Nigist Eleni Hospital-WCU

Nigist Eleni Hospital-WCU Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Nigist Eleni Hospital-WCU, Hospital, Hossana.

Nigist Eleni Mohammed Memorial Comprehensive Specialized Hospital is Wachemo University's Medicine and Health Science College Hospital with almost all the specialities

27/03/2026

በሆስፒታላችን ከአንዲት ታካሚ ክብደቱ ከ13 ኪሎግራም የሚበልጥ ኦቫሪያን ካንሰር ( Ovarian cancer ) በቀዶ ህክምና ተወገደ።መጋቢት 18/2018 ዓ/ም********//**********...
27/03/2026

በሆስፒታላችን ከአንዲት ታካሚ ክብደቱ ከ13 ኪሎግራም የሚበልጥ ኦቫሪያን ካንሰር ( Ovarian cancer ) በቀዶ ህክምና ተወገደ።
መጋቢት 18/2018 ዓ/ም
********//**********

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከአንዲት ታካሚ ክብደቱ 13 ኪሎግራም በላይ የሚመዝን ኦቫሪያን ካንሰር ( Ovarian Cancer ) በዛሬው እለት በቀዶ ህክምና ሊወገድ ችሏል።

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የማህጸንና ጽንስ ስፔሻሊስት ሀኪም ዶ/ር በየነ አበራ በንግግራቸው እንደገለጹት ፣ ኦቫሪያን ካንሰር ( Ovarian Cancer )ወይንም የእንቁላል ማምረቻ ካንሰር በሴቶች የመራቢያ አካል በተለይም እንቁላል በሚያመርቱት የሴት የዘር ፍሬዎች ላይ የሚከሰት የካንሰር አይነት ሲሆን ታካሚዎቹንም ለከፍተኛ ህመም የሚዳርግ ነው ብለዋል።

አክለውም ዶ/ር በየነ እንደተናገሩት ታካሚዋ በስራ ምክንያት ዱባይ በነበረችበት ወቅት ህክምናዋን እየተከታተለች ቢሆንም ህመሙ ሲበረታባት ወደ ሀገር-ቤት መመለሷን በመግለጽ በሆስፒታላችን በተደረገላት ክትትል ካንሰሩ በቀዶ-ህክምና ሊወገድ ችሏል ብለዋል።

መጋቢት 18/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከሰኞ እስከ እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!

21/03/2026
19/03/2026

እንኳን ለ1ሺ 447ኛዉ ዒድ አልፈጥር በዓል በሠላም
አደረሳችሁ! አደረሰን!

የ1ሺ 447ኛዉ ዒድ አልፈጥር በዓል ምክንያት በማድረግ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዳዊት ሃዬሶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፥ እንኳን ለ1ሺ 447ኛዉ ዒድ አልፈጥር በዓል በሠላም አደረሳችሁ! አደረሰን ሲሉ መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

በመልዕክታቸውም ሕዝበ ሙስሊሙ በረመዳኑ ወር ሲያዘወትራቸዉ የነበሩ የአብሮነት፣ የመደጋገፍ፣ የመጠያየቅና መተባባር ተግባራትን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደምያስፈልግም አመልክተዋል።

በዓሉ የደስታ፣ የጤናና የፍቅር እንዲሆን እመኛለሁ!

ዒድ ሙባረክ!

አመሠግናለሁ!

ዶ/ር ዳዊት ሃዬሶ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት
ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ

መጋቢት 10/2018 ዓ.ም

ደም በመለገስ ህይወት እናድን በሚል መሪ-ቃል በሆስፒታላችን የደም ልገሳ መርሀግብር ተካሔደ መጋቢት 9/2018 ዓ.ም********//********በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰ...
18/03/2026

ደም በመለገስ ህይወት እናድን በሚል መሪ-ቃል በሆስፒታላችን የደም ልገሳ መርሀግብር ተካሔደ
መጋቢት 9/2018 ዓ.ም
********//********

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ደም በመለገስ ህይወት እናድን በሚል መሪ-ቃል የደም ልገሳ ዘመቻ ለተከታታይ ሁለት ቀናት የተካሔደ ሲሆን ከ 125 ዩኒት ደም በላይም ለመሰብሰብ ተችሏል ።

