Ethiopian health today

Ethiopian health today Ethiopian Health Today is for awareness creation: health, education,foreign relation,Aid organizations,and professional development.

ተመልሷል። ይሻላል ሐኪምን ህዝብን እንዲያገለግል መድረግ እንጅ ማሰር ለሀገርም ለምንም ጥቅም የለውም። እንኳን ወደ ቤትህ ተመለስክ ዶር አብርሃም አማረ። Abrham Amare
11/04/2026

ተመልሷል። ይሻላል ሐኪምን ህዝብን እንዲያገለግል መድረግ እንጅ ማሰር ለሀገርም ለምንም ጥቅም የለውም። እንኳን ወደ ቤትህ ተመለስክ ዶር አብርሃም አማረ። Abrham Amare

በሶስት ክልሎች የጤና ባለሙያዎች እጥረት መኖሩ ተገለጸሚያዚያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም (አሐዱ ሬዲዮ) - የጤና ሚኒስቴር በሶስት ክልሎች ማለትም በአፋር፣ በሶማሌ እና በጋምቤላ ክፍት የስራ ቦታ...
11/04/2026

በሶስት ክልሎች የጤና ባለሙያዎች እጥረት መኖሩ ተገለጸ

ሚያዚያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም (አሐዱ ሬዲዮ) - የጤና ሚኒስቴር በሶስት ክልሎች ማለትም በአፋር፣ በሶማሌ እና በጋምቤላ ክፍት የስራ ቦታዎች ቢኖሩም የባለሙያዎች እጥረት መኖሩን ለአሐዱ አስታውቋል።

የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ ሚኒስቴሩ በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ሀይል የመቅጠር አቅም ቢኖረውም ራቅ ወዳሉ አካባቢዎች ሄደው የመስራት ፍላጎት እንደሌላቸው ተናግረዋል።

ይህንን ችግር ለመፍታትም በምን ዓይነት አማራጮች ላይ ትኩረት መደረግ እንዳለበት በሚል ውይይት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ዶክተር ደረጄ አክለውም ከጥቅማ ጥቅም ጋር በተገናኘ ከጤና ባለሙያዎች የሚነሱ ጥያቄዎች መኖራቸውን ጠቅሰው ችግሮቹን ለመፍታት በተለይም ባለሙያዎቹ ተደራጅተው የመኖሪያ ቤት እንዲኖራቸው እና የትርፍ ሰዓት ክፍያን ጨምሮ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የጤና ባለሙያዎች ባልተፈለገ መንገድ ወደ ውጭ ሀገር እንዳይሰደዱ እና በሀገር ውስጥ ቆይተው እንዲያገለግሉ ከትምህርት ስርዓት ማሻሻያ ጀምሮ የተለያዩ እርምጃዎች መወሰዳቸውን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው ከመንግስት መደበኛ የስራ ሰዓት ውጪ በግላቸው እንዲሰሩ መፈቀዱንም አስታውሰዋል።

በ ፋሲል አረጋይ
✍️

 ታግተው የነበሩት የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል ባለሙያዎች እና የአምቡላንስ ሹፌር ከእገታ ተለቀዋል።ሁሉም ባለሙያዎቻችን እንዲለቀቁ ከደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል እና ከታጋች ቤተሰቦች ጎን በመቆም...
10/04/2026



ታግተው የነበሩት የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል ባለሙያዎች እና የአምቡላንስ ሹፌር ከእገታ ተለቀዋል።

ሁሉም ባለሙያዎቻችን እንዲለቀቁ ከደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል እና ከታጋች ቤተሰቦች ጎን በመቆም ከፍተኛ ርብርብ ላደረጋችሁ ለደባርቅ ከተማ የሐገር ሽማግሌዎች፣ ለደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል ሰራተኞች እና ታካሚዎች፣ ለዳባት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሙያተኞችና ታካሚዎች፣ መንገድ ላይ የቆመችውን አምቡላንስ ከነመድኃኒቷ ወደ አምባጊወርጊስ ከተማ ላስገባችሁ አካላት፣ ለአማራ ሐኪሞች ማህበር፣ በቅርብም በሩቅም ያላችሁ ወገኖችን በሙሉ ከልብ እናመሰግናለን!!!

