Digital Hakim

  • Home
  • Digital Hakim

Digital  Hakim Physicians activist

ዛሬ በማረሚያ ቤት ዶ/ር ዳንኤልን ለመጠየቅ የገቡ ሬዚደንት ሐኪሞች ነበሩ፤ ዕናቱም ልትጠይቀው ገብታ ስለነበር እያለቀሰች ሲያያት በጣም ተረብሾ ሌሎችንም ማናገር ሳይችል ቀርቷል።ምስኪን ኢትዮ...
19/07/2025

ዛሬ በማረሚያ ቤት ዶ/ር ዳንኤልን ለመጠየቅ የገቡ ሬዚደንት ሐኪሞች ነበሩ፤ ዕናቱም ልትጠይቀው ገብታ ስለነበር እያለቀሰች ሲያያት በጣም ተረብሾ ሌሎችንም ማናገር ሳይችል ቀርቷል።

ምስኪን ኢትዮጵያዊት ዕናት ልጇን ለፍታ አሳድጋ፣ በተገቢው መንገድ አስተምራ ለማልቀስ ተዳርጋለች!
በጣም የተረበሸ ስሜት ውስጥ ነው የዋልኩት።
መበርታት ይገባናል!

አንድነታችን ካላጠናከርን ግን ነጣጥለው ሊበሉን ነው።
Inbox

19/07/2025

ሀገራችን እኮ ብዙ የተለፋባቸው 120 ስፔሻሊስት እና ሰብ-ስፔሻሊስት ሀኪሞች በአንድ ፕሌን ተሳፍረው የሚሰደዱባት ሀገር ነች። በወንጭፍ ተምሮ በረሃብ የሚቆራመትን ሀኪም ሲሰድብ የሚውል ካድሬ በሚመራት ሀገር ላይ እንደት ርሃቡን ችሎ ይቀመጥ።

እኛ የምንታገለው ከመሰደድ እየታሰርንም ፣ እየተገደልንም ፣ እየተገረፍንም ችግሮች በመጠኑም ቢሆን ይሰካከሉ ይሆናል ህዝባችንም ከጎናችን ይሰለፋል በሚል ተስፋ ነው።

ጥሪ በጤና ዙሪያ ለምትሰሩ የማህበራዊ ሚዲያ አካላት በጤና ዙሪያ ላይ የምትሰሩ እና የጤና ባለሞያውን እሮሮ የሚያሳስባችሁ የጤና ነክ ማህበራዊ ድረ ገፆች በሙሉ የጤና ባለሞያዎች ጥያቄ መልስ ...
19/07/2025

ጥሪ በጤና ዙሪያ ለምትሰሩ የማህበራዊ ሚዲያ አካላት

በጤና ዙሪያ ላይ የምትሰሩ እና የጤና ባለሞያውን እሮሮ የሚያሳስባችሁ የጤና ነክ ማህበራዊ ድረ ገፆች በሙሉ የጤና ባለሞያዎች ጥያቄ መልስ እስከሚያገኝ ድረስ ከአሁን ቀደም ስታደርጉ ከነበረው ድምፅ የመሆን ስራ በእጅጉ ጨምራችሁ የጤና ባለሞያውን ድምፅ እና የዚህን ትግል አላማ እንድታስጋቡ ስንል የአክብሮት ጥሪያችንን እናቀርባለን::የጤና ባለሞያው ልክ እንደ ሌላው ዜጋ ሁሉ ያለበትን አሰቃቂ ሁኔታ ለህዝብ እንድታደርሱ ስንል አደራ እንላለን!
አንድነት ሀይል ነው
የኢትዮጵያ ጤና ባለሞያዎች ንቅናቄ

19/07/2025

የተማረው ሓይል ማስራብ ፖሊቲካዊ ስልት ነው

"የኮሌጅ እትብቴ በተቀበረባት ጎንደር፣ የጎንደር ሕክምና ሳይንስ ኮሌጅ, የዛሬዋ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ የምርቃ ስነስርአት ላይ ለተሰጠኝ እውቅናና ሽልማት ምስጋናዬን ለማቅረብ ቃላቶች ያጥሩኛል"...
19/07/2025

