Nigist Eleni Hospital-WCU

Nigist Eleni Hospital-WCU Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Nigist Eleni Hospital-WCU, Hospital, Hossana.

Nigist Eleni Mohammed Memorial Comprehensive Specialized Hospital is Wachemo University's Medicine and Health Science College Hospital with almost all the specialities

ከ 2 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የሕክምና መገልገያ ቁሳቁሶች እና የመድሀኒት ድጋፍ ለኦቶና ሆስፒታል ተደረገነሐሴ 10/2017 ዓ.ም*******************************ግምቱ ከ...
16/08/2025

ከ 2 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የሕክምና መገልገያ ቁሳቁሶች እና የመድሀኒት ድጋፍ ለኦቶና ሆስፒታል ተደረገ
ነሐሴ 10/2017 ዓ.ም
*******************************
ግምቱ ከ 2 ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆን የህክምና መገልገያ ቁሳቁስ ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለ ኦቶና ኮምፕርሔንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ድጋፍ ተደርጓል።

በወላይታ ሶዶ ዩኒበርሲቲ ኦቶና ኮምፕርሔንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒተ ላይ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ድንገተኛ የእሳት አደጋ በመከሰቱ ምክኒያት በሆስፒታሉ ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ ኮምፕርሔንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታልም ጉዳት የደረሰበትን ኦቶና ሆስፒታልን መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ርብርብ የበኩሉን እንደሚወጣ መናገሩ የሚታወስ ሲሆን በዛሬውም እለት የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዳዊት ሃዬሶ፣ የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት አባላት፣ የን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው እና የን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል ማኔጅመንት አባላት በተገኙበት ለኦቶና ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ድጋፍ ተደርጓል።

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳዊት ሃዬሶ በንግግራቸው፦
በድንገት የተከሰተው የእሳት አደጋ የፈጠረው ውድመት ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ሆስፒታሉ ቀደም-ሲል ወደሚሰጠው የህክምና አገልግሎት እንዲመለስ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የበኩሉን ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል ጠቅሰው ሁላችንም በጋራ እና በአንድነት ከተባበርን በአጭር ጊዜ ውስጥ ሆስፒታሉን መልሰን ማቋቋም እንችላለን ብለዋል።

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጉቼ ጉሌ እንደገለጹት፦ በእሳት አደጋው ምክኒያት የተስተጓጎለውን የህክምና አገልግሎት መልሶ ለማስጀመር ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸው በዛሬው እለትም ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ላደረገው የህክምና መገልገያ ቁሳቁሶችና የመድሀኒት ድጋፍ ከፍ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው እንደተናገሩት፦ በኦቶና ሆስፒታል ላይ የደረሰው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ያደረሰው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ሆስፒታሉን መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት ጋር በመነጋገር ይህን ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልጸው በቀጣይም ሆስፒታሉን ለማቋቋም በሚደረግ ርብርብ ድጋፋቸው እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።

ነሐሴ 10/2017 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል ህዝብ ግንኙነት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!

08/08/2025
05/08/2025
የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኦቶና ሆስፒታል ላይ በደረሰው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ማዘኑን ገለጸ!!******************************...
28/07/2025

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኦቶና ሆስፒታል ላይ በደረሰው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ማዘኑን ገለጸ!!
********************************

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከትናንት በስትያ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኦቶና ኮምፕርሔንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ላይ በደረሰው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ማዘኑን ገልጿል።

በሆስፒታሉ ላይ የደረሰው ድንገተኛ የእሳት አደጋ እጅግ አሳዛኝ መሆኑን በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው ገልጸዋል።

አክለውም ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው እንደተናገሩት፦ በደረሰው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ምክንያት የተጎዳውን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኦቶና ኮንፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ወደ አገልግሎት ለመመለስ በሚደረገው ርብርብ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣም አንስተዋል።

ሀምሌ 21/2017 ዓ.ም
በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል!!!
Let Your light shine in the Society!!

