Qajeelcha Fayyaa G/S/Oromoo የኦሮሞ ዞኑ ጤና መምሪያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Kemise
  • Qajeelcha Fayyaa G/S/Oromoo የኦሮሞ ዞኑ ጤና መምሪያ

Qajeelcha Fayyaa G/S/Oromoo የኦሮሞ ዞኑ ጤና መምሪያ Oromo Health Department Health Education and Promotion Center, main objective is disseminating update health information for the community.

Oromo zone is one of special zone in amhara region. Its capita city is Kemisse which is found 325 KM from Addis Ababa. It has tow urban and five rural worda.

በከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታል ከ1ሺ በላይ ለሚጠጉ የህብረተሰብ ክፍሎች የአይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና አገልግሎት እየተሰጠ ነው።***በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ጤና መምሪያ እና ...
29/07/2025

በከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታል ከ1ሺ በላይ ለሚጠጉ የህብረተሰብ ክፍሎች የአይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና አገልግሎት እየተሰጠ ነው።
***
በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ጤና መምሪያ እና የከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታል ከቤተ አብርሃም ክሊኒክ ጋር በጋራ በመሆን የአይን ሞራ ግርዶሽ የቀዶ ህክምና አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

በከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታል ህክምና ሲያደርጉ ካገኘናቸው ታካሚዎች መካከል ወ/ሪት ዘሀራ መሀመድ የቃሉ ወረዳ ነዋሪ ስትሆን ከ12 አመት በላይ የአይን ብርሃኗ እንደማያይ ትናገራለች በዚህም የስነ ልቦና ችግር እንደደረሰባት ገልፃ በተደረገላት የአይን ቀዶ ህክምና የአይን ብርሃኗ ማየት በመቻሏ አዲስ ሂወትን አዲስ መወለድን እና አዲስ ብርሃንን ያየሁበት ቀን ነው ትላለች በዚህም በተደረገላት ህክምና መደሰቷንም ተናግራለች።

ሌሎች በሆስፒታሉ ነፃ የአይን ቀዶ ህክምና የተደረገላቸው ታካሚዎችም በተደረገላቸው ህክምና የአይን ብርሃናቸው እንደተመለሰላቸው ገልፀው በተደረገላቸው ህክምናም አመስግነዋል።

የከሚሴ ከተማ ጠቅላላ ሆስፒታል ስራአስኪያጅ አቶ ካሊድ ሙስጠፋ እንደተናገሩት ከዞን ጤና መምሪያና ረጅ ድርጅቶች ጋር በመሆን ከዚህ በፊት ማየት የማይችሉና እቤት የቀሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በመለየት አገልግሎት መስጠት መቻላቸውን ገልፀው ከ1ሺ በላይ የአይን ሞራ ግርዶሽ ያለባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች ለመስራት ህክምና እየተደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
በቀን ከ150 ሰዎች በላይ አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኝ የገለፁት ስራ አስኬጁ የተለያዩ ረጅ ድርጅቶች ጋር በመሆን ቀጣይነት እንዲኖረው ይሰራልም ነው ያሉት።

የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ጤና መምሪያ ተላላፊ በሽታዎችና መቆጣጠር ባለሙያ ወ/ሮ ነፊሳ አብዱ በበኩላቸው ከዞን ጤና ከከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታልና ከቤተ አብርሃም የአይን ክሊኒክ ጋር በጋራ በመሆን ለ6ኛ ጊዜ የአይን ብርሃን ግርዶሽ ያለባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች የአይን ብርሃናቸውን ለመመለስ ሰፊ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው 1200 የሚጠጉ ከተለያዩ አጎራባች ወረዳዎች የህብረተሰብ ክፍሎችን አገልግሎት እንደሚሰጥም ገልፀዋል።

