የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ Aari Zone Health Department ትክክለኛው ገጽ

  • Home
  • Ethiopia
  • Jinka
  • የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ Aari Zone Health Department ትክክለኛው ገጽ

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ Aari Zone Health Department ትክክለኛው ገጽ የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና በሚል መሪህ የጤና ሥርዓቱን አጠናክሮ ማስቀጠል

19/09/2025

በእርግዝና ወቅት የሚደረግ ክትትልና እንክብካቤ ለእናትም ሆነ ለልጅ ጤና ወሳኝ ነው!

Hordoffii fi kunuunsi waqtii ulfaa taasifamu fayyaa haadhaafis ta'e kan daa'imaaf murteessaadha!



Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ የተቀናጀ ውይይት ማድረጉን አስተወቀጂንካ_መስከረም 9/2018 ዓ.ም (ኣዞጤመ)  የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ሣምንታዊ PHEOC wk37/2025  እና የቀጣይ ለሎቾ ተግባራ...
19/09/2025

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ የተቀናጀ ውይይት ማድረጉን አስተወቀ
ጂንካ_መስከረም 9/2018 ዓ.ም (ኣዞጤመ)

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ሣምንታዊ PHEOC wk37/2025 እና የቀጣይ ለሎቾ ተግባራትን በማቀናጀት ተገምግሟል ።

የግምገማ መድረኩ ላይ በስፍት የወባ ወረርሽኝ ያለበት ደረጃ የተገመገመ ሲሆን 1667 የወባ ታማሚዎች ህክምና ያገኙ ሲሆን ከባለፈው ሳምንት አንጻር ሲታይ በ230 (14%) ቀነሷል። ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ሳምንት አንጻር 686(70%) ጭማሪ ተመዝግቧል ይህም ከአምናው አንጻር ወረርሽኝ መሆኑን ያመለክታል ።

ለዝህም ከፍተኛ የወባ ጫና ያለባቸው
1,ጂንካ ከተማ 326(20%) ሲሆን የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል 631 (37%) በአጠቃላይ በጂንካ 957 ታማሚ ይገኝበታል
2, ደቡብ ኣሪ 353(21%) ሁለቱ ወረዳዎች 78% ሲሆን ቀሪ ወረዳዎች 22% ድርሻ አላቸው ።

ለሎችም የተከናወኑ ሪፖርቶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል ። ዝርዝር መረጃዎችን በቴሌግራም ገጻችን ይመልከቱ።👇

https://t.me/+9ChLwsFQYos1N2E0

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በድሉ ባጊማስ የማጠቃለያ ንግግር ወቅት የምከተሉትን መልዕክቶች አስተላልፈዋል።

የወባ በሽታን ለመከላከል የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንድቀጥሉ እና የተደለደሉት የአልጋ አጎበሮች በአስቸኳይ ለማህበረሰቡ በማሰራጨት ሪፖርት እንድደረግ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በቅንጅት እና በጋራ በመስራት ተግባራትን ከመራን ለውጥ እንድመጣ ትኩረት መስጠት ይገባናል በማለት መድረኩን አጠቃለዋል ።

በመድረኩም የመምሪያው ማኔጅመንት እና ባለሙያዎች በተነሱ አጀንዳዎች አሳብ አስተያየት ሰጥተውበታል ።

የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና !!
የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ

"መልካም ዜና" የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል SIGN FRACTURE CARE INTERNATIONAL ከሚባል ግብረ-ሰናይ ድርጅት ዋጋው ከ600,000 ብር በላይ የምተመን ለአጥንት ቀዶ ሕክምና የሚ...
18/09/2025

"መልካም ዜና" የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል SIGN FRACTURE CARE INTERNATIONAL ከሚባል ግብረ-ሰናይ ድርጅት ዋጋው ከ600,000 ብር በላይ የምተመን ለአጥንት ቀዶ ሕክምና የሚዉል የህክምና መሳሪያ ዛሬ መስከረም 08/2018ዓ. ም ድጋፍ ማግኘቱን ስያበስር የተሰማዉን ልባዊ ደስታ ይገልፃል::

ይህ የህክምና መሳሪያ ለረዥም አጥንት ስብራት መልሶ ጥገና የሚያገለግል ሲሆን በገበያ ላይ በቀላሉ ስለማይገኝ ከዚህ በፊት እንደ ሆስፒታል በጣም ስንቸገር የነበርንበትና የሞተርና የመኪና አደጋ ተጎጂ ተገልጋዮቻችን በእጥረቱ ምክንያት ለከፍተኛ እንግልት ሲዳረጉ ነበር::
አስቡት! የአጥንት ስብራት ኖሮት ሕክምናውን በቅርበት ማግኘት ሳይችል ቀርቶ ረዥምና ምቹ ያልሆነ መንገድ ከህመሙ ጋር መጓዝ ምን ያህል አሰቃቂ እንደሆነ መረዳት ይቻላል ።