የ2017 ዓ.ም 3ኛ ዙር የክረምት በጎ ፍቃድ መርሀግብር በን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ ሆስፒታል በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ!!ሐምሌ 18/2017 ዓ.ም******************************በጎ ፍ...
25/07/2025

የ2017 ዓ.ም 3ኛ ዙር የክረምት በጎ ፍቃድ መርሀግብር በን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ ሆስፒታል በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ!!
ሐምሌ 18/2017 ዓ.ም
******************************

በጎ ፍቃደኝነት ለጤናማ ማህበረሰብ በሚል መሪ-ቃል የ2017 ዓ.ም 3ኛ ዙር የክረምት በጎ ፍቃድ መርሀግብር የንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሰራተኞች እና ባለሞያዎች በነቂስ በመውጣት በሆስፓሉ ጊቢ ውስጥ የጽዳት ዘመቻን አከናውነዋል።

የን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል ቺፍ አስተዳደርና ልማት ዳይሬክተር እና የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች ዋና አስተባባሪ የሆኑት አቶ ተክሌ እጃጆ እንደገለጹት፦ የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች በተለያዩ መረሀ-ግብር በወጣው እቅድ መሠረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው በዛሬውም ዕለት የሆስፒታሉ ሰራተኞች በነቂስ በመውጣት በሆስፒታሉ ቅጥር ጊቢ ውስጥ የሚገኙ በርካታ ስፍራዎችን በበጎ ፍቃድ ሲያጸዱ መቆየታቸውን ገልጸው ይህም ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አንስተዋል።

በመጨረሻም ቺፍ አስተዳደርና ልማት ዳይሬክተሩ ዛሬ በበጎ ፍቃደኝነት የጽዳት ዘመቻ ላይ የተሳተፉ የሆስፒታሉ ሰራተኞችን በማድነቅ ላበረከቱት መልካም አሰተዋጽኦም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ሀምሌ 18/2017 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል ህዝብ ግንኙነት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል የተገልጋይ ውይይት መድረክ ተካሔደሐምሌ 17/2017 ዓ.ም*****************************በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ...
24/07/2025

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል የተገልጋይ ውይይት መድረክ ተካሔደ
ሐምሌ 17/2017 ዓ.ም
*****************************

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2017 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ ዓመት የተገልጋይ ውይይት መድረክ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኤርሚያስ ሞሊቶ፣ የን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው፣ የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ተወካይ አቶ ሚሻሞ ወርቅነህ፣ የሆስፒታሉ ማኔጅመንት አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው ተሳታፊዎች በተገኙበት ተካሒዷል።

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ኤርሚያስ ሞሊቶ በውይይት መድረኩ እንደገለጹት፦
በሆስፒታሉ የመጣው ለውጥ ትልቅ መሆኑን በማንሳት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የመጣውን አስደሳች ለውጥ በይበልጥ መቀጠል እንዲቺል የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

አክለውም በውይይቱ የተነሱ ሀሳቦችን የሆስፒታሉ ማኔጅመንት በመውሰድ የአገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተና የተገልጋይ እርካታን ከመጨመር ጋር ተያይዞ የተነሱ ሀሳቦችን ትኩረት ተሰጥቶበት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው በመልዕክታቸው እንደገለጹት፦

ሆስፒታሉን ለማዘመን በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ገልጸው በአሁኑ ሰዓት ከወረቀት ነጻ የሆነ የህክምና አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
አክለውም ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተሩ እንደገለጹት፦ አሁን የተመለከትነውን አመርቂ ለውጥ በቀጣይም በጋራ ጠንክረን በመስራት ማስቀጠል ይኖርብናልም ሲሉ ተናግረዋል።

የህክምና ስራ ሒደት አስተባባሪ እና የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ተወካይ የሆኑት አቶ ሚሻሞ ወርቅነህ እንደገለጹት በሆስፒታል ውስጥ የታየው ከፍተኛ መነቃቃት ሳያቋርጥ መቀጠል እንዳለበት ገልጸው ሆስፒታሉ በሚሰጠው አገልግሎት ዞኑ በጋራና በአብሮነት እንደሚሰራም ጠቁመዋል።