"የኮሌጅ እትብቴ በተቀበረባት ጎንደር፣ የጎንደር ሕክምና ሳይንስ ኮሌጅ, የዛሬዋ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ የምርቃ ስነስርአት ላይ ለተሰጠኝ እውቅናና ሽልማት ምስጋናዬን ለማቅረብ ቃላቶች ያጥሩኛል" - ዶ/ር ፈቀደ አግዋር ፤ የልብ ቀዶ ህክምና ሀኪም

የተሸላሚዎች ዝርዝር

1. የፕረዚደንታዊ ሌጋሲ ከፍተኛ ሽልማት ዘርፍ
- ፕ/ር Mengesha Admassu (የቀድሞው የዩኒቨርሲቲው ፕረዚደንት)
- ፕ/ር Yared Wondimkun (የመጀመሪያው የዩኒቨርሲቲው ፕረዚደንት)

2. የማኅበረሰብ ተጽዕኖ የላቀ ሽልማት (Community Award)
- ፕ/ር ብሩክ ላጲሶ

3. ዓለም አቀፋዊ የመሪነት ዘርፍ (Global Leadership Award)
- ዶ/ር Kesete Admasu (የቀድሞ Federal Ministry of Health Ethiopia ሚኒስትር)

4. ወጣት ሥራ ፈጣሪና ተጽዕኖ ፈጣሪ ዘርፍ
- አቶ Jaleta Mulatu

5. በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ድጋፍ እና አጋርነት ዘርፍ
- ዶ/ር Kassu Ketema Gurmu MD, PhD

6. በትምህርት እና ምርምር ልኅቀት ዘርፍ
- ዶ/ር ኤርምያስ ዲኖ

7. በሕዝባዊ አገልግሎት ዘርፍ (Public Service Award)
- ዶ/ር ተዋበች ቢሻው (የመጀመሪያዋ ሴት ጤና መኰንን)

8. በሕይወት ዘመን አበርክቶ ዘርፍ
- ፕ/ር ጉታ ዘነበ

9. በጤናና ሰብዓዊ አገልግሎት ዘርፍ
- ዶ/ር Fekede Agwar

10. በባሕል፤ በመገናኛ ብዙኀን እና ኪነ-ጥበብ ዘርፍ
- አቶ sileshi Girma (ዴዔታ፣ ቱሪዝም ሚኒስቴር)

11. በሥራ ፈጠራና ኢንቨስትመንት ዘርፍ
- Dr Girma Ababi

12. በዲያስፖራ አምባሳደርነት ከፍተኛ ተሸላሚ
- ዶ/ር ኑሩ አብሲኖ

13. ልዩ የሰብዓዊ አገልግሎት ሽልማት (Social Humanitarian Impact Award)
- ወጣት ዳዊት አየነው (“ካለን ብናካፍል")

ሐምሌ 12, 2017 ዓ.ም
University of Gondar

19/07/2025

plan B

19/07/2025

Dr Jerry neurosurgeon

19/07/2025

💥Hamster እና የጤና ባለሙያ💥

የሰሞኑ የጤና ባለሙያዎች ጥያቄ ሲነሳ አንዳንድ የማህበረሱ ክፍል መደናገጥ ይታይባቸዋል። የዉሸትም የመሰላቸው አሉ። ጤና ባለሙያ የሀገሪቱ ከፍተኛ ተከፋይ፣ በውብ ቤት የሚኖር፣ መኪና ያለው እና ኑሮ ደልቶኣቸው የፈለጉትን እያደረጉ የሚኖሩ ነበር የሚመስላቸው። እውነታው ግን በተቃራኒ ነው። ከስራ ጫና አንፃር ዝቅተኛ ተከፋይ: የWHO የክፈያ እርከን እንኳ ያልደረሱ።

በኢትዮጵያ የደሃ መስፈርት ከድህነት በታች ላይ ተመዳቢ አይደለም ቤት፣ መኪና በቀን 2 ጊዜ መብላት የማይችል፡ የቤት ኪራይ መክፈል የከበደው ፡ በእዳ ምክንያት አንገቱን ደፍቶ የሚኖር እና ቤተሰቦቹን እንኳ ለማየት ያልታደለ ነው።