ይህንን የተገልጋዮቻችን እንግልት ለመቅረፍ በሆስፒታሉ በኩል በተደረገ መልካም ግንኙነትና በልበ-ቀናው የኢትዮጵያ እንቁ ልጅ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የአጥንት ሕክምና ስፔሻሊቲ ትምህርት ክፍል ኃላፊ በሆኑት ፕሮፌሰር ብሩክ ላምብሶ(Professor of Orthopaedic Surgery at AAU) ቀና ትብብር የህዝባችን እንግልት ለማስቀረት ተችሏል::
ይህ የህክምና ዕቃ በቀላሉ የማይገኝና ዋጋው እጅግ ዉድ ከመሆኑ የተነሳ አንድ ታማሚ ከሌሎች ወጪዎች ዉጪ ለዕቃው ብቻ በአማካኝ ከ5000-7000ብር ያወጣል ይህም ለኛ ማህበረሰብ እጅግ ከባድ ነው::

ታዲያስ! እንግዲህ ከነገ ማለትም ከቀን 09/01/2018ዓ. ም ጀምሮ ከዚህ በፊት ለእቃው ስከፈል የነበረዉን ወጭ #በነፃ ሕክምና የሚሰጥ መሆኑን ስናበስር ልባዊ ደስታ ይሰማናል::
ሆስፒታላችን ይህንን መልካም ግንኙነት በማጠናከር በቅርብ ጊዜ ራሱን የቻለ የSIGN FRACTURE CARE PROGRAM የሚከፍት ይሆናል::

የህዝብ ልጅ ላበረከቱት ድጋፍ በማመስገን የዘገበው የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ነው።
የኣሪ ዞን ጤና መምሪያም ለሆስፒታሉ ስለተደረገው ድጋፍ የተሰማንን ደስታ በዞኑ ሕዝብ ስም እናመሠግናለን ።

የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ
ጂንካ
መስከረም 8/2018 ዓ.ም

በኢፌዴሪ የጤና ሚኒስትር ሚኒስቴር ዴኤታ ደረጄ ዱጉማ (ዶ/ር) የተመራ ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኣሪ ዞን የሥራ ጉብኝት አደረጉበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማህበራዊ ክላስተር በጂንካ ከተማ ...
17/09/2025

በኢፌዴሪ የጤና ሚኒስትር ሚኒስቴር ዴኤታ ደረጄ ዱጉማ (ዶ/ር) የተመራ ልዑክ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኣሪ ዞን የሥራ ጉብኝት አደረጉ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማህበራዊ ክላስተር በጂንካ ከተማ የሚገኙ የክልል ጤና ቢሮ የሥራ እንቅስቃሴ፣ የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል ኦክሲጂን ማዕከልና በክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የጂንካ ህብረተሰብ ላቦራቶሪ ማዕከል ግንባታ ሂደት ጎብኝተዋል።

በጤና ተቋማት ለዜጎች የሚሰጠውን የህክምና አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና ለማቀላጠፍ ትኩረት የሚያደርግ ሲሆን ጉብኝቱ በየአካባቢው ያሉ መልካም ተሞክሮዎችን ለማስቀጠልና ውስንነቶችን በማረም በኩል ከፈተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖር ተመልክቷል ።

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ
ጂንካ
መስከረም7/2018

15/09/2025
የአድራሻ ለውጥ ማስታወቂያ መስከረም 3/2018 ዓ.ምለክቡራን የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ተገልጋይ ደንበኞች በሙሉ የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ከዝህ ቀደም ስል ከነበረው ቢሮ በመውጣት ከመስከረም 5/...
13/09/2025

የአድራሻ ለውጥ ማስታወቂያ
መስከረም 3/2018 ዓ.ም

ለክቡራን የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ተገልጋይ ደንበኞች በሙሉ የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ከዝህ ቀደም ስል ከነበረው ቢሮ በመውጣት ከመስከረም 5/2018 ዓ.ም ጀምሮ በጂንካ ከተማ በ01 ጤናዳም ቀበሌ በሚገኘው የጂንካ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት ዋናው መግቢያ በር ላይ ጽድት ያለ ለሠራተኞች እና ለተገልጋዮች ምቹ የሆነ ቢሮ በመከራየት በዓዲሱ አመት ጥራት ያለውን አግልግሎት ለደንበኞች ለመስጠት በማሰብ የአድራሻ ለውጥ የተደረገ መሆኑን ደንበኞቻችን በማወቅ አግልግሎት ለማግኘት የሚችሉ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን ።

ይህ መልእክት ለሌሎች እንድደርስ በማጋራት የደንበኞቻችንን እንግልት ይቀንሱ!!