የአውትሪቹ ኮርዲኔተር ሲስተር መሰረት ፋንታሁን እንደተናገሩት ቤተአብርሃም ክሊኒክ ከዞን ጤናና ከከሚሴ ጠቅላላ ሆስፒታል ጋር በመሆን የአይን ሞራ ግርዶሽ ላለባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ገልፀው ህብረተሰቡን ተደራሽ ለማድረግ ቀጣይነት እንዲኖረው ይሰራል ብለዋል በዚህም ለታካሚዎች ክትትል እንደሚደረግም ተናግረዋል።

28/07/2025
የዓይን ሞራ ግርዶሽ ችግር ላለባቸው ህሙማን የነፃ ቀዶ ህክምና አገልግሎት ዘመቻ በከሚሴ አጠቃላይ ሆስፒታል በዛሬው እለት ሀምሌ 21 መካሄድ መጀመሩን እና እስከ አርብ ሀምሌ 25/2017 እን...
28/07/2025

የዓይን ሞራ ግርዶሽ ችግር ላለባቸው ህሙማን የነፃ ቀዶ ህክምና አገልግሎት ዘመቻ በከሚሴ አጠቃላይ ሆስፒታል በዛሬው እለት ሀምሌ 21 መካሄድ መጀመሩን እና እስከ አርብ ሀምሌ 25/2017 እንደሚቀጥል ተገለፀ፦
***

የኦሮሞ ዞን ጤና መምሪያና የከሚሴ ሆስፒታል ከ HCP በጎ አድራጎት ከተሰኘ ድርጅት ጋር በመተባበር በአይን ሞራ ግርዶሽ ለሚቸገሩ በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደርና ከአጎራባች ዞኖች ለሚመጡ ለ5 ቀናት የሚቆይ የነፃ ቀዶ ህክምና (የዓይን ሞራ ግርዶሽ ገፈፋ) መሰጠት መጀመሩን ሲር ነፊሳ አብዱ በጤና መምሪያው የNCD ኦፊሰር ገልጸዋል፡፡

በዘመቻው በዋናነት በዞናችንና በዙሪያው በሚገኙ ዞኖች በስፋት እየተስተዋለ ያለውን የአይን ሞራ ግርዶሽ ችግር ለመግታት ታስቦ እየተሰራ መሆኑን እና ዘመቻውን ለማሳካት ላለፉት 30 ቀናት በሁሉም በዞኑ በሚገኙ ቀበሌዎች በተደረገው የቅስቀሳ ስራ ተለይተው የሚመጡ ከ1000 በላይ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ገፈፋ የሚደረግላቸው መኖራቸውን ሲር ነፊሳ ገልፀዋል።

ህክምናውን እየሰጡ ለሚገኙት የHCP ዓይን ህክምና ቡድንና የከሚሴ ሆስፒታል አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም በዞን ጤና ሴክተር በየደረጃው ለሚገኙ አመራርና ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

የዓይን ሞራ ግርዶሽ አብዛኛውን አምራች የሆነውን ዜጋ እይታ በመጋረድ ከተለያዩ የሕይወት እንቅስቃሴዎች ወደኋላ የሚያስቀር የጤና ችግር በመሆኑ ተጠቂ የሆኑ በአካባቢያችንና በዙሪያው ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ታካሚዎች በመኖራቸው በተናጠል ለመስራት አስቸጋሪ በመሆኑ በዘመቻ መልኩ እየተሰጠ መሆኑን አቶ ኡስማን አሊ የዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ገልጸዋል፡፡

የዓይን ሞራ ግርዶሽ አብዛኛዉን ጊዜ እድሜያቸው ከ50 በላይ የሆኑ ሰወች ላይ ሊከሰት እንደሚችል በችግሩ ዙሪያ የተደረጉ ጥናቶች ያመላክታሉ፡፡
በዚህ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ገፈፋ ቀዶ ህክም ዘመቻ ወደ 1000 ለሚሆኑ የሚሰራላቸው መሆኑና በመጀመሪያው ቀንም ከ250 በላይ ታካሚዎች ቀዶ ህክምና የተሰራላቸው ሲሆን በቀጣይ 4 ቀናትን ቀሪ ታካሚዎች ህክምናውን የሚያገኙ መሆኑን እንዲሁም ሌሎች የዐይን ሞራ ግርዶሽ ተጠቂ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል።