መልካም የስቅለት በዓል!!!
✍️ ደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል

ከኢትዮጵያ አእምሮ ሕክምና ማሕበር የተሠጠ መግለጫ(ይነበብ!)✍️ St. Paul's Hospital Millennium Medical College-SPHMMC
10/04/2026

ከኢትዮጵያ አእምሮ ሕክምና ማሕበር የተሠጠ መግለጫ
(ይነበብ!)
✍️ St. Paul's Hospital Millennium Medical College-SPHMMC

SPHMMC, Dutch Experts Partner to Boost Medical Equipment CapacitySt. Paul’s Hospital Millennium Medical College (SPHMMC)...
09/04/2026

SPHMMC, Dutch Experts Partner to Boost Medical Equipment Capacity

St. Paul’s Hospital Millennium Medical College (SPHMMC) has entered into a partnership with Netherlands-based volunteer experts to enhance healthcare service delivery through the donation and installation of essential medical equipment.

SPHMMC Provost Dr. Muluken Tesfaye held discussions with a multidisciplinary team of Dutch professionals and Netherlands-based Ethiopian experts, focusing on the effective implementation of the joint initiative.

The delegation included Mr. Arjan de Jager, Managing Director of the Barneveld Technical Training Institute (BTO); Mr. Christiaan Oudenaarden, project coordinator at St. Paul’s; Mr. Dinkbeyesus Yacob, an electrical design engineer based in the Netherlands; Dr. Sara Aynalem, a former colleague of St. Paul’s Hospital; and Mr. Elbert Wildemans, a technical expert and instructor affiliated with BTO.

The discussion was also attended by Dr. Lemi Belay, Vice Provost for Academic and Medical Services, and Dr. Addis Kassahun , Head of the Dental and Maxillofacial Department.

Speaking on the occasion, Dr. Muluken noted that the partnership would significantly strengthen the institution’s capacity to deliver high-quality healthcare services and improve patient care outcomes.

The collaboration includes the establishment of four fully equipped dental clinics, each outfitted with modern dental chairs, X-ray units, dental systems, compressors, complete furnishings, reception areas, and other essential treatment equipment. Delivered in a fully packed container, the support will directly benefit the Dental and Maxillofacial Department and is expected to markedly enhance dental care services at the hospital.

In addition to the dental facilities, the project also provides a gynecology treatment chair, electric hospital beds, wheelchairs, and a wide range of medical supplies.

Implementation of the project is being carried out by experts from the Netherlands, including Mr. Christiaan Oudenaarden and Mr. Elbert Wildemans.

According to the project team, the installation and handover process is progressing as scheduled and is expected to be finalized soon.

The partnership underscores ongoing efforts to strengthen healthcare infrastructure and expand access to essential medical services across Ethiopia
✍️ St. Paul's Hospital Millennium Medical College-SPHMMC

የአምቡላንስ አገልግሎትን ለማጠናከር የሚያስችል ስልጠና ተሰጠበኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በክልሉ አምቡላንስ አገልግሎት በመስጠት ላይ ከሚገኙ ቅርን...
09/04/2026

የአምቡላንስ አገልግሎትን ለማጠናከር የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በክልሉ አምቡላንስ አገልግሎት በመስጠት ላይ ከሚገኙ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችና ማስተባበሪያዎች ለተወጣጡ የአምቡላንስ ሾፌሮችና የፕሮግራም አስተባባሪዎች በአምቡላንስ አስተዳደር፣ አያያዝ እና ሪፖርት አቀራረብ ላይ በአርባ ምንጭ ከተማ ሲሰጥ የቆየውን ስልጠና ዛሬ አጠናቋል፡፡

ለአራት ተከታታይ ቀናት በተሰጠዉ ስልጠና ተሳታፊዎች በመጀመሪያ ደረጃ የሕክምና እርዳታ አሰጣጥ ላይ ያላቸውን እውቀትና ክህሎት ማሳደግ እንዲሁም የሪፖርት አቀራረብን ለማጠናከር ያለመ እንደሆነ ነው የተገለጸው።

