27/02/2026
በድህረ-ወሊድ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ዙሪያ ለባለሞያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል!!
የካቲት 20/2018 ዓ.ም
*********//**********
Engender Health ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ እና ከን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ ሆስፒታል ጋር በጋራ በመተባበር በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከተለያዩ ዲፓርትመንቶች ለተወጣጡ የጤና ባለሞያዎች እና በሆስፒታሉ እየተማሩ ለሚገኙ የማህፀንና ጽንስ ስፔሻሊቲ ሬዚደንት ሀኪሞች በድህረ-ወሊድ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ዙሪያ ለተከታታይ 5 ቀናት የሚቆይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል የጤና ባለሞያዎች የተከታታይ የጤና ማጎልበቻ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ዓለሙ ኤርሲዶ እንደተናገሩት ከወሊድ በሗላ እናቶች የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት መጠቀማቸው ያልተፈለገ እርግዝናን ለመከላከል ጠቀሜታው ከፍ ያለ ነው ብለዋል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ Engender Health ሪጅናል ኮርድኔተር የሆኑት አቶ ሀያቱ መሃመድ በንግግራቸው እንዳሉት፦ እናቶች ከወለዱ በሗላ የሚሰጥ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ማስፋት አስፈላጊ እንደሆነ በመጥቀስ ከአላስፈላጊ እርግዝና ጋር ተያይዞ የሚመጣ የጨቅላ ህጻናት ሞትን ለመቀነስም የቤተሰብ እቅድ አገልግሎቱ ወሳኝ ነው ብለዋል።
አክለውም አቶ አያቱ መሃመድ እንዳሉት በንግስት እሌኒ ሆስፒታል የሚወልዱ እናቶች በርካታ መሆናቸውን ተከትሎ ይህ አይነቱ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና የሚኖረው ጠቀሜታ ትልቅ ነው ብለዋል።
የካቲት 20/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከ ሰኞ-እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!