ሰሞኑን ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚዘዋወሩ የጤና ባለሞያ ጥያቄዎች መኖር ከበደን እንጂ ስራ አንሰራም አይደለም። እየራበን ነው እንጂ የቢራ መጠጫ አነሰን አይደለም። የቤት ኪራይ መክፈል አልቻልንም እንጂ ቤተመንግሥት ገንቡልን አይደለም።

24/7 ሳይሰለች ደከመኝ ሳይል የሚሰራ ሰራተኛ ራበኝ ሲል፣ መኖር ከበደኝ ሲል ፡ መታከም ከብዶት ሀኪሙ በገንዘብ እጥረት ሲሞት እንዴት ዝም ይባላል። እንዴት ፖለቲካ ይሆናል።

ቤተሰብ መመስረት ዘበት ነው። ተቸግረው ያሰተማሩትን ወላጆች ፡ አሳዳጊዎች፡ ጓደኞችን ማገዝ ማስደሰት ብርቅ ነው። መዝናናት፣ ከሚወዱት ጋር ጊዜ ማሳለፍ አይታሰብም። ይህ የጤና ባለሙያ ህይወት ነው።
ለስፔሻሊት 12K ለዶክተር 10K ሌሎች ከ9K በታች ይከፈላቸዋል። በቅርባችን ኬንያ የበግ ጠባቂዎች ደሞዝ ይበልጠናል።

ሀምሰተር ከJunior Nurse እስከ senior nurse
ከ GP እስከ specialist Dr. ሁሉም የጤና ባለሙያ ሀምሰተር ሲሰሩ ነበር። ይህ ምን ያክል የጤና ዘርፍ ሰራተኞች ህይወት እንደከበዳቸው ያሳያል። ምን ያክል ችግር ውስጥ እንዳሉ ይመሰክራል።

ጤናማ ያልሆነ ሀኪም ሊያክም አይችልም። እየተራበ Focus ሊያደርግ አይችልም። እዳ እያለበት ሊረጋጋ አይችልም።

የጤና ባለሙያተኞች ጥያቄያቸው የኔም ያንችም የሁሉም ዜጋ ጥያቄ መሆን አለበት።
ነገ ላይ ልጅህ ሚስትህ/ ባለሽ እናትና አባታችህ በነሱ እጅ ይታከማሉ። ይህ ጥያቄ ችላ ተብሎ ሊሆን ይችላል። ነብሰ ጡር ሚሰትህን ፣ ICU ተኝቶ የሚታከም ልጅህ ፣ ድንገተኛ የሚመጣ አባትህ ፣ ክትትል የምታደረገዋ እናትህ ህክመና ሲያጡ አትውቀሳቸው። ወደው ሳይሆን የጠፉት ምግብ ፈለጋ ሄደው ነው። አንትን ማገልገል ሳይፈልጉ ቀርተው ሳይሆን እዳቸውን ለመክፈል ስራ ፈልገው ሄደው ነው። ማህበረሰቡን ማከም ተሰላችተው ሳይሆን የታኪሲ አተው ነው የቀሩት። ተረዳቸው።

ለጤና ባለሙያተኞች ድምፅ እንሁናቸው።

ህይወት ስናድን ኖረናል አሁን የራሳችንን እናድን።

ሕይወት ስናድን ኖረናል! አሁን ግን የራሳችንንም ሕይወት ማዳን ይኖርብናል! ሰዓቱ እያለቀ ነው! 58 ቀናት ብቻ ቀርተዋል !ዝምታው አሁን ያብቃ!

We save lives! Now it's time to save ours too! The Clock is Ticking! 58 Days to Hold the System Accountable. The Silence Should End Now!

lubbuu baraaraa jiraanne! Amma garuu lubbuu ofii keenyaas baraaruu qabna!
Sa'aatiin lakkaawaa jira! Guyyoota 58 qofatu hafe! Amma booda hin callisnu!