በስልጠናዉ የመጀመሪያ ደረጃ እርዳታ፣ መሰረታዊ የህይወት ማዳን ተግባር ፣ የአደጋ ጊዜ ምላሽና አስተዳደር፣ አምቡላንስ አገልግሎት፣ የተግባቦት ስርዓትና ሌሎችም ርዕሰ ጉዳዮች ተካተዋል፡፡

ሰልጣኞች በስልጠናዉ ያገኙትን ዕውቀትና ክህሎት በተግባር ላይ አዉለዉ በተሻሻለና በዘመነ መልኩ ቀልጣፋ አገልግሎት ለሕብረተሰቡ ለመስጠት ቃል ገብተዋል።

በአሁኑ ወቀት በክልሉ ሰላሳ አምስት የማኅበሩ አምቡላንሶች አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኙም ለማወቅ ተችሏል።

መረጃዉ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኮሚዩኒኬሽን ነዉ

ለሰብዓዊነት እንኖራለን!
---------------------
Training Provided to Strengthen Ambulance Services

The Ethiopian Red Cross Society (ERCS) Southern Ethiopia Regional Branch has completed a 4-day training in Arba Minch Town, focused on improving ambulance management, handling, and reporting.

The training was provided to ambulance drivers and program coordinators selected from branch offices and coordination units that currently provide ambulance services in the region. It focused on ambulance management, handling, and reporting.

The training, which lasted for four consecutive days, aimed to enhance participants’ knowledge and skills in first aid provision, as well as to strengthen their reporting practices.

Topics covered during the training included first aid, Basic Life Support (BLS), emergency response and management, ambulance services, communication systems, and other related subjects.

The trainees have committed to applying the knowledge and skills they gained in practice and to delivering improved, modern, and efficient services to the community.

Currently, 35 ERCS ambulances are serving communities across the region—making a real difference every day.
Source: Regional Branch Office Communication

We Live for Humanity!


---------------
📌Website: https://redcrosseth.org/
📌Instagram፡ https://www.instagram.com/ercs1935/
📌LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/ethiopian-red-cross-society/
📌YouTube: https://www.youtube.com/
📌X(Twitter): https://x.com/EthioRedCross
📌Telegram: https://t.me/ERCSHQ
📌 Tiktok: https://www.tiktok.com/
📌 Flickr፡- 137615657@N05/" rel="ugc" target="_blank">https://www.flickr.com/photos/137615657@N05/
✍️ Ethiopian Red Cross Society

Ethiopia subsidized the Health sector with 160 Billion ETB or,Ethiopia subsidized Ethiopian Health professionals with 16...
09/04/2026

Ethiopia subsidized the Health sector with 160 Billion ETB or,
Ethiopia subsidized Ethiopian Health professionals with 160 Billion ETB,

Whatsoever it is good👇

የመድሀኒትናምግብ የጥራት ቁጥጥር ስርአትን ለማጠናከር በመውጫና መግቢያ ኬላ ላይ የሚተገበር ባለሶስት ደረጃ የቁጥጥርና የፍተሻ ስርዓት ሆኖ የሚያገለግል የሞጆ ደረቅ ወደብ የፍተሻ ሚኒ ላብራቶ...
09/04/2026

የመድሀኒትናምግብ የጥራት ቁጥጥር ስርአትን ለማጠናከር በመውጫና መግቢያ ኬላ ላይ የሚተገበር ባለሶስት ደረጃ የቁጥጥርና የፍተሻ ስርዓት ሆኖ የሚያገለግል የሞጆ ደረቅ ወደብ የፍተሻ ሚኒ ላብራቶሪ በይፋ ተጀምሯል
____________

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ፍሬ ህይወት አበበ በመውጫና መግቢያ ኬላ ላይ የሚተገበር ባለሶስት ደረጃ የቁጥጥርና የፍተሻ ስርዓት ሆኖ የሚያገለግል የሞጆ ደረቅ ወደብ የፍተሻ ሚኒ ላብራቶሪ በይፋ አስጀምረዋል።

