09/04/2026
የሚሊኒዬም ጤና ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የStaff Forum አካሄደ::
#ሚያዚያ 01/2018 ዓ.ም
የሚሊኒዬም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የሠራተኞች ፎረም (Staff Forum) በዛሬው ዕለት አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የጤና ጣቢያው ኃላፊ፣ የማኔጅመንት አባላትና የጤና ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን ፣ በዋናነት በጤና ጣቢያው የአገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
ተሳታፊ ባለሙያዎችም የተሻለ የሥራ አካባቢን ለመፍጠርና ለታካሚዎች ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት የሚያግዙ የተለያዩ ገንቢ ሃሳቦችን በማንሳት ተወያይተዋል።
በመጨረሻም ለተነሱ ሃሳቦች ምላሽና የቀጣይ መፍትሄ አቅጣጫዎችን ተቀምጠዉ ዉይይቱ በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል።
አ/ጣቢያ
#ሀዋሳ