19/09/2025
የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ የተቀናጀ ውይይት ማድረጉን አስተወቀ
ጂንካ_መስከረም 9/2018 ዓ.ም (ኣዞጤመ)
የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ሣምንታዊ PHEOC wk37/2025 እና የቀጣይ ለሎቾ ተግባራትን በማቀናጀት ተገምግሟል ።
የግምገማ መድረኩ ላይ በስፍት የወባ ወረርሽኝ ያለበት ደረጃ የተገመገመ ሲሆን 1667 የወባ ታማሚዎች ህክምና ያገኙ ሲሆን ከባለፈው ሳምንት አንጻር ሲታይ በ230 (14%) ቀነሷል። ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ሳምንት አንጻር 686(70%) ጭማሪ ተመዝግቧል ይህም ከአምናው አንጻር ወረርሽኝ መሆኑን ያመለክታል ።
ለዝህም ከፍተኛ የወባ ጫና ያለባቸው
1,ጂንካ ከተማ 326(20%) ሲሆን የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል 631 (37%) በአጠቃላይ በጂንካ 957 ታማሚ ይገኝበታል
2, ደቡብ ኣሪ 353(21%) ሁለቱ ወረዳዎች 78% ሲሆን ቀሪ ወረዳዎች 22% ድርሻ አላቸው ።
ለሎችም የተከናወኑ ሪፖርቶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል ። ዝርዝር መረጃዎችን በቴሌግራም ገጻችን ይመልከቱ።👇
https://t.me/+9ChLwsFQYos1N2E0
የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በድሉ ባጊማስ የማጠቃለያ ንግግር ወቅት የምከተሉትን መልዕክቶች አስተላልፈዋል።
የወባ በሽታን ለመከላከል የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንድቀጥሉ እና የተደለደሉት የአልጋ አጎበሮች በአስቸኳይ ለማህበረሰቡ በማሰራጨት ሪፖርት እንድደረግ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በቅንጅት እና በጋራ በመስራት ተግባራትን ከመራን ለውጥ እንድመጣ ትኩረት መስጠት ይገባናል በማለት መድረኩን አጠቃለዋል ።
በመድረኩም የመምሪያው ማኔጅመንት እና ባለሙያዎች በተነሱ አጀንዳዎች አሳብ አስተያየት ሰጥተውበታል ።
የዜጎች ጤና ለሀገር ብልጽግና !!
የኣሪ ዞን ጤና መምሪያ