Nigist Eleni Hospital-WCU

Nigist Eleni Hospital-WCU Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Nigist Eleni Hospital-WCU, Hospital, Hossana.

Nigist Eleni Mohammed Memorial Comprehensive Specialized Hospital is Wachemo University's Medicine and Health Science College Hospital with almost all the specialities

በድህረ-ወሊድ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ዙሪያ ለባለሞያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል!!የካቲት 20/2018 ዓ.ም*********//**********Engender Health ...
27/02/2026

በድህረ-ወሊድ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ዙሪያ ለባለሞያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል!!
የካቲት 20/2018 ዓ.ም
*********//**********

Engender Health ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ እና ከን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ ሆስፒታል ጋር በጋራ በመተባበር በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከተለያዩ ዲፓርትመንቶች ለተወጣጡ የጤና ባለሞያዎች እና በሆስፒታሉ እየተማሩ ለሚገኙ የማህፀንና ጽንስ ስፔሻሊቲ ሬዚደንት ሀኪሞች በድህረ-ወሊድ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ዙሪያ ለተከታታይ 5 ቀናት የሚቆይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል የጤና ባለሞያዎች የተከታታይ የጤና ማጎልበቻ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ዓለሙ ኤርሲዶ እንደተናገሩት ከወሊድ በሗላ እናቶች የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት መጠቀማቸው ያልተፈለገ እርግዝናን ለመከላከል ጠቀሜታው ከፍ ያለ ነው ብለዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ Engender Health ሪጅናል ኮርድኔተር የሆኑት አቶ ሀያቱ መሃመድ በንግግራቸው እንዳሉት፦ እናቶች ከወለዱ በሗላ የሚሰጥ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ማስፋት አስፈላጊ እንደሆነ በመጥቀስ ከአላስፈላጊ እርግዝና ጋር ተያይዞ የሚመጣ የጨቅላ ህጻናት ሞትን ለመቀነስም የቤተሰብ እቅድ አገልግሎቱ ወሳኝ ነው ብለዋል።

አክለውም አቶ አያቱ መሃመድ እንዳሉት በንግስት እሌኒ ሆስፒታል የሚወልዱ እናቶች በርካታ መሆናቸውን ተከትሎ ይህ አይነቱ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና የሚኖረው ጠቀሜታ ትልቅ ነው ብለዋል።

የካቲት 20/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከ ሰኞ-እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!

24/02/2026

አስቸኳይ ማስታወቂያ!

የ2018 ዓ.ም አጋማሽ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ተፈታኞች በሙሉ!

የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና (Exit Exam) የካቲት 17/2018 ዓ/ም መሰጠት መጀመሩ ይታወቃል፡፡

ሆኖም ባልታሰበ የኃይል መቆራረጥ ችግር በዳታ ማዕከል ላይ በማጋጠሙ ችግሩን በመፍታት እንደገና ለማስጀመር ጥረት የተደረገ ቢሆንም የፕሮግራም መዛባትን በማስከተሉ የፈተናውን ሙሉ ፕሮግራም በአንድ ቀን ማሸጋሸግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

ስለሆነም ሁሉም ፕሮግራሞች የዛሬን ጨምሮ ባሉበት ክፍለ ጊዜ ላይ ሆነው በተዋረድ በአንድ ቀን የተሸጋሸጉ መሆኑ ታውቆ ለሁሉም ተፈታኞች መረጃው እንዲደርሳቸው እንዲደረግ እያሳሰብን ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡

#ማስታወሻ፡- ዛሬ ፈተና ጀምረው የነበሩ ተፈታኞች እንደሙከራ ፈተና (Moc Exam) በመውሰድ ነገ በተመሳሳይ ሰዓት እንደገና የሚፈተኑ ይሆናል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት!

24/02/2026
Human Bridge የተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት በሆስፒታላችን የህክምና አገልግሎተና የመማር ማስተማር ስራን መደገፍ የሚያስችል የጋራ ስምምነት አኖረ!!የካቲት 16/2018 ዓ.ም********/...
23/02/2026

Human Bridge የተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት በሆስፒታላችን የህክምና አገልግሎተና የመማር ማስተማር ስራን መደገፍ የሚያስችል የጋራ ስምምነት አኖረ!!
የካቲት 16/2018 ዓ.ም
********//********
Human Bridge የተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሚሰጡ የህክምና አገልግሎቶችን እና መማር ማስተማሩን ለመደገፍ የጋራ ስምምነት ላይ ደርሷል።

በእለቱም የተገኙት የ Human Bridge Regional Director ዶ/ር አዳሙ አንለይ እንደተናገሩት በሆስፒታሉ የሚሰጡ የህክምናና የመማር ማስተማር ስራውን ይበልጥ ለማዘመን በጋራ መስራት ከፍ ያለ ውጤት እንደሚኖረው በመጥቀስ ሆስፒታሉን የሚጠቅሙ መሠል ድጋፎችም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል።

Diplomatic previleges and Immunity Directorate Director የሆኑት ዳኛ በላቸው አንሺሶ በንግግራቸው እንደገለጹት፦ Human Bridge ላለፉት አያሌ አመታት በርካታ የጤና ተቋማትን ለማዘመን ድጋፍ እያደረገ የሚገኝ ግብረሰናይ ድርጅት መሆኑን በማስታወስ እንደነዚህ ካሉ ስመ-ጥር ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት ለማህበረሰቡ የሚሰጠው ጠቀሜታ ላቅ ያለ እንደሚሆን አሳስበዋል።