ላብራቶሪው መድሀኒቶችና ምግቦች ከመሰራጫታቸው በፊት በወደብ ላይ እንዳሉ ፍተሻ እንዲደረግላቸው በማስቻል ጥራትና ፈዋሽነታቸው የተረጋገጡ ምርቶች ብቻ ለህብረተሰቡ እንዲደርሱ ያግዛል ብለዋል።

እንደዚህ ያሉ ላብራቶሪዎችን ማስፋፋት አስፈላጊ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታዋ ይህንን መነሻ በማድረግ ወደ ሌሎቹ ቅርንጫፎች የማስፋት ስራ መሠራት እንዳለበት ገልጸዋል። ለዚህም በቂ የሰው ኃይልና ግብዓት ስለሚያስፈልግ ከአጋር አካላት ጋር በተቀናጀ ሁኔታ በመስራት ስርዓቱን ዘላቂ ለማድረግ አጋሮችና ባለድርሻ አካላት ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

የምግብና መድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሂራን ገርባ በሞጆ ደረቅ ወደብ የሚገኘው የመድሀኒትና የምግብ ሚኒ ላብራቶሪ የፍተሻ አገልግሎቱን በይፋ መጀመሩን አስታውቀዉ፤ በቀጣይም የፍተሻ ስርዓቱን በማጠናከር፣ በሁሉም ቅርንጫፎች ለማስፋፋት እቅድ መያዙን ገልጸዋል።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB
✍️ Ministry of Health,Ethiopia

በጤና ተቋማት የነዳጅ እጥረት እንዳይፈጠር ምን እየተሠራ ነው ?ባሕር ዳር፡ ሚያዝያ 01/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በአማራ ክልል ከሚገኙ ጤና ተቋማት መካከል በማዕከላዊ ጎንደር ዞን  የጉሃላ  ...
09/04/2026

በጤና ተቋማት የነዳጅ እጥረት እንዳይፈጠር ምን እየተሠራ ነው ?

ባሕር ዳር፡ ሚያዝያ 01/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በአማራ ክልል ከሚገኙ ጤና ተቋማት መካከል በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የጉሃላ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አንዱ ነው።

የጉሃላ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሥራ አሥኪያጅ ደርሶ ሲሳይ ሆስፒታሉ ከ200 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን እያስተናገደ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የመብራት መቆራረጥ ችግር እየገጠመው እንደኾነም ገልጸዋል። ለዚህም ችግሩ ሲገጥም ነዳጅን ተጠቅሞ በጄኔሬተር አገልግሎት እየተሠጠ እንደኾነ ነው ያነሱት።

ሆስፒታሉ በሚገኝበት ከተማ የነዳጅ ማደያ አለመኖሩ ለሥራቸው እንቅፋት እንደኾነባቸው ተናግረዋል።ይህ ደግሞ መብራት ሲጠፋ በጄኔሬተር በሆስፒታሉ የሚሰጡ የላበራቶሪ ምርመራዎች፣ ቀዶ ጥገና አገልግሎቶች እና በሪፈር ወደ ሌሎች ተቋም ለሚላኩ ታካሚዎች የአንቡላንስ አገልግሎት ለመስጠት አስቸጋሪ እንዳደረገባቸውም አንስተዋል።

የአማራ ክልል ጤና ቢሮ የሕክምና እና ታድሶ አገልግሎት ዳይሬክተር ድንበሩ ባየልኝ አሁን ካለው የነዳጅ አጠቃቀም ሁኔታ ጋር ተያይዞ የጎላ ባይኾንም ችግሮች እንደተስተዋሉ ገልጸዋል።

ይህንን ለመቅረፍም ለጤና ተቋማቱ ቅድሚያ ትኩረት እንዲሰጡ እየተደረገ እንደኾነ ተናግረዋል። በዚህም እስካሁን ባለው ሁኔታ የገዘፈ ችግር አለመኖሩን አንስተዋል።

