Gezeso Health Center Laboratory Department

Gezeso Health Center Laboratory Department Our services are listed infront of our department door. It is very good for patient satsfuction and our happness

የመንግስት አቅጣጫና ፖሊሲ ተከትለው የሚሰሩ የጤና ልማት ድርጅቶች ሪፖርት አሰጣጥ ላይ የሚሥተዋሉ ጉድለቶች ሊታረሙ እንደሚገባቸዋ የደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ የሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲ...
10/04/2023

የመንግስት አቅጣጫና ፖሊሲ ተከትለው የሚሰሩ የጤና ልማት ድርጅቶች ሪፖርት አሰጣጥ ላይ የሚሥተዋሉ ጉድለቶች ሊታረሙ እንደሚገባቸዋ የደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ የሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲቲዩት አስታውቋል፡፡

የደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ የሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲቲዩት በሶስት ዋና ዋና ተግባሮች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ይታወቃል ጤና እና ጤና ነክ ችግር ፍቺ ምርምሮች ላይ የሕብረተሰን ጤና አደጋ ክስተቶች መመልከት እንዲሁም ጥራት ያለው የላብራቶሪ አገልግሎት ወደ ላቀ ደረጃ አቅም መገንባት ላይ ትኩረት ሰቶ እየሰራ መሆኑን መነሻ በማድረግ ተግባራትን በየደረጃው ይገመግማል በዚህ ረገድ መደበኛና በድንገተኛ ወረርሽኞችን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ ተግባራት በመንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች በጋራ ይፈፀማሉ፡፡

ኢኒስቲቲዩቱ ልዩ ትኩረት ያሻቸዋል ቡሎ ካስቀመጣቸው አሳቦች መካከል ወባን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ተግባራት፣ የለሽሚያሲስ በሽታ ቅኝት ፣የክትባት ጥራትን በመደበኛው የክትባት አሰጣጥ ትግበራ ማረጋገጥ ፣በተለያዩ ጊዜያቶች እየቀረቡ ያሉ የማጅራት ገትር በሽታን በላብራቶሪ የማረጋገጥ የሚሉት አሳቦች ተካተውበታል፡፡

የመንግስት አቅጣጫና ፖሊሰ ተከትለው የሚሰሩ የጤና ልማት አጋር ድርጅቶች አንድ ዕቅድ፣ አንድ በጀት ፣እንድ ሪፖርት መርዕ መነሻ በማድረግ በተገቢው ሪፖርት የሚያደርጉ አካላት የመኖራቸውን ያክል በዞኖችና፣ በልዩ ወረዳ ስራዎችን እና በወረዳዎች ጭምር ስራዎች ቢሰሩም በተገቢው ሪፖርት ከማድረግ ረገድ ተግዳሮት መሆኑን አንስቷል፡፡

የደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ የሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲቲዩት ጤና እና ጤና ነክ ድንገተኛ አደጋዎች ቅኝት ምላሽ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ታሪኩ መለሰ ውይይቱን መርተውታል በንግግራቸው በመደበኛና በወረርሽኝ መልኩ ለሚከሰቱ የመከላከልና መቆጣጠር ተግባራትን አጣምሮ የመምራት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ተደርጎ ሊወስድ እንደሚገባው አስረድተዋል፡፡
የአየር ንብረት ለውጥን ተከትለው እያጋጠሙ ያሉ ሁኔታዎችን አጽንዖት ሰጥቶ መከታተል በተለይም ከኮሌራ በሽታ ጋር በተያያዘ ሊያጋጥሙ የሚጭሉ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ በተገቢው መስራት እንዲሁም የተወሳሰበ የምግብ እጥረትን መነሻ በማድረግ የልየታ ስራዎችን ማከናወን ይጠበቃል ብለዋል፡፡

የሕብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት ባካሄደው የሳምንታዊ ውይይት ወባን የወባ በሽታን ለመከላከል፣ ለመቆጣጠር የኩፍኝ ወረርሽኝ በሽታ፣የኮቪድ 19 ወረርሽኝ፣ ፣የተቅማጥ በሽታ፣የእናቶችና ህጻናት ሞት፣ የእብድ ውሻ በሽታ፣ከፍተኛ የምግብ እጥረት በሽታ፣ የአንትራክስ በሽታ ክስተት፣የወረርሽኝ ክስተቶች የተወሳሰበ የምግብ እጥረት የልየታ ተግበራ፣የእከክ በሽታ የኮሌራ ያሉበትን ሁኔታ ገምግሟል አቅጣጫዎችንም አስቀምጧል፡
ዕቅድን መነሻ በማድረግ ነባራዊ ሁኔታና ዋና ዋና ጉድለቶች በማመላከት መልኩ በአጭር በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ የሚከናወን ዋና ዋና ጉዳዮችን መሳካት ተግባራት የጋራ ርብርብን ይሻሉ አሳቦች ቀርበዋል፡፡
የደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መንግስት ጤና ቢሮ

10/04/2023

የተሟላ የላቦራቶሪ አገልግሎት መስጠት ለህብረተሰቡ ጤናን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነዉ።
Laboratory is the backbone of other health departments.

if we have a CBC machine we save different people's life additionaly the first available tests.
29/07/2022

if we have a CBC machine we save different people's life additionaly the first available tests.

