እናት መካከለኛ ክሊኒክ / Enat Medium Clinic

እናት መካከለኛ ክሊኒክ / Enat Medium Clinic ለተሻለ ህክምና ማን እንደ እናት!!

🤰   ( )፦  ​በእርግዝና ወቅት የእግር እብጠት መከሰት በጣም የተለመደና አብዛኛውን ጊዜ የተፈጥሮ ለውጦች ውጤት ነው። ይህ ለምን ይከሰታል? እንዴትስ መከላከል ይቻላል?​🔍  ፦1. ​የፈሳ...
07/05/2026

🤰 ( )፦
​በእርግዝና ወቅት የእግር እብጠት መከሰት በጣም የተለመደና አብዛኛውን ጊዜ የተፈጥሮ ለውጦች ውጤት ነው። ይህ ለምን ይከሰታል? እንዴትስ መከላከል ይቻላል?
​🔍 ፦
1. ​የፈሳሽ መጠን መጨመር፦ ሰውነት ጤናማ የፅንስ እድገትን ለመርዳት ተጨማሪ ፈሳሽ እና ደም ያመነጫል። ይህ ፈሳሽ ወደ ህብረ ሕዋሳት (Tissue) ውስጥ በመግባት እብጠት ያስከትላል።
2. ​የማህፀን መጠን መጨመር፦ ፅንሱ እያደገ ሲሄድ በደም ስሮች ላይ ጫና ይፈጥራል። ይህም የደም ዝውውርን በማዝገየት ደም በእግር አካባቢ እንዲከማች ያደርጋል።
3. ​የሆርሞን ለውጥ፦ እንደ ሪላክሲን ያሉ ሆርሞኖች ሰውነት ፈሳሽ እንዲይዝ ያደርጋሉ።
4. ​የስበት ኃይል፦ ለረጅም ሰዓት መቆም ወይም መቀመጥ ፈሳሾች ወደ ታችኛው የእግር ክፍል እንዲወርዱ ያደርጋል።
​✅ ፦
1. ​እግርን ከፍ ማድረግ፦ ሲቀመጡ ወይም ሲተኙ እግርዎን ከፍ አድርገው በመሰቀል የፈሳሽ ዝውውሩን ማገዝ።
2. ​በግራ ጎን መተኛት፦ ይህ አተኛኘት በደም ስሮች ላይ የሚፈጠረውን ጫና በመቀነስ የደም ዝውውርን ያሻሽላል።
3. ​ምቹ ጫማ ማድረግ፦ በጣም ጥብቅ ያልሆኑ እና ለሰውነት ምቹ የሆኑ ጫማዎችን መጠቀም።
4. ​ውሃ በበቂ ሁኔታ መጠጣት፦ የሚገርመው ነገር፣ ብዙ ውሃ መጠጣት ሰውነት ከመጠን በላይ ፈሳሽ እንዳይይዝ ይረዳል።
​⚠️ ?
​እብጠቱ የተለመደ ቢሆንም፣ የሚከተሉት ምልክቶች ከታዩ ግን ለከፍተኛ ደም ግፊት (Preeclampsia) ወይም ለሌላ ችግር ምልክት ሊሆን ስለሚችሉ በአስቸኳይ ወደ ጤና ተቋም መሄድ ያስፈልጋል፦
​📍 ድንገተኛ የሆነ የፊት ወይም የእጅ እብጠት ከተከሰተ።
​📍 ከባድ ራስ ምታት ወይም የዕይታ መለወጥ ካጋጠመዎት።
​📍 በአንድ እግር ላይ ብቻ የሚታይ ከፍተኛ እብጠት፣ ህመም እና መቅላት ካለ።
! 💙
👩‍⚕️
በዶ/ር አብነት አዳነ (የፅንስና ማህፀን ህክምና ስፔሻሊስት)
​📍 #አድራሻ፦ ዱራሜ፣ ከዶ/ር ቦጋለች ገበቡሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል ፊት ለፊት።
​📞 ፦
0913295363 / 0926268855
🌐 Telegram: https://t.me/+Wm5YIC1zUOMzMjE0
🌐 Facebook: Enat Clinic
! 👍✨