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ
ጂንካ

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በድሉ ባጊማስ 2018 ዓ/ም አዲስ ዓመትን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።ጳጉሜ 5/2017 ዓ.ም_ኣዞጤመ(ጂንካ) የመምሪያው ኃላፊ አቶ...
10/09/2025

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በድሉ ባጊማስ 2018 ዓ/ም አዲስ ዓመትን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።
ጳጉሜ 5/2017 ዓ.ም_ኣዞጤመ(ጂንካ)

የመምሪያው ኃላፊ አቶ በድሉ ባጊማስ አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የጤና፣ የብልጽግና፣ የመተሳሰብ፣ የመቻቻል፣ በሁሉም ዘርፍ ስኬትን የምናስመዘግብበት ዓመት እንዲሆን ለመላው ኢትዮጲያዊያን እና ለዞናችን ሕዝቦች እንዲሁም ለጤና ሴክተር ማህበረሰብ ተመኝተዋል፡፡

አያይዘውም በመልዕክታቸው የ2018 ዓ/ም አዲስ ዓመት ሀገራችንን በማንሰራራት ምዕራፍ ላይ በሚትገኝበትና ታላቁ የህዳሴ ግድብ በተመረቀበት ማግስት መከበሩ ልዩ እንደሚያደርገው አውስተው በለውጡ መንግሥት የጤና ልማት ተግባራት ለውጥ ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል፡፡

በአዲሱ ዓመት 2018 ዓ/ም በተለዩ በጤናው ሴክተር ችግሮች ላይ በሕዝቡና በጤና ባለሙያዎች በሚነሱ የመልካም አስተዳደርና አገልግሎት አሰጣጥ ጉድለት ላይ እንዲሁም በጤና ልማት ተሳትፎና ተደራሽነት፣ በጤና መድህን ሽፋንና ማነቆዎች ጠንካራ ሥራ ይሰራል ብለዋል፡፡

በጤናው ሴክተር የመጡ ለውጦችን በማፅናት፣ የታዩ ጉድለቶች በማረምና በህብረ ብሔራዊነት በመፈፀም ከአሁን የበለጠ እምርታዊ ለውጥ የሚመጣበት ዘመን እንዲሆን እንደሚሠራ በማብራራት መጪውን ዘመን ብሩህ ለማድረግ የጤናው ሴክተር አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት እንዲረባረቡ ጥሪያቸው አስተላልፈዋል፡፡

በድጋሚ አዲሱ ዓመታ የሠላም፣ የጤና፣ የእርስ በእርስ መረዳዳት ባህል የበለጠ የሚጎለብትበት፣ ሀገራችን ወደ ከፍታና ብልጽግና ማማ የምትሻገርበት፣ ህብረ ብሔራዊነት የሚያብብበት፣ የመቻቻል ዓመት እንዲሆን ከልብ ተመኝተዋል፡፡

መልካም አዲስ ዓመት!!

አቶ በድሉ ባጊማስ
የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ

04/09/2025

ጤና ሚኒስቴር፤ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች በሥራቸው በሚገኙ ጤና ተቋማት ውስጥ የሚሠሩ የሕክምና ባለሙያዎች እና ቤተሰቦቻቸው በነጻ ሕክምና የሚያገኙበትን "የሠራተኛ ክሊኒክ" እንዲያዘጋጁ መመሪያ አስተላለፈ።ሚኒስቴሩ፤ የጤና ተቋማት "ያላቸውን ተሽከርካሪ በመጠቀም" በሕክምና ባለሙያዎች የሥራ መግቢያ እና መውጫ ሰዓት የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲቀርብ መወሰኑንም አስታውቋል። 'የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች ንቅናቄ' ውሳኔዎቹን "እንደ ጥሩ ጅምር" ቢወስደውም፤ የቀረቡት ማሻሻያዎች ተፈጻሚ ሊሆኑ የሚችሉበትን አግባብ በተመለከተ ጥያቄ አንስቷል።

https://bbc.in/3Vle7Sz

በኣሪ ዞን በደቡብ ኣሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ወርልድ ቭዥን ኢትዮጵያ ለሚደግፋቸው የጤና ተቋማት የተገዙ መድኃኒቶች እና የህክምና ቁሳቁሶዎች ለተቋማቱ  ማስረጫቱን አስታውቋል ።ጂንካ_ነሐሴ 22/...
28/08/2025

በኣሪ ዞን በደቡብ ኣሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ወርልድ ቭዥን ኢትዮጵያ ለሚደግፋቸው የጤና ተቋማት የተገዙ መድኃኒቶች እና የህክምና ቁሳቁሶዎች ለተቋማቱ ማስረጫቱን አስታውቋል ።