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው በንግግራቸው እንዳሉት፦ ደም መለገስ የህይወት ትልቁ ስጦታ መሆኑን በማንሳት ዛሬ በሆስፒታሉ የሚገኙ ሰራተኞች እና ተማሪዎች በራሳቸው ተነሳሽነት ደም መለገሳቸውን አድንቀዋል።
አክለውም ዶክተር ይድነቃቸው እንደገለጹት ታካሚዎች ደም በሚያስፈልጋቸው ወቅት ሳይቸገሩ ደም ማግኘት እንዲችሉ ደም የመለገስ ባህላችንን ከፍ ልናደርግ ይገባል ብለዋል።

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል የጤና ት/ት እና አገልግሎት ኮርፖሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ተክሌ እጃጆ እንደገለጹት ደም መለገስ ከስጦታዎች ሁሉ ትልቁ ስጦታ መሆኑን በማስታወስ የሆስፒታላችን ሰራተኞች እና ተማሪዎች በተነሳሽነት ደም መለገሳቸው ደም ለሚያስፈልጋቸው ተካሚዎች ያለው ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነው ብለዋል።

መጋቢት 9/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከ ሰኞ-እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!

በሆስፒታላችን ለሚሰሩ ሙስሊም የህክምና ባለሞያዎች  የኢፍጣር መርሀግብር ተካሔደ!!መጋቢት 3/2018 ዓ/ም************//***********በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታ...
12/03/2026

በሆስፒታላችን ለሚሰሩ ሙስሊም የህክምና ባለሞያዎች የኢፍጣር መርሀግብር ተካሔደ!!
መጋቢት 3/2018 ዓ/ም
************//***********

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለሚሰሩ ሙስሊም የህክምና ባለሞያዎች የኢፍጣር መርሀግብር ተካሒዷል።

በእለቱም የተገኙት የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል የህክምና ትምህርትና አገልግሎት ኮርፖሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ተክሌ እጃጆ በንግግራቸው እንደገለጹት የዛሬውን የኢፍጣር መርሀግብር ከሙስሊም እህትና ወንድሞቻችን ጋር በጋራ ማሳለፋችን ትልቅ ደስታን ይፈጥርልናል በማለት ፕሮግራሙ የጋራ እሴቶቻችንን አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚኖረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል።

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል የህክምና አገልግሎቶች ም/ኮርፖሬት ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር እንዳለ ፍቅሬ እንዳሉት የዛሬው የጋራ የኢፍጣር ፕሮግራም መከባበርን ፣ አንድነትን እና የጠበቀ የእርስ በእርስ መዋደድን የሚያሳይ በመሆኑ በሁላችንም ዘንድ ባህል ሆኖ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።

መጋቢት 3/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከ ሰኞ-እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!

06/03/2026



የካቲት 27/2018 ዓ/ም

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከአሜሪካኑ Cure blindness ከሚባል ግብረ-ሰናይ ድርጅት ጋር በጋራ በመተባበር ከመጋቢት 21-25/2018 ዓ.ም የአይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና በነጻ የሚረጥ ስለሆነ ከ የካቲት 20/2018 ዓ.ም ጀምሮ በሆስፒታላችን እና በአቅራቢያችሁ ባሉ ጤና ተቋማት ቅድመ-ምርመራ እየተደረገ መሆኑን እየገለጽን ለታካሚዎች ትራንስፖርት፣ ምግብ፣ ማደሪያ እና ህክምና በነጻ መሆኑንም እናሳስባለን።

በመቀጠልም በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል የአይን ህክምና ዲፖርትመንት ሀላፊ የሆኑት ዶ/ር አፍራኖ ሱሚቻ የሚከተለውን መልዕክት አስተላልፈዋል።

የካቲት 27/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከ ሰኞ-እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!

በሆስፒታላችን የአንድ ማዕከል የጡት እና የማህፀን ጫፍ ካንሰር ህክምና አገልግሎትን ለማስጀመር ከስምምነት ተደረሰ!!የካቲት 24/2018 ዓ/ም*********//*********የጀርመኑ ማርቲን ...
03/03/2026

በሆስፒታላችን የአንድ ማዕከል የጡት እና የማህፀን ጫፍ ካንሰር ህክምና አገልግሎትን ለማስጀመር ከስምምነት ተደረሰ!!
የካቲት 24/2018 ዓ/ም
*********//*********

የጀርመኑ ማርቲን ሉተር ዩኒቨርሲቲ ከ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ በመሆን ያስጀመሩት የ EKC ፕሮጀክት በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንድ ማዕከል የጡትና የማህፀን ጫፍ ካንሰር ህክምና አገልግሎትን ለማስጀመር ከስምምነት ደርሷል።