 ! 🤰✨​ውድ እናቶች፤ የልጅዎ የጤና መሰረት እርሶ ነዎት!​በእርግዝና ወቅት ፎሊክ አሲድ (Folic Acid) መውሰድ ለምን እንደሚያስፈልግ ያውቃሉ? ፎሊክ አሲድ የፅንስ የጭንቅላት እና የአ...
07/05/2026

! 🤰✨
​ውድ እናቶች፤ የልጅዎ የጤና መሰረት እርሶ ነዎት!
​በእርግዝና ወቅት ፎሊክ አሲድ (Folic Acid) መውሰድ ለምን እንደሚያስፈልግ ያውቃሉ? ፎሊክ አሲድ የፅንስ የጭንቅላት እና የአከርካሪ አጥንት እድገት በአግባቡ እንዲከናወን የሚያደርግ ወሳኝ ቫይታሚን ነው።
?
✅ የፅንስ የነርቭ ቱቦ ችግሮችን (Neural Tube Defects) ለመከላከል፤
✅ የአከርካሪ አጥንት ክፍተት (Spina Bifida) እንዳይከሰት ለማድረግ፤
✅ የጭንቅላት እድገት የተሟላ እንዲሆን ይረዳል።
?
ለማርገዝ ሲታሰብ ጀምሮ እስከ መጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት መውሰድ ለልጅዎ የጤና ዋስትና ነው።
!
​📍 አድራሻችን፦ ዱራሜ፣ ከዶ/ር ቦጋለች ገቡሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል ፊት ለፊት።
​🏥
!

“የኢትዮጵያ የከንፈርና ላንቃ ክፍተት በጎ አድራጎት ማኅበር” በይፋ ተመሰረተ​​በኢትዮጵያ የከንፈርና ላንቃ ክፍተት ያለባቸውን ወገኖች ሕይወት ለመለወጥና ዘላቂ የሆነ ሀገር በቀል የሕክምና ድ...
07/05/2026

“የኢትዮጵያ የከንፈርና ላንቃ ክፍተት በጎ አድራጎት ማኅበር” በይፋ ተመሰረተ


​በኢትዮጵያ የከንፈርና ላንቃ ክፍተት ያለባቸውን ወገኖች ሕይወት ለመለወጥና ዘላቂ የሆነ ሀገር በቀል የሕክምና ድጋፍ ሥርዓት ለመዘርጋት ያለመው “የኢትዮጵያ የከንፈርና ላንቃ ክፍተት በጎ አድራጎት ማኅበር” ዛሬ በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ስምንተኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው አዳራሽ በይፋ የምስረታ ሥነ-ሥርዓቱን አካሂዷል።

​ይህ ታሪካዊ ማኅበር እንዲመሰረት ሐሳቡን በማመንጨትና በሳይንሳዊ ጥናት በመደገፍ ረገድ ቀዳሚውን ሚና የተጫወቱት፣ በሀገራችን የመጀመሪያው የፕላስቲክና የሪኮንስትራክቲቭ ቀዶ ሕክምና ፕሮፌሰር የሆኑት ፕሮፌሰር መኮንን እሸቴ ናቸው።

ፕሮፌሰሩ በምስረታው ዕለት ስለ ከንፈርና ላንቃ ክፍተት ሳይንሳዊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ በቀጣይም በማኅበሩ ውስጥ በቦርድ አባልነት እንዲያገለግሉ ተመርጠዋል።

​ማኅበሩ ሲቋቋም አስፈላጊውን የፋይናንስ ድጋፍ (Fund) በማድረግ “Smile Train” የተባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት ከፍተኛ እገዛ አድርጓል። እስከ ዛሬ ድረስ የከንፈርና ላንቃ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት በዋናነት በዓለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፍና መሪነት ሲከናወን ቢቆይም፤ አሁን ግን ይህንን ወሳኝ የሕክምና አገልግሎት ወደ ሀገር በቀል ተቋም በማሸጋገር የፋይናንስ ምንጮችንና ቴክኒካዊ አቅሞችን በራስ አቅም ለማስተባበር ማኅበሩ በይፋ ሥራውን ጀምሯል።