ህይወት እናድሓና ፀኒሕና ኢና! ሕጂ ንዓርስና ነድሕነሉ ግዜ እዩ!
እቲ ሰዓት ይውዳእ ኣሎ! 58 መዓልቲ ጥራሕ ቀርየን! ሱቕታ ሕዚ ይኾናኖ!

shemppuwa ashii

19/07/2025

ልብ በሉ 👐👋 እየሰራን እየጠየቅን ነው

ከረጅም ጊዜ በኋላ ዛሬ ለመፃፍ ተነሳሁ። እኔ በባለፈው count down ፎቶ ተነስቼ በመለጠፌ ወደ ገጠር እንድሄድ ምናምን ተብዬ ለ2 ወራት ገደማ ቤቴ ተቀምጬ አስቀያሚ ጊዜ አሳልፊያለው። ከ...
19/07/2025

ከረጅም ጊዜ በኋላ ዛሬ ለመፃፍ ተነሳሁ።
እኔ በባለፈው count down ፎቶ ተነስቼ በመለጠፌ ወደ ገጠር እንድሄድ ምናምን ተብዬ ለ2 ወራት ገደማ ቤቴ ተቀምጬ አስቀያሚ ጊዜ አሳልፊያለው። ከብዙ ውይይት እና ሽምግልና በኋላ በሌላ ሆስፒታል ተመድቤ ስራ ጀምሪያለው።

እውነቱን ለመናገር ከላይ እየተገለፀ እንዳለው መንግስትም እየሰራቹ ጠይቁ ብሏል። ታዲያ ፍራቻው ምንድነው? በሰላማዊ መንገድ እስከሆነ ድረስ መብትን ለመጠየቅ ለምን እንፈራለን? የጤና ባለሞያው በዚህ ደረጃ ፈሪ እና በሰው መስዋዕትነት ጥቅም ለማግኘት የሚጓጓ ብቻ በመሆኑ አዝናለው። እኔ በሰላማዊ መንገድ እስከሆነ ድረስ ጥያቄያችንን መጠየቄን እቀጥላለው። የትኛውንም መስዋዕትነትም በደስታ እከፍላለው። አሁን ከምንኖረው ኑሮ ምንም ይሻላል። We live in this world once so let’s do the right thing and fight for our rights. What’s the use of education if we can’t stand United in time of injustice and scared to request our rights?

ዛሬ ልፅፍ ተገድጃለሁ!!!! እናንተ የተከበራችሁና እየተገፋችሁ ሂወትን የምትታደጉ ውብ የኢትዮጵያ ልጆች ራሳችሁን እየጎዳችሁ ሰዎችን የምጠግኑ የዘጎቻችሁን ህመም የምትታመሙ ዕንቁዎች ጊዜው ሆ...
19/07/2025

ዛሬ ልፅፍ ተገድጃለሁ!!!! እናንተ የተከበራችሁና እየተገፋችሁ ሂወትን የምትታደጉ ውብ የኢትዮጵያ ልጆች ራሳችሁን እየጎዳችሁ ሰዎችን የምጠግኑ የዘጎቻችሁን ህመም የምትታመሙ ዕንቁዎች ጊዜው ሆነና ተገፋችሁ በደለኛ ተባላችሁ ጋወን ለባሾች ተባላችሁ ብዙ ብዙ ሰማችሁ እኛም ከንፈር እየመጠጥን ዝም አልን ብንናገር እኛን ደግሞ ምን እንደሚሉን እያሰብን!!! ልጅ ዳቦ ሲል አባት ልጁን አስሮ ከገረፈ አባትየው ጤነኛ ነው ወይ???? አባትየውስ አባውራ ወይም የቤተሠቡ መሪ አስተዳዳሪ ሁኖ ቢቀጥል ለቤተሠብ ምን በቀጣይ ምን ሊፈጥር ይችላል ????? ለማንኛውም በአንድነት የህግ ባለሙያ እያማከራችሁ ትግላችሁን ቀጥሉ ለናንተ ባይደርስ ለቀጣይ ትውልድ ቀን ይውጣ ጤና ይከበር።አንድነት ይጎላል

19/07/2025

#57% ግብር ? የዘመናችን ጀግና
👇👇

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Digital Hakim posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your practice to be the top-listed Clinic?

Share