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው እንደተናገሩት፦ የጡትና የማህፀን ጫፍ ካንሰር በጊዜ ከታወቁ ታክመው ሊድኑ የሚችሉ የካንሰር አይነቶች መሆናቸውን በመጥቀስ ይህ ፕሮጀክት የጡትና የማህፀን ጫፍ ከንሰርን አስቀድሞ በመመርመር፣ የበሽታ ልየታ በማድረግና በሽታውን በማከም ለሴት እህቶቻችን የሚኖረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል።

አክለውም ዶክተር ይድነቃቸው እንደገለጹት ከዚህ ቀደም በሆስፒታሉ ህክምናው የተጀመረ ቢሆንም ለታካሚዎች የተሟላ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት የዚህ ፕሮጀክት መምጣት ከፍተኛ አቅም እንደሚጨምርም አብራርተዋል።

የ EKC ፕሮጀክት አስተባባሪ የሆኑት አቶ አቤል ሽታ በበኩላቸው እንደገለጹት፦ ይህ ፕሮጀክት በዋናነት በሴቶች ካንሰር ላይ እንደሚሰራ በመጥቀስ በአከባቢው ለሚገኙ ሴቶች ትልቅ እፎይታን ይፈጥራል ብለዋል።
አክለውም አቶ አቤል እንደተናገሩት በአብዛኛው በካንሰር የተጠቁ ታካሚዎች ወደ ጤና ተቋማት የሚሔዱት ዘግይተው እንደሆነ በማስታወስ ይህ ፕሮጀክት መጀመሩ ሴቶች በቶሎ የቅድመ-ካንሰር ምርመራና ህክምና እንዲያገኙ ይረዳቸዋል ብለዋል።

የካቲት 24/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከ ሰኞ-እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!

28/02/2026

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እየተሰጠ የሚገኘው ምቹ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሆስፒታሉን ይበልጥ ለማዘመን የሚኖረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ!!
የካቲት 21/2018 ዓ.ም
ዘገባው የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ነው።

27/02/2026
በድህረ-ወሊድ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ዙሪያ ለባለሞያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል!!የካቲት 20/2018 ዓ.ም*********//**********Engender Health ...
27/02/2026

በድህረ-ወሊድ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ዙሪያ ለባለሞያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል!!
የካቲት 20/2018 ዓ.ም
*********//**********

Engender Health ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ እና ከን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ ሆስፒታል ጋር በጋራ በመተባበር በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከተለያዩ ዲፓርትመንቶች ለተወጣጡ የጤና ባለሞያዎች እና በሆስፒታሉ እየተማሩ ለሚገኙ የማህፀንና ጽንስ ስፔሻሊቲ ሬዚደንት ሀኪሞች በድህረ-ወሊድ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ዙሪያ ለተከታታይ 5 ቀናት የሚቆይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል የተከታታይ ሙያ ማጎልበቻና ስልጠና አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ዓለሙ ኤርሲዶ እንደተናገሩት ከወሊድ በሗላ እናቶች የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት መጠቀማቸው ያልተፈለገ እርግዝናን ለመከላከል ጠቀሜታው ከፍ ያለ ነው ብለዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ Engender Health ሪጅናል ኮርድኔተር የሆኑት አቶ ሀያቱ መሃመድ በንግግራቸው እንዳሉት፦ እናቶች ከወለዱ በሗላ የሚሰጥ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ማስፋት አስፈላጊ እንደሆነ በመጥቀስ ከአላስፈላጊ እርግዝና ጋር ተያይዞ የሚመጣ የጨቅላ ህጻናት ሞትን ለመቀነስም የቤተሰብ እቅድ አገልግሎቱ ወሳኝ ነው ብለዋል።

አክለውም አቶ ሀያቱ መሃመድ እንዳሉት በንግስት እሌኒ ሆስፒታል የሚወልዱ እናቶች በርካታ መሆናቸውን ተከትሎ ይህ አይነቱ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በተቋሙ ለሚወልዱ እናቶች የሚኖረው ጠቀሜታ ትልቅ ነው ብለዋል።

የካቲት 20/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከ ሰኞ-እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!

Address

Hossana
42528

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nigist Eleni Hospital-WCU posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category