
22/08/2024
የአዳሬ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ በዛሬው ዕለት ባዘጋጀው የሰራተኞች ፎረም ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የጤና ጣቢያውን የ 2016 በጀት ዓመት አፈፃፀምና የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ ገመገመ።
በመድረኩም የሀዋሳ ከተማ አስ/ጤና መምሪያ ሀላፊ አቶ ማራዶና ዘለቀ ፣ የመምሪያው ማኔጅመንት አባላት እና ተወካዮች፣ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳዳሪ አቶ አምራች እና የክፍለ ከተማው አመራሮች፣ የዳካ እና የፍላደልፊያ ቀበሌ ስራስኪያጆች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተው ከቀረበው ሪፓርት መነሻ ሰፊ ውይይት ማድረግ ተችሏል።
በተጨማሪም በተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የስራ ክፍሎች እና ባለሙያዎች የማበረታቻ ሽልማትና የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
ነሀሴ 16/2016
አዳሬ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