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው እንደገለጹት፦ ይህ የጋራ ስምምነት ለሆስፒታሉ ብሎም ለህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጁ የሚኖረው ፋይዳ ትልቅ መሆኑን በመጥቀስ ጥራቱ ከፍ ያለ የህክምና አገልግሎትና መማር ማስተማር ሲኖር ለህብረተሰቡ ያለው ጠቀሜታም ከፍ እንደሚል ተናግረዋል።

የሀዲያ ዞን ጤና መምሪያ ሀላፊ የሆኑት ዶ/ር ደሳለኝ ሽጉጤ እንደተናገሩት በንግስት እሌኒ ሆስፒታል የሚታከሙ ታካሚዎች በርካታ መሆናቸውን ተከትሎ ይህ አይነቱ የጋራ ስምምነት ታካሚዎች ጥራት ያለው ህክምናን እንዲያገኙ ይረዳቸዋል ብለዋል።

የካቲት 16/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከ ሰኞ-እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!

ACSIS ከተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት ለሆስፒታላችን የእውቅና ሰርተፊኬት ተበረከተየካቲት 14/2018 ዓ.ም*******//*********ACSIS ( Healthcare System Impact Syn...
21/02/2026

ACSIS ከተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት ለሆስፒታላችን የእውቅና ሰርተፊኬት ተበረከተ
የካቲት 14/2018 ዓ.ም
*******//*********
ACSIS ( Healthcare System Impact Syndicate Africa ) የተሰኘ ሀገር-በቀል ግብረሰናይ ድርጅት የእናቶችና ጨቅላ ህጻናትን ሞት ለመቀነስ በሀዲያ ዞን እና አጎራባች ለሚገኙ ጤና ጣቢያዎች በድንገተኛ ቀዶ-ህክምና የማዋለድ አገልግሎትን ለማስጀመር ጠቅላላ ሀኪሞችን በ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለተከታታይ 3 ወራት በድንገተኛ ቀዶ ህክምና ማዋለድ እና በአልትራሳውንድ አገልግሎት በማሰልጠኑ ለሆስፒታላችን የእውቅና ሰርተፊኬት አበርክቷል።

የካቲት 14/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከ ሰኞ-እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!

19/02/2026

#ይነበብ

 #ማስታወቂያ  #ይነበብ
16/02/2026

#ማስታወቂያ #ይነበብ

የወባ በሽታ ስርጭትን መከላከልና መቆጣጠር የሚያስችሉ ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶባቸው እየተሰሩ ይገኛሉ '' ዶ/ር እንዳለ ፍቅሬ''*****//******የካቲት 2/2018 ዓ.ምበዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ...
09/02/2026

የወባ በሽታ ስርጭትን መከላከልና መቆጣጠር የሚያስችሉ ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶባቸው እየተሰሩ ይገኛሉ '' ዶ/ር እንዳለ ፍቅሬ''
*****//******
የካቲት 2/2018 ዓ.ም

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የወባ በሽታ ስርጭትን መከላከልና መቆጣጠር የሚያስችሉ ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶባቸው እየተሰሩ እንደሚገኙ የሆስፒታሉ ቺፍ ክሊኒካል ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር እንዳለ ፍቅሬ ተናግረዋል።

ዶ/ር እንዳለ ፍቅሬ እንዳሉት የሆስፒታሉ ዋነኛ አላማ በአከባቢው ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች በሚከሰቱበት ጊዜ ፈጣን አገልግሎት በመስጠት የማህበረሰቡን ጤና ማስጠበቅ ሲሆን ህብረተሰቡም የወባ በሽታ ስርጭትን ለመቀነስ የአልጋ አጎበርን በአግባቡ በመጠቀም፣ ውሀ ያቆሩ ቦታዎችን በማጽዳትና የአከባቢውን ንጽህናን በመጠበቅ የወባ በሽታ ስርጭትን ለመከላከል የበኩሉን አስተዋጽኦ ማድረግ እንደሚገባ በማስታወስ የትኛውም ግለሰብ የህመም ስሜት ሲሰማው ወደ ሆስፒታላችን መጥቶ በመታከም ለጤና አስጊ የሆነውን የወባ በሽታ አስቀድሞ በመከላከል ጤናውን መጠበቅ እንዳለበትም አሳስበዋል።

የካቲት 2/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከ ሰኞ-እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!

 *****//******የካቲት 1/2018 ዓ.ምየሆስፒታላችን ጠቅላላ ሐኪም እና ሌክቸረር የነበሩት ዶ/ር ደስታ አበበ በደረሰባቸው ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን በንግስት እ...
08/02/2026


*****//******
የካቲት 1/2018 ዓ.ም

የሆስፒታላችን ጠቅላላ ሐኪም እና ሌክቸረር የነበሩት ዶ/ር ደስታ አበበ በደረሰባቸው ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን በንግስት እሌኒ ሆስፒታል ማህበረሰብ ስም እየገለጽን ለመላው የስራ ባልደረቦቻቸው፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ተማሪዎቻቸው ልባዊ መጽናናትን እንመኛለን!!

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ሆስፒታል

Address

Hossana
42528

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nigist Eleni Hospital-WCU posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Category