Laboratory centers have been set up to dx monkey pox in Ethiopia.Laboratory departments have a great role for identifica...
22/06/2022

Laboratory centers have been set up to dx monkey pox in Ethiopia.
Laboratory departments have a great role for identification of different viruse and their causative ones.

ትልቅነት አልሞ መራመድ ስሆን ስከቱ ደስታዉ ነዉ።
13/05/2022

ትልቅነት አልሞ መራመድ ስሆን ስከቱ ደስታዉ ነዉ።

የ11 ልጆች አባትና የ69 ዓመት አዛውንት የዘንድሮ የጅማ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ገቢ ተማሪ ሆነዋል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የ11 ልጆች አባት እና የ69 ዓመቱ አዛውንት ታደሰ ጊችሌ የጅማ ዩኒቨርሲቲ እየተቀበላቸው ካሉ አዲስ ገቢ ተማሪዎች መካከል አንዱ ሆነዋል።

የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስደው 502 የመግቢያ ነጥብ ያመጡት እና በጅማ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡት ተማሪ ታደሰ ጊችሌ ፥ ከምዕራብ ወለጋ ገንጅ ወረዳ መነሻቸውን አድርገው ለትምህርት ጅማ ዩኒቨርሲቲ በዕድሜ ከልጆቻቸው በትምህርት ደግሞ ከእኩዮቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል።

በ1945 ዓ.ም የተወለዱት አቶ ታደሰ የ11 ልጆች አባት ሲሆኑ ፥ ባለቤታቸው ወይዘሮ ቢዲጡ ቶላ እና ልጆቻቸው ‘’ትምህርቴን ጨርሼ ትልቅ ደረጃ እንድደርስ ትናንትም ዛሬም አስተዋፅኦ አድርገዋል’’ ብለዋል።

እንደ እኩዮቻቸው ፊደል ቆጥረው ሳይንሱን አርቅቀው የሚፈልጉበት የልጅነት ራዕያቸዉ ላይ ለመድረስ በቤተሰብ ሃላፊነትና በዝቅተኛ የኑሮ ሁኔታ ቢፈተኑም ፥ ካሰቡበት ለመድረስ ባላቸው ጠንካራ የመማር ፍላጎት ዩኒቨርሲቲ መግባታቸውን ይናገራሉ፡፡

በጅማ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አዲስ ገቢ የሆኑት ተማሪ ታደሰ ፥ ‘’አንዳንዶች በዚህ እድሜህ ትምህርቱን አቋርጠህ ለምን ወደ እርሻህ አትመለስም ይሉኛል ፤ እኔ ግን የልጅነት ህልሜን ማሳካት ስላለብኝ ከትምህርቴ ጎን ለጎን የእርሻና የቡና ችግኝ እያስፋፋሁ ቆይቻለሁ’’ ብለዋል።

ተማሪ ታደሰ ጊችሌ ወደ ፊት በዩኒቨርሲቲ ቆይታ በጤና ዶክትሬት ማጥናት እና በሕክምናው ዘርፍ የሚታዩ ክፍተቶችን በማስተካከል ኢትዮጵያን እና ወገኔን ማገልገል እፈልጋለሁ ማለታቸውን ከጅማ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

12/05/2022

እኛ ስለ እናንቴ እንጨነቃለን
በመሆኑም በርካታ አገልግሎቶችን በመስጠት ላይ እንገኛለን።
ጥቅቶቹን ላስቃኛችሁ
A.cost services
1.HCG test
2. HBsag test
3.Widal test
4.Weilfleix test
5.stool examination
6.Hematocrit determination
7.Urine chemical determination
8.Urine microscopic examination
9.Blood group and RH
10.VDRL/RPR test
11.Blood glucose determination

B. Cost Free services
1.VCT test
2.urine analysis for ANC
3.VDRL for ANC
4.Blood group for ANC
5.COVID 19 examination
6.TB Examination
7.hematocrit determination for ANC

እንኳን ወዴ ገዜሶ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የላቦራቶሪ ድፓርትመንት ገጽ በሰላም መጡ።ይህ ገጽ በድህሬ ገጹ ላይ የምለጥፋቸዉን ማንኛዉም ነገር ብኖር ላቦራቶሪ ክፍል ዉስጥ ደንበኞቻችን የምያገኙአቸ...
12/05/2022

እንኳን ወዴ ገዜሶ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የላቦራቶሪ ድፓርትመንት ገጽ በሰላም መጡ።
ይህ ገጽ በድህሬ ገጹ ላይ የምለጥፋቸዉን ማንኛዉም ነገር ብኖር ላቦራቶሪ ክፍል ዉስጥ ደንበኞቻችን የምያገኙአቸዉን አገልግሎቶች ስሆን ለላ የማይመለከተዉ ሰዉ የማይገባዉን አስጸያፍ ነገር መለጠፍ አይቻልም።

Address

Bonkke
Arba Minch'
ADDEDUBUSHA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gezeso Health Center Laboratory Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Gezeso Health Center Laboratory Department:

Share