30/10/2025
"የ2017 በጀት አመት የኢላላ ስኬቶቻችን ለቀጣይ ስራችን ስንቅ የሚሆን ነው"
በአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ባለስልጣን ቦሌ ቅርንጫፍ ክላስተር 4 ጽ/ቤት የ2017በጀት አመት እቅድ አፈፃፀምና የ2018 በጀት አመት እቅድ ከባለድርሻ አካላት ጋር ገምግመዋል።
በቦሌ ክ/ከተማ የምግብ መድሃኒት ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ዳይሬክቶሬት ሽታሁን የኔታ እና የክላስተር 4 አስተባባሪ ወ/ሮ ብርቱካን ፈንታሁን ከባለድርሻ አካላት ጋር የ2017 እቅድ አፈፃፀም የ2018 በጀት አመት እቅድ እንዲሁም የ2018 አንደኛ ሩብ አመት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።
ጽ/ቤቱ በ2017 በጀት አመት በኢላላ ዋንጫ ቃልኪዳን በርካታ እቅዶችን ከእቅድ በላይ መፈፀሙ የተገለፀ ሲሆን እነዚህ አፈፃፀሞች ለበጀት አመቱ ስንቅ ሆነው የሚያገለግሉ መሆኑ ተገልጿል።
ባለድርሻ አካላት በቀረበው የአፈፃፀም ሪፖርት ላይ ሀሳብ አስተያየት እንዲሁም ጥያቄዎች ተነስተው በጥልቀት ውይይት ከተደረገ በኋላ የቦሌ ምግብ መድሀኒት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ሽታሁን የኔታ እና ወ/ሮ ብርቱካን ፈንታሁን የቦሌ ክላስተር 4 አስተባባሪ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶ ውይይቱ ተጠናቋል።
ጥቅምት 20/2018 ዓ.ም