ማኅበሩን በበላይነት እንዲመሩና ግቦቹን እንዲያሳኩ በዕለቱ የተመረጡት የሥራ አስፈፃሚ አባላት የሚከተሉት ናቸው፦
​አቶ ተስፉነህ እምሩ – የማኅበሩ ሥራ አስኪያጅ
​ወ/ት ፌቨን አድማሱ – የሒሳብ ሹም
​ወ/ት የሮሰን ተሾመ – ኦዲተር
​ወ/ት ሚስጥረ አስፋው – ገንዘብ ያዥ


የማኅበሩ ዋና ዓላማ የከንፈርና ላንቃ ክፍተት ያለባቸው ዜጎች ጊዜውን የጠበቀ ቀዶ ሕክምና እንዲያገኙ ማድረግ ብቻ ሳይሆን፤ የጥርስ፣ የስነ-ልቦና፣ የንግግር ሕክምና እና ሌሎች ተያያዥ ድጋፎችን ያካተተ “ሁሉን አቀፍ” አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ፣ ህክምናውና በሽታው በመንግስት ትኩረት እንዲያደርግ፣ በከንፈርና ላንቃ ክፍተር ላይ ጥናትና ምርምርምን ለማበረታት፣ ማኅበረሰቡ ላይ ንቃተ ህሊና ለመጨመር ነው።

በተጨማሪም ማኅበሩ አዲስ እንደመሆኑ መጠን ሥራዎቹን በብቃት ለማከናወን የቢሮ ፍላጎት ያለበት በመሆኑ፣ የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ይህንን ሀገር በቀል ተቋም በቢሮ አቅርቦት፣ ሌሎችም እገዛዎች በማማሟላት በኢትዮጵያ ሲቪል ማኅበራት ማደራጃ ፈቃድ እንዲያገኝ የአንበሳውን ድርሻ ወስዷል። ጤና ሚኒስቴርም ለማኅበሩ ምስረታ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል።

​በምስረታው ሥነ-ሥርዓት ላይም የጤና ሚኒስቴር ተወካይ፣ የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የአካዳሚክና የምርምር ምክትል ፕሮቮስት የሆኑት ዶክተር መረርቱ ተመስገን ተገኝተው ማኅበሩ መመሥረቱ ለሀገሪቱ የሕክምና ዘርፍ ትልቅ እመርታ መሆኑን ገልጸው ደስታቸውን ገልጸዋል።

እንደ አርቲስት ፍቃዱ ከበደ እና ሌሎች ታዋቂ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችም ተገኝተው ለማኅበሩ አጋርነታቸውን አሳይተዋል።

​በመጨረሻም፣ ማኅበሩ ለጤና ሚኒስቴር፣ ለየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ እና ለፕሮፌሰር መኮንን እሸቴ ላበረከቱት ልዩ አስተዋፅኦ የምስጋና ምስክር ወረቀት አበርክቷል።

​📍 የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን

📅 ሚያዝያ 28/2018 ዓ.ም
📍
📌 Follow Us on Social Media

አንድ የ30ዎቹ መጀመሪያ ላያ ያለ ወጣት ለወራት ያህል በግራ በኩል የላይኛው ሆድ አካባቢ በሚመላለስ ውጋት ተሰቃይቶ ነበር። እንቅስቃሴ ባደረገ ቁጥር ህመሙ እየተቀሰቀሰበት የቀን ተቀን ህይወ...
07/05/2026

አንድ የ30ዎቹ መጀመሪያ ላያ ያለ ወጣት ለወራት ያህል በግራ በኩል የላይኛው ሆድ አካባቢ በሚመላለስ ውጋት ተሰቃይቶ ነበር። እንቅስቃሴ ባደረገ ቁጥር ህመሙ እየተቀሰቀሰበት የቀን ተቀን ህይወቱን እረፍት ነስቶት ከረመ።

[የሕክምና ታሪኮች #19]

ከሆድ አልትራሳውንድ እስከ ሲቲ ስካን፣ አልፎ ተርፎም የኮሎኖስኮፒ ምርመራዎች ተደርጎለት የህመሙ ምክንያት ሊታወቅ አልቻለም ነበር። ለወራት የህመም ማስታገሻ ቢወስድም ህመሙ ግን ቅንጣት ታህል ሊታገስለት አልቻለም።

የተሰሩለትን ምርመራዎች ካሳየኝ በሁዋላ እንዳለውም ሁሉም ነገር ምንም እንደማያሳይ ስረዳ ምርመራውን ቀየርኩትና የሆዱን ጡንቻ እንዲያጠነክር አንገቱን እጥፍ ሳረገው ህመም እንደተሰማው ከፊቱ ገፅታ እንዳስተዋልኩ ወዲያው በጣቴ ህመም ሚሰማውን ቦታ ስነካው ህመሙ ይበልጥ ተባባሰ ይህ ቀላል አካላዊ ምርመራ ህመሙ ከውስጥ አካል ሳይሆን ከሆድ ግድግዳ ነርቭ መቆንጠጥ ጋር የተያያዘ መሆኑን አረጋገጠልኝ።

በመቀጠልም ልክ ህመሙ ባለበት ቦታ ላይ አስፈላጊውን መዳኒት በመርፌ ሰጠውት፣ ለወራት ሲያሰቃየው የነበረው ውጋት በአንድ ቀን ውስጥ ድራሹ ጠፋ። ከዚያ በኋላ በነበሩት የክትትል ወራቶች ውስጥ ህመሙ ዳግመኛ አልተመለሰም፤ እሱም እንደ ልቡ መንቀሳቀስ ጀምሮ ወደ ቀድሞ ሰላማዊ ህይወቱ በደስታ ተመለሰ።

ዋና መልዕክት: የፊት ለፊት የሆድ ግድግዳ ነርቭ መቆንጠጥ (Anterior cutaneous nerve entrapment syndrome) ብዙ ጊዜ ከሆድ ውስጥ ሕመሞች ጋር እየተመሳሰለ ለቆየ የሆድ ሕመም መንስኤ ሲሆን፣ ይህ ሕመም አብዛኛውን ጊዜ በሆድ ግድግዳ ላይ ባለች አንዲት ትንሽ ቦታ፣ በንቅስቃሴ ወይም የሆድ ጡንቻን በማጠንከር ይብብሳል። ይህም በአካላዊ ምርመራ ብቻ በሽታውን ለመለየት ያስችላል። ከሁሉም በላይ ደግሞ፣ መዳኒት በመርፌ መልክ ሕመሙ በባሰበት ቦታ በመስጠት በሽታውን ለማረጋገጥም ሆነ በሽታውን ለማከም ይረዳል።

በመሆኑም ይህንን የፊት ለፊት የሆድ ግድግዳ ነርቭ መቆንጠጥ እንደ አንድ የሆድ ህመም መንስኤ ግምት ውስጥ ማስገባት ተገቢ ነው።

[ማስታወሻ: ዶ/ር ሰገነት በአስተማሪ የህክምና ፅሁፎች ዘርፍ ለሊንክድኢን (LinkedIn) ሽልማት ታጭተዋል:: ድምጽዎን በመስጠት ያበረታቱ: https://lnkd.in/dWpfNTgH ]

Segenet Bizuneh
Internist, GI/Hepatology fellow
St. Paul's Hospital Millennium Medical College - SPHMMC

Telegram: t.me/HakimEthio

06/05/2026
🔵  ፡   ( )  ?​የዘር ፍሬ ካንሰር ( ) በአብዛኛው ከ 15–49 የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ወንዶችን የሚያጠቃ ቢሆንም፣ አስቀድሞ ከተደረሰበት ሙሉ በሙሉ የመዳን ዕድሉ ከ90% በላይ ...
06/05/2026