ጂንካ_ነሐሴ 22/2017ዓ.ም(ኣዞጤመ)

በወርልድ ቭዥን ኢትዮጵያ የተገዙ መድኃኒቶች እና የህክምና ቁሳቁሶዎች በጤና ጣቢዎች ድልድል ተደርጓል።

መድኃኒቶች ፣ የCBC machine እና Microscope ለሽሽር ኮምፔረንስብ ጤና ኬላ ድልድል በተደረገው መሠረት ለጤና ኬላ ገቢ ተደርጓል።

የወርልድ ቭዥን ኢትዮጵያ ከፍተኛ ስነ_ምግብ ባለሙያ አቶ አለማየሁ ፍቅሩ እንደገለፁት ለሽሽር ኮምፔረንስብ ጤና ኬላ ብዙ የህክምና ቁሳቁስ እና ሳንተሽን ስራዎች በተጨማሪ የሚጎሉ ህክምና ቁሳቁሶዎችን በየጊዜው ለማሟላት እየተሰራ እንደሚገኙ አብራርተዋል።

በጌታመር ጤና ጣቢያ መድኃኒቶች እና የCBC machine በሌሎችም በጋዘር መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ፣ቢሊ ጤና ጣቢያ የመድኃኒት ድልድል ተደርጎ ተሰራጭቷል።

በተጨማሪ SC ተኝተው ለሚታከሙ ህፃናት ልዩ ልዩ የህክምና ቁሳቁስ ፣ የመጫወቻ እና አልጋ ፍራሾች እንዲሁም ሌሎች ፍራሾችን ለሁሉም ተሸንሽኖ ስርጭት ተደርጓል።

የወርልድ ቭዥን ኢትዮጵያ የስነ_ምግብ ባለሙያ አቶ አለማየሁ ፍቅሩ እና የደቡብ ኣሪ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የስነ_ምግብ ባለሙያ አቶ ዳዊት ባይስማይ ተገኝተዉ የግብዓትና የመድኃኒት ርክክብ አድርገዋል ስል የዘገበው የደቡብ ኣሪ ወረዳ መንግስት ኮምኒኬሽን ነው።

የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና !!
የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ

ልብ ሰባሪ ዜና!!በጌዴኦ ዞን ራጴ ወረዳ በደረሰ የመሬት ናዳ የ9 ሰው ህይወት አለፈ‎በጌዴኦ ዞን በራጴ ወረዳ በጫራቃ እና በሀሮ  ቀበሌ  ከምሽቱ 5: 00 ሠዓት አከባቢ  በደረሰ የመሬት ና...
28/08/2025

ልብ ሰባሪ ዜና!!

በጌዴኦ ዞን ራጴ ወረዳ በደረሰ የመሬት ናዳ የ9 ሰው ህይወት አለፈ

በጌዴኦ ዞን በራጴ ወረዳ በጫራቃ እና በሀሮ ቀበሌ ከምሽቱ 5: 00 ሠዓት አከባቢ በደረሰ የመሬት ናዳ የ9 ሰዎች ህይወት በማለፉ የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገለጿል፡፡

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ሀላፊ አቶ በድሉ ባጊማስ በሰው ህይወት በደረሰው የሞት አደጋ ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማቸው በመግለፅ ለሟች ቤተሰብ እና ወዳጅ ዘመድ መጽናናትን ተመኝተዋል ፡፡

ፈጣሪ የወገኖቻችንን ነፍስ ይማር !

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ በድንገተኛ እሳት አደጋ ውድመት ለገጠመው ለኦቶና ሆስፒታል 15,000 ብር በአካውታቸው ገቢ በማድረግ አጋርነታቸውን የገለፁ ሲሆን ከተባበርን መልሶ መገንባት እንችላለን...
27/08/2025

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ በድንገተኛ እሳት አደጋ ውድመት ለገጠመው ለኦቶና ሆስፒታል 15,000 ብር በአካውታቸው ገቢ በማድረግ አጋርነታቸውን የገለፁ ሲሆን ከተባበርን መልሶ መገንባት እንችላለን ።

የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና
የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ
ነሐሴ 21/2017 _ጂንካ

የወባ በሽታ ወረርሽኝን ለመቀነስ ብሎም ለማጥፋት ሁሉም አካላት በቅንጅት የመከላከል ሥራዎችን መሥራት ይገባቸዋል ።የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ
24/08/2025

የወባ በሽታ ወረርሽኝን ለመቀነስ ብሎም ለማጥፋት ሁሉም አካላት በቅንጅት የመከላከል ሥራዎችን መሥራት ይገባቸዋል ።

የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ

Address

South
Jinka

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ Aari Zone Health Department ትክክለኛው ገጽ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram