 2014

Santiago de Chile Marathon - 2013 & 2014

Maratón Internacional Lala - 2014

Via

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል አንዲት እናት አምስት ህፃናት ተገላገለች።በነቀምቴ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ አስቴር ታረፋ በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ጠቅላላ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፥ በአንድ ምጥ አምስት...
25/09/2025

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል አንዲት እናት አምስት ህፃናት ተገላገለች።

በነቀምቴ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ አስቴር ታረፋ በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ጠቅላላ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፥ በአንድ ምጥ አምስት ጤናማ ሕፃናት (3 ወንድ እና 2 ሴት) ተገላግለዋል።

ይህ ክስተት የሆስፒታሉን ሠራተኞችና ቤተሰብ በደስታ አጥለቅልቋል።

ወ/ሮ አስቴር እንዳሉት፣ ከአምስት ዓመት በፊት ሌላ ልጅ የመውለድ ተስፋ ቆርጠው ነበር።

ባለቤታቸው አቶ ታማስገን አለሙ በበኩላቸው፣ ከፍተኛ ደስታቸውን ሲገልጹ፣ አምስት ጨቅላ ሕፃናትን በአንድ ጊዜ ማሳደግ ትልቅ ፈተና እንደሚሆንባቸው ያላቸውን ስጋት ገልጸዋል።
Information

Look at this🤔This is evidence based🤫
25/09/2025

Look at this🤔
This is evidence based🤫

Watch, follow, and discover more trending content.

25/09/2025

Look at this🤔
This is evidence based🤫

Address

Zambiya Street
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian health today posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian health today:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram