Adare General Hospital, Hawassa

Adare General Hospital, Hawassa One of general hospital in sidaama region and serving more than 2 million people

25/02/2026
የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የሁለተኛ ሩብ ዓመት የሰራተኞች ፎረም አካሄደ።ጥር 28/2018 አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል - ሀዋሳ የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የ2018 የመጀመሪያ አጋማሽ አፈጻጸም ...
06/02/2026

የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የሁለተኛ ሩብ ዓመት የሰራተኞች ፎረም አካሄደ።

ጥር 28/2018 አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል - ሀዋሳ

የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የ2018 የመጀመሪያ አጋማሽ አፈጻጸም ግምገማ እና የሰራተኞች ፎረም ተካሂዷል።

በመድረኩ የሆስፒታሉ የ6 ወራት አፈጻጸም ቀርቦ ሰፊ ውይይት የተደረገ ስሆን በቀጣይ የአዲሱ የሰራተኞች የትርፍ ሰዓት ዲውቲ አከፋፈል ላይ በወጣው መመሪያ ላይ ሰፋ ያለ ገለጻ ተደርጓል።
በመድረኩ አዝናኝ እና አስተማሪ የጥያቄ እና መልስ ውድድሮች በሰራተኞች መካከል ተካሂዶ አሸናፊዎች ሽልማት ተቀብለዋል።
የፎረሙን መድረክ የመሩት የሆስፒታሉ ስራአስኪያጅ አቶ ዘነበ ቱርጨ ባለፉት 6 ወራት የነበረን አመርቂ አፈጻጸም በማስቀጠል መሻሻል ያለባቸው ነጥቦች ላይ አጽንኦት ተሰጥቶት መሰራት እንዳለበት ጠቁመዋል።
በአዲሱ ማስፋፊያ ህንጻን በከፊል ስራ መጀመሩን እና በቀጣይ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት ለማስጀመር ማነቆ የሆነውን ሊፍት ለማስገባት ጨረታ ለ2ኛ ዙር መውጣቱን አንስተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ አገልግሎት ለማስጀመር የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች እና የፈርኒቸር ቁሳቁሶችን የማፈላለግ ስራ እየተሠራ እንደሆነም አክለው አንስተዋል።

አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ጥር 2018 ሀዋሳ።

የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የሁለተኛ ሩብ ዓመት የህዝብ ፎረም አካሄደ።ጥር 15/2018 አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል - ሀዋሳ የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የ2018 የመጀመሪያ አጋማሽ አፈጻጸም ከህ...
23/01/2026

የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የሁለተኛ ሩብ ዓመት የህዝብ ፎረም አካሄደ።

ጥር 15/2018 አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል - ሀዋሳ

የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የ2018 የመጀመሪያ አጋማሽ አፈጻጸም ከህብረተሰቡ በተወጣጡ ተወካዮች አስገምግሟል። ሆስፒታሉ በየሶስት ወሩ በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ከህብረተሰቡ ጋር ጠንካራ ጎኖቹን እያጠናከረ መሻሻል ባለባቸው ጉዳዮች እየመከረ በለውጥ ጎዳና ላይ ይገኛል።
የሆስፒታሉ የ6 ወራት ዋና ዋና አፈጻጸሞች;-
*በተመላላሽ ህክምና አገልግሎት ያገኙ 92,481
*በድንገተኛ ህክምና አገልግሎት 18,460
*ዋና የቀዶ ህክምና አገልግሎት ያገኙ 1,487
*የወሊድ አገልግሎት 1,353 አንዲሁም በተኝቶ ህክምና 3,521፤ በእስፔሻሊቲ አገልግሎት እና በሌሎችም ከእቅድ አንጻር የተሻለ አፈጻጸም እንደተመዘገበ ተመልክቷል።

ከዝህም ባለፈ አዲሱ የማስፋፊያ ህንጻ በከፊል አገልግሎት መጀመሩ እና መንግስት ሆስፒታሉን ሙሉ ለሙሉ ለማጠናቀቅ የሰጠውን ትኩረት ተሳታፊዎች በታላቅ ደስታ አንስተዋል።

ውይይቱን የሀዋሳ ከተማ አስ/ጤና መምሪያ የህክምና አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ወ/ሰንበት ዳንኤል እና የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ጻዲቁ ጌታቸው የመሩ ሲሆን ከህብረተሰቡ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ስጥተዋል።

በመጨረሻም የሆስፒታሉ ማስፋፊያ ግንባታ በመጠናቀቁ የህክምና ቁሳቁስ የሚሟላበት ሂዴት ላይ ህብረተሰቡ ተሳትፎ የሚያደርግበት አሰራርን እንዲዘረጋ ገንቢ ሀሳብ ተነስቷል።

አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ጥር 2018 ሀዋሳ።

የገና በዓልን በስራ ገበታቸው ሆነው አገልግሎት እየሰጡ ያሉ የሆስፒታሉ ትጉህ ሰራተኞች።የሆስፒታሉ ስራአስኪያጅ እና ማኔጀመንት አባላት በዓልን በስራ ገበታቸው ተገኝተው አገልግሎት እየሰጡ የሚ...
07/01/2026

የገና በዓልን በስራ ገበታቸው ሆነው አገልግሎት እየሰጡ ያሉ የሆስፒታሉ ትጉህ ሰራተኞች።

የሆስፒታሉ ስራአስኪያጅ እና ማኔጀመንት አባላት በዓልን በስራ ገበታቸው ተገኝተው አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ትጉህ ሰራተኞችን አበረታተዋል።

አዳሬ ጠቅላላ ሆስፒታል: ታህሳስ 29/2018 ሀዋሳ።

የአዳሬ ጠቅላላ ሆስፒታል የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ማእድ የማጋራት ስነ-ስርዓት አከናወነ።ሆስፒታሉ ከዝህ ቀደም እንደሚያደርገው ህዝባዊ እና ሀይማኖታዊ በዓላትን ምክንያት በማድረግ አነ...
06/01/2026

የአዳሬ ጠቅላላ ሆስፒታል የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ማእድ የማጋራት ስነ-ስርዓት አከናወነ።

ሆስፒታሉ ከዝህ ቀደም እንደሚያደርገው ህዝባዊ እና ሀይማኖታዊ በዓላትን ምክንያት በማድረግ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ሰራተኞች ማእድ የማጋራት መርሀ-ግብርን አከናውኗል።

በመርሀ-ግብሩ ላይ የተገኙት የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ሀላፊ አቶ ይርዳቸው አናቶ ይህ ማእድ የማጋራት ተግባር ያለንን በጋራ ተካፍሎ ከመመገብ በላይ ቤተሰባዊ አንድነትንና ኢትዮጵያዊ እሴት የሚያጎለብት እንደሆነ አንስተው ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።
የሆስፒታሉ ስራአስኪያጅ አቶ ዘነበ ቱርጬ በበኩላቸው አነስተኛ ገቢ ያላቸው ሰራተኞች በዓሉን ከሌሎች ሰራተኞች ጋር በጋራ ያለንን በመከፋፈል ማክበራችን የስራ ተነሳሽነትን እንደሚጨምር አንስተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላፈዋል።

አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል-ሀዋሳ: ታህሳስ 28/2018

በአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል አዘጋጅነት ስደረግ የነበረው የ100 ቀናት እቅድ አካል የሆነው የደም ልገሳ ዘመቻ ተጠናቀቀ።ላለፉት ቀናቶች በከተማችን በፒያሳ እና አቶቴ ዋርካ አከባቢዎች ስካሄድ ...
29/12/2025

በአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል አዘጋጅነት ስደረግ የነበረው የ100 ቀናት እቅድ አካል የሆነው የደም ልገሳ ዘመቻ ተጠናቀቀ።

ላለፉት ቀናቶች በከተማችን በፒያሳ እና አቶቴ ዋርካ አከባቢዎች ስካሄድ የነበረው የደም ልገሳ ዘመቻ ላይ ህብረተሰቡ ስላደረገው ተሳትፎ እና ውድ የሆነውን ክቡር ስጦታ ለለገሱ ደም ለጋሾች ሆስፒታሉ ልባዊ የሆነ ምስጋና ያቀርባል።

እንድሁም ዘመቻውን ስያስተባብሩ ለነበሩት የላቦራቶሪ እና የMCC አባላት ምስጋና ያቀርባል።

ታህሳስ 2018 አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል -ሀዋሳ

የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የ100 ቀናት እቅድ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ-ግብር አካሄድ።አዳሬ ጠቅላላ ሆስፒታል፤ ታህሳስ 18/2018የእቅድ መርሀ-ግብር ላይ የሆስፒታሉ ማኔጅመንት፤ የዘር...
27/12/2025

የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የ100 ቀናት እቅድ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ-ግብር አካሄድ።

አዳሬ ጠቅላላ ሆስፒታል፤ ታህሳስ 18/2018

የእቅድ መርሀ-ግብር ላይ የሆስፒታሉ ማኔጅመንት፤ የዘርፍ አስተባባሪዎች እና ሰራተኞች የተሳተፉ ስሆን በተመረጡ 100 ቀናት እቅድ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ማለትም;- የእናቶችና የህጻናት አገልግሎት ፤ የቀዶ-ህክምና፤ Accreditation, የመድኃኒት እና የላቦራቶሪ ምርመራ አቅርቦት ፤ HCF, ጽዱ ተቋም ፤ ስፔሻሊቲ አገልግሎቶች እና አዲሱ የማስፋፊያ ህንጻን አገልግሎት ማስጀመር ዋነኛ ስሆኑ ጎን ለጎን የተገልጋይ እርካታን ከፍ ማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል።

እቅዱ ግብ እና የድጋፍና ክትትል ስርአት ተቀምጦበት የጋራ መግባባት ተደርሶበታል።

ታህሳስ 18/2018 አዳሬ ጠቅላላ ሆስፒታል - ሀዋሳ

26/11/2025
የጥንቃቄ መልዕክት !!! 😷👂📯🚫
12/11/2025

የጥንቃቄ መልዕክት !!! 😷👂📯🚫

መልካም ዜና!ለአይን ህክምና ፈላጊዎች በሙሉ!
27/10/2025

መልካም ዜና!
ለአይን ህክምና ፈላጊዎች በሙሉ!

እንኳን ደስ አላችሁ ደስ አለን ‼የሲዳማ ብ/ክ/መ/ጤና ቢሮ ባዘጋጀው አመታዊ የጤና ጉባኤ የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የ600,000 ብር መድኃኒት ፣ የዋንጫ እና ሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆኗል።በዝ...
20/10/2025

እንኳን ደስ አላችሁ ደስ አለን ‼

የሲዳማ ብ/ክ/መ/ጤና ቢሮ ባዘጋጀው አመታዊ የጤና ጉባኤ የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የ600,000 ብር መድኃኒት ፣ የዋንጫ እና ሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆኗል።

በዝግጅቱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ፣ የክልሉ አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደ፣ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ፣ የክልሉ ምክትላን ኃላፊዎች፣ የሐዋሳ ከተማ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ይርዳቸው አናቶ፣ የተለያዩ ሆስፒታሎችና ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ኃላፊዎችና አጋር ድርጅቶች ተገኝተዋል ።

የክልሉ ጤና ቢሮ በቀን 10/02/2018 ዓ/ም ባካሄደው የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ላይ የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል በክልሉ ካሉ ከአጠቃላይ ሆስፒታሎች 2ኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ የተለያዩ የጤና ፓኬጆችን በመተግበር ግንባር ቀደም በመሆን የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ተሸላሚ መሆን ችሏል።

ለዚህ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ላደረጉት ለአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ማኔጅመንት አባላት እንዲሁም ለሁሉም ስታፍ ትልቅ አክብሮት አለን።

አዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል፤ሲዳማ፤ኢትዮጵያ

ለአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል በአዲሱ የመንግስት የግዥ አፈጻጸም ስርዓት መመሪያ ላይ ስልጠና ተሰጠ።መስከረም 14/2018 አዳሬ አ/ሆስፒታል ስልጠናው በአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የተዘጋጀ ሲሆን ...
24/09/2025

ለአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል በአዲሱ የመንግስት የግዥ አፈጻጸም ስርዓት መመሪያ ላይ ስልጠና ተሰጠ።

መስከረም 14/2018 አዳሬ አ/ሆስፒታል

ስልጠናው በአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የተዘጋጀ ሲሆን
በ"መንግስት የግዥ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 29/2018" ላይ ከሲዳማ ክልል ግዥ እና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን በመጡ አሰልጣኞች ተሰቷል።
ስልጠናው ላይ የግዥ፤ የጨረታ ኮሚቴዎች፤ የንብረት አስተዳደር፤ ኦዲተሮች እና የማኔጅመንት አባላት ተሳታፊ ሆነዋል።

Address

Central Piassa
Hawassa
251

Telephone

+251462211661

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Adare General Hospital, Hawassa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Adare General Hospital, Hawassa:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Category

የአዳሬ አ/ ሆስፒታል ታሪካዊ አመጣጥ

አዳሬ ከአነስተኛ ክልኒክ - አጠቃላይ ሆስፒታል

1. አመሠራረት

በ1954 ዓ.ም የሀዋሳ ክሊንክ በመባል በከተማ ፣ በክልሉ እና በሌሎች አስተዳደር አካላት እርዳታ የተገነባው የመጀመሪያ የጤና ተቋም ሲሆን በወቅቱ 2,695 የነበረውን የሀዋሳ ከተማ ማህበረሰብ እና ከአጎራባች ወረዳዎች የሚመጡ ተገልጋዮችን እንዲያገለግል በወቅቱ በነበረ ጠቅላይ ግዛት እንደተቋቋመ የታሪክ ድርሳናት ያስረደሉ፡፡

ጤና ተቋሙ ሲቋቋም ዋነኛ ዓላማ የወባ ስርጭት ለመቆጣጠር ሲሆን በወቅቱ ጤና ተቋሙ ስራ ባለመጀመሩ ከከተማ ውጪ ወደ ከተማ እየመጡ በባህላዊ ህክምና ህብረተሰቡን ሲያክሙ የነበሩ አቶ ማሞ የሚባሉ የአካባቢው ሀኪም(ጤና ረዳት) “Village doctor” ነበሩ ፡፡