31/10/2025
ሻብያ ኤርትራን ሲገነጥል ግብጻዊው ቡትሮስ ቡትሮስጋሊ የተባበሩት መንግስታት ፕሬዝዳንት መሆኑ ጥሩ አጋጣሚ ፈጥሮለት ነበር!
ስድስተኛው የተባበሩት መንግስታት ፕሬዝዳንት ግብጻዊው ቡትሮስ ቡትሮስጋል የተባበሩት ፕሬዝዳንት በመሆን የተሾመው ጥር በ1984 ዓ.ም. ነበር፡፡ ይህ ግለሰብ ኤርትራ ሁሉንም የባህር በር በ1985 ዓ.ም. ወስዳ እንድትገነጠል በማመቻቸት ግንባር ቀደም ሚና የተጫወተ ነው፡፡ በሱ ቦታ ሌላ ሰው ቢሆን ኖሮ በዚህ ደረጃ ኢትዮጵያ ላይ ግፍ አይፈጸምም ነበር፡፡
ቢሆንም በወቅቱ የነበረው መንግስት ጊዜያዊ እና ህጋዊ ባለመሆኑ በኢትዮጵያ ህዝቦችም ሆነ በአለም ሐገሮች ህግ መሰረት የኤርትራ መገንጠል ተቀባይነት የለውም፡፡ በሻብያ ወታደር ጉልበት ተፈጥሮ የሚገኝ እና ዘላቂ ያልሆነ ነው፡፡ ሰውዬው ኤርትራ ከ1200 ኪሜ በላይ የባህር ዳርቻዎችን የኢትዮጵያ የአሰብ ግዛትን ጨምሮ ምንም ሳይቀር ተጣድፎ እንድትወስድ ያደረገው ኢትዮጵያ አባይን እንዳትገድብ በማዳከም ለመስበር ነበር፡፡ ሰውዬው ከ7 አመት በፊት ሞቷል፡፡
ቢሆንም ግብጽ እ.አ.አ በ2011 በአረብ ማእበል የተነሳ ፕሬዝዳንት ሆስኒ ሙባረክ ከስልጣኑ በህዝባዊ ማእበል ሲወገድ፤ ኢትዮጵያ የአባይ ፕሮጀክትን በይፋ ለመገደብ ወሰነች፤ እና ዛሬ ላይ ግድቡ ተገድቦ ተጠናቆ ይገኛል፡፡ የግብጽ ሴራም አፈር በልቷል፡፡ ወደፊት በኤርትራ መገንጠል ላይ ለሰራችው ሴራም፤ የሚመጣው ትውልድ ለእያንዳንዱ ሊትር ውሃ በማስከፈል ይበቀላታል፡፡ የግዜ ጉዳይ ነው፡፡
በአሁኑ ወቅት በኤርትራ እና በኢትዮጵያ መካካል የድንበር ማካለሉ አልተጠናቀቀም፡፡ ድንበሩ በህጋዊነት አልተሰመረም፡፡ ድንበር ማካለሉ ሳይጠናቀቅ በውዝግብ የአልጀርስ ስምምነትን ሁሉ በማካተት እና በጦርነት ሳይሰመር እስከዛሬ እንዳለ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅት 122 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ህዝብ 3.6 ሚሊዮን የኤርትራ ህዝብ በታሪክ አጋጣሚ በጉልበት ጠራርጎ የወሰደበትን የባህር በሩን እየጠየቀ ይገኛል፡፡