በአገልግሎት አሰጣጥ ዙርያ በርካታ ለውጦች እየመጡ እንዳሉ በማንሳት ህዝቡ ሳይጉላላ መድሃኒቶች እና የህክምና አገልግሎቶችን ከሆስፒታሉ እንዲያገኙ በማድረግ ትልቅ ለውጥ እየተመለከቱ ያሉበት ሁኔታ እንዳለ የውይይቱ ተሳታፊዎች ጠቅሰው በቀጣይም መሻሻል ያለባቸው ስራዎች ሲኖሩ ሆስፒታሉ ፈጣን ምላሽ መስጠት እንዳለበትም አሳስበዋል።

ሐምሌ 17/2017 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል ህዝብ ግንኙነት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!

23/07/2025

ፎረንሲክ ሜድስን በንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መሠጠት ተጀመረ
ሀምሌ 16/2017 ዓ.ም

ፎረንሲክ ሜድስን በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መስጠት የተጀመረ ሲሆን በሆሳናና አጎራባች ዞኖች ለሚገኙ ማህበረሰብ አባላት እፎይታን ይፈጥራልም ተብሏል

የንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው እንደተናገሩት ፎረንሲክ ሜድስን ከሚሰጣቸው በርካታ አገልግሎቶች አንዱ የአስክሬን ምርመራ ሲሆን ከዚህ ቀደም ለአስክሬን ምርመራ አዲስ አበባ እና ወራቤ ኮ/ስ/ሆስፒታል ድረስ ይኬድ እንደነበረ ገልጸው በአሁኑ ሰአት ይህ ምርመራ እዚ መጀመሩ በሆሳናና አጎራባች ዞኖች ውስጥ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍል እፎይታን ይፈጥራል ብለዋል።

በመጨረሻም የፎረንሲክ ሜድስን እና ቶክሲኮሎጂ እስፔሻሊስት የሆኑት ዶ/ር አቤኔዘር ሄራሞ የሚከተለውን ሀሳብ አስተላልፈዋል።

ሀምሌ 16/2017 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል ህዝብ ግንኙነት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!

White-coat day celebration of Clinical year one (C-I) Medical students of Wachemo University College of Medicine and Hea...
22/07/2025

White-coat day celebration of Clinical year one (C-I) Medical students of Wachemo University College of Medicine and Health Sciences, 2025

The White coat ceremony is a well known culture among medical students; it is a powerful tradition that celebrates the beginning of a lifelong journey in healthcare.

It reminds students of their purpose, their potential and the importance of compassion in their practice. So when they celebrate this little achievement it is crucial for students for several reasons.

The ceremony serves to welcome students to healthcare practice and emphasizes the core value of humanism in medicine.

July 22/2025
Wachemo University, Nigist Eleni Mohammed Memorial Comprehensive Specialized Hospital !!
Let Your light shine in the Society!!

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ 2017 ዓ.ም የሆስፒታሉን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ገመገመ!******************************የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ...
20/07/2025

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ 2017 ዓ.ም የሆስፒታሉን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ገመገመ!
******************************

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ የ2017 ዓ.ም የሆስፒታሉን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ገምግሞ በማፅደቅ በቀጣይ የታቀዱ እቅዶች ላይ ሰፊ ውይይት አካሂዷል።

ቦርዱ በ2017 ዓ.ም የታዩ መልካም እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው በማንሳት አዳዲስ በሆስፒታሉ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችንም በቅርበት ለመከታተል እና በባለቤትነት ለመፈጸም አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።
በመጨረሻም ቦርዱ ሆስፒታል ውስጥ ያለውን የተለያዩ ተግባራት በመጎብኘት ተጠናቋል።

ሀምሌ 12/2017 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል ህዝብ ግንኙነት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!

Address

Hossana
42528

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nigist Eleni Hospital-WCU posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Category