🔵 ፡ ( ) ?
​የዘር ፍሬ ካንሰር ( ) በአብዛኛው ከ 15–49 የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ወንዶችን የሚያጠቃ ቢሆንም፣ አስቀድሞ ከተደረሰበት ሙሉ በሙሉ የመዳን ዕድሉ ከ90% በላይ መሆኑን ያውቃሉ?
፣ ! 📢
​🛑
​ካንሰሩ መጀመሪያ ላይ ህመም ስለማይኖረው ብዙዎች ችላ ሊሉት ይችላሉ። እነዚህን ምልክቶች ልብ ይበሉ፦
1. ​በዘር ፍሬ ላይ የሚወጣ እብጠት ወይም ጠንከር ያለ ነገር
2. ​በቆለጥ (Sc***um) አካባቢ የክብደት ስሜት መሰማት
3. ​በታችኛው የሆድ ክፍል ወይም በብሽሽት አካባቢ የሚሰማ መጠነኛ ሕመም
4. ​በቆለጥ ከረጢት ውስጥ ድንገተኛ የፈሳሽ መከማቸት።
​⚠️
​ምንም እንኳ ትክክለኛው መንስኤ ባይታወቅም፣ የሚከተሉት ሁኔታዎች ተጋላጭነትን ሊጨምሩ ይችላሉ፦
፦ ህፃናት ሲወለዱ ፍሬያቸው ወደ ከረጢቱ ካልወረደ (Cryptorchidism)።
፦ በቅርብ የቤተሰብ አባል ላይ ተመሳሳይ የካንሰር ታሪክ ካለ።
#ዕድሜ፦ በተለይ ወጣቶችና መካከለኛ ዕድሜ ላይ የሚገኙ ወንዶች።
​✅ ?
​ይህ የካንሰር ዓይነት በዘመናዊ ሕክምና (በቀዶ ጥገና፣ በኬሞቴራፒ ወይም በጨረር) የመዳን ዕድሉ እጅግ ከፍተኛ ነው። ዋናው ቁልፍ ግን ቀድሞ መመርመር ነው!
​💡 ?
1. ​ራስን መመርመር፦ በየወሩ የዘር ፍሬዎ ላይ ያልተለመደ ለውጥ ወይም እብጠት መኖሩን በራስዎ ያረጋግጡ።
2. ​ሐኪም ማማከር፦ ማንኛውም ዓይነት ለውጥ ካዩ—ሕመም ባይኖረውም እንኳ—በፍጥነት ወደ ጤና ተቋም በመሄድ ባለሙያ ያማክሩ።
​ !
​💬 ስለዚህ ጉዳይ ወይም ስለ ሌላ የጤና ርዕስ ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ ይፈልጋሉ? ጥያቄዎን በኮሜንት ያጋሩን!
​📍 ።
📍 #መገኛችን፡ ዱራሜ ዶ/ር ቦጋለች ገቡሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል ፊት ለፊት
📞 ስልክ፡ 0913295363 ወይም 0926268855
-
#የወንዶችጤና

06/05/2026

ልጅ የመውለድ ህልምዎ እውን እንዲሆን ለማገዝ ዝግጁ ነን! 🌸

 !🌸የእናትነት ወይም የአባትነት ጉዞ አንዳንድ ጊዜ ፈታኝ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ተስፋ መቁረጥ አያስፈልግም! በእናት መካከለኛ ክሊኒክ፣ ዘመናዊ የምርመራ መሣሪያዎችን እና ርኅራኄ የተሞላ...
06/05/2026

!🌸

የእናትነት ወይም የአባትነት ጉዞ አንዳንድ ጊዜ ፈታኝ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ተስፋ መቁረጥ አያስፈልግም! በእናት መካከለኛ ክሊኒክ፣ ዘመናዊ የምርመራ መሣሪያዎችን እና ርኅራኄ የተሞላበት የህክምና አገልግሎትን በማቀናጀት ለችግርዎ መፍትሄ እንሰጣለን።

በዘርፉ ሰፊ ልምድ ባላቸው በዶ/ር አብነት አዳነ (የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት) የሚመራው ክሊኒካችን የሚከተሉትን አገልግሎቶች ይሰጣል፡-

✅ የመሀንነት ምርመራ
✅ የወር አበባ ኡደት መዛባት ህክምና
✅ የሆርሞን መዛባት ችግሮች
✅ ተደጋጋሚ የፅንስ መጨናገፍ ህክምና
✅ የወንድ የዘር ፍሬ እክል ህክምና

ቤተሰብ የመመስረት ጉዞዎን ዛሬውኑ ይጀምሩ። በእኛ ዘንድ በክብር እና በታማኝነት ይስተናገዳሉ!

📍 #መገኛችን፡ ዱራሜ ዶ/ር ቦጋለች ገቡሬ መታሰቢያ አጠቃላይ ሆስፒታል ፊት ለፊት
📞 #ስልክ፡ 0913295363 ወይም 0926268855

-

05/05/2026

Address

Durame

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when እናት መካከለኛ ክሊኒክ / Enat Medium Clinic posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to እናት መካከለኛ ክሊኒክ / Enat Medium Clinic:

Share