14/03/2026
🤱 ( ) 🏥
👉በህክምና እርዳታ የሚደረግ የተፈጥሮ ወሊድ ማለት እናቲቱ በምጥ ወቅት ስታምጥ የህክምና ባለሙያዎች በልዩ መሣሪያዎች (ቫኩም ወይም ፎርሴፕስ) በመታገዝ ህፃኑ እንዲወጣ የሚረዱበት ሂደት ነው።
ይህ አይነቱ ወሊድ ለምን ሊያስፈልግ ይችላል?
🥚
ምጡ ከሚገባው በላይ ከቆየ እና እናቲቱ ህፃኑን በራሷ ግፊት ማስወጣት ካልቻለች።
🥚
እናቲቱ ህፃኑን በሰላም ለመውለድ የሚያስፈልጋት ጉልበትና አቅም ሲሟጠጥ።
🥚
የህፃኑ የልብ ምት በጣም ሲጨምር ወይም ሲቀንስ፣ እንዲሁም በቂ ኦክስጅን እያገኘ እንዳልሆነ ሲታወቅ።
አንዳንድ ጊዜ ደግሞ እናቲቱ ከፍተኛ የደም ግፊት ካለባት እና ሁለተኛው የምጥ ደረጃ (የማማጥ ወቅት) ከሚገባው በላይ ከቆየ፣ የደም ግፊቱ እንዳይባባስ ሲባል በህክምና እርዳታ እንዲወለድ ሊደረግ ይችላል።
ለተጨማሪ የጤና እና የእናቶች እንክብካቤ መረጃዎችን ለማግኘት ጽሁፎቼን መከታተልሽን ቀጥዪ።
#ዶክተርአፍሪካንይጠይቁ