ሕክምና የ24 ሰዓት አገልግሎት በመኾኑ በዚህ ሂደት የመብራት መቆራረጥ ሊገጥም ይችላል ብለዋል። ለዚህ ደግሞ ጄኔሬተር አስፈላጊ በመኾኑ ነዳጅ እንደሚያስፈልግ ነው የገለጹት። ከፍ ያለ ሕክምና የሚያስፈልገው ታካሚ ሲኖር በሪፈር ወደ ሌሎች ተቋማት ለመላክ አጋዥ ለኾኑት አንቡላንሶች ነዳጅ አስፈላጊ እንደኾነም ተናግረዋል።

አሁን ላይ የተፈጠሩ ውስን ክፍተቶች እና ቀጣይ ሊገጥሙ የሚችሉ ሁኔታዎችን ታሳቢ ያደረገ የቅድመ ጥንቃቄ ሥራዎች በትኩረት እየተሠራ እንደኾነም አንስተዋል።

በቀጣይ ጉሃላ እና ሌሎች በአቅራቢያቸው የነዳጅ ማደያ የሌላቸው ሆስፒታሎች ውል ወስደው ለጤና ተቋማት እና አንቡላንሶች ቅድሚያ እንዲሰጣቸው የሚያደርጉ ሥራዎች ይሠራሉ ብለዋል።

በተለያየ ምክንያት ችግር ለገጠማቸው የጤና ተቋማት መፍትሔ ለመስጠትም ከክልል እስከ ወረዳ ድረስ ያሉ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች ጥረት እንዲያደርጉም አሳስበዋል።

ዘጋቢ፦ ሮዛ የሻነህ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
✍️ Amhara Media Corporation/ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን

በኢትዮጵያ አማራ ክልል፣ ሰሜን ጎጃም ዞን፣ ሰሜን ሜጫ ወረዳ መጋቢት 24/2018 ሶስት የጤና ባለሙያዎች በጥይት ተገድለዋል። ነርስን ጨምሮ ሁለቱ የጤና ባለሙያዎች በሰሜን ሜጫ በሚገኘው አቢ...
08/04/2026

በኢትዮጵያ አማራ ክልል፣ ሰሜን ጎጃም ዞን፣ ሰሜን ሜጫ ወረዳ መጋቢት 24/2018 ሶስት የጤና ባለሙያዎች በጥይት ተገድለዋል።

ነርስን ጨምሮ ሁለቱ የጤና ባለሙያዎች በሰሜን ሜጫ በሚገኘው አቢዮት ፋና የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ጣቢያ ሲሰሩ የነበሩ ሲሆን፣ ሦስተኛው ደግሞ በግል የጤና ተቋም ውስጥ ይሠሩ ነበር።

ግድያው የተፈጸመው በአማራ ክልል በኢትዮጵያ መንግስት እና በክልል ኃይሎች መካከል ግጭት እየተስፋፋ ባለበት ወቅት ነው።

የጤና ባለሙያዎች በማንኛውም ጊዜ ሊጠበቁ እና ለሚያስፈልጋቸው ሰው ሁሉ ህይወትን የሚያድኑ ስራዎቻቸውን ሊያከናውኑ ይገባል። በተጨማሪም የአለም ጤና ድርጅት በተፈፀመው ግድያ ገልተኛ አካል ምርመራ እንዲያደረግ ይጠይቃል።

adhanom

Happy Neurosurgeons Day!Today, on World Neurosurgery Day, St. Paul's Hospital Millennium Medical College (SPHMMC) apprec...
08/04/2026

Happy Neurosurgeons Day!
Today, on World Neurosurgery Day, St. Paul's Hospital Millennium Medical College (SPHMMC) appreciates our neurosurgeons and all those serving across Ethiopia for their vital role in saving lives and improving neurological health.
We commend their dedication and reaffirm our commitment to advancing neurosurgical care through training, quality services, and research.

St. Paul's Hospital Millennium Medical College celebrates and honors all neurosurgeons for their life-saving work and dedication to advancing neurological care.
SPHMMC reaffirms its commitment to strengthening neurosurgical services, expanding access to care, and fostering academic excellence through education and research.
✍️ St. Paul's Hospital Millennium Medical College-SPHMMC

Address

Zambiya Street
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian health today posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian health today:

Share