ሀምሌ 21/2017 ዓም/ከሚሴ
ኦዞጤመ/ህ/ግ

በጤና ዘርፍ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በሁሉም ደረጃ በእቅድ ተይዞ እየተተገበረ መሆኑን ተገለጸ፦*****የኦሮሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ኡስማን አሊና ም/ኃላፊ አንሻ መሀመድ በዘንደ...
28/07/2025

በጤና ዘርፍ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በሁሉም ደረጃ በእቅድ ተይዞ እየተተገበረ መሆኑን ተገለጸ፦
*****

የኦሮሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ኡስማን አሊና ም/ኃላፊ አንሻ መሀመድ በዘንደሮ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ዙሪያ ከጤና መምሪያው ቴክኒካል ኮሚቴ አባላት ጋር ግምገማ አካሂደዋል።

የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት መስጠት ከተጀመረበት ግዜ አንስቶ በዞን፣ በወረዳና በጤና ተቋማት የተሰጡ አገልግሎትቶች የችግኝ ተከላ፣ የነፃ የጤና ምርመራና የህክምና አገልግሎት በቤት ለቤት፣ በጎዳና ላይ እና በጤና ተቋማት መስጠትና የደም ልገሳ ተግባራት በተጠናከረ መልኩ እየተሰራ መሆኑን አቶ ጴጥሮስ አርአያ(የእናቶች ኦፊሰር) ባቀረቡት ሪፖርት ገልጸዋል።

በቀረበው ሪፖርት ውይይት ከተደረገ በኋላ አቶ ኡስማን አሊና ወሮ አንሻ መሀመድ በሰጡት ማጠቃለያ በዘንድሮው የጤናው ዘርፍ የክረምት በጎ አድራጎት መርሃ ግብር ከተለመደው ተግባራት በተጨማሪ የጤና ተቋማትን ምቹ እና ፅዱ የማድረግ ስራዎችንም ጨምሮ እየተሰራ መሆኑን በመግለፅ በእስካሁን አፈጻጸም ተግባራትን ተስማምተን በተገባው ልክ የማይፈጸሙ ወረዳዎች መኖራቸውን ገልጸዋል።

አቶ ኡስማን አክለውም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የዜግነት ሃላፊነት ብቻ ሳይሆን በደስታ የምናስቀጥለው ትልቅ አሻራ መሆኑን ተገንዝበን አገልገሎቱን በጤናው ሴክተር በሚገኙ ተቋማት፣ በሴቶች የልማት ህብረት አደረጃጄቶች፣ የበጎ ፍቃድ አአገልግሎት ለመስጠት የተመዘገቡትን ጨምሮ እንዲሁም የግል ጤና ተቋማትን በማሳተፍ አገልግሎቱ አጠናክረን በሚቀጥሉት ሁለት ወራት ይሰጣል ብለዋል።

ከፍለው መታከም የማይችሉ በርካታ ዜጎች ተጠቃሚ የሚያደርግ ነጻ የጤና ምርመራና ህክምና አገልግሎት፣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ፣ የደም ልገሳ እንዲሁም የአቅመ ደካማዎችን ቤት የመስራትና መጠገን፣ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች፣ የማዕድ ማጋራት፣ ከአጋር አካላት ጋር የሚሰራውን ነጻ የአይን ሞራ ገፈፋ አገልግሎት፣ የህክምና መሳሪያዎች ጥገና እና ሌሎች በጎ አገልግሎት በጤናው ሴክተር እንደሚከናወኑ ገልጸው ለተግባራዊነቱም ሁሉም አካላት እርብርብ እንዲያደረግ ጥሪ አቅርበዋል።
ሃምሌ 21/2017 ዓ.ም/ከሚሴ/ኦዞጤመ ህ/ግ

27/07/2025

ሁለተኛዉ የተባበሩት መንግስታት የምግብ ሥርዓተ ጉባዔ በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ብዙ ጠቀሜታ አለዉ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ
_________
ሁለተኛዉ የተባበሩት መንግስታት የምግብ ሥርዓተ ጉባዔ በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ መካሄዱ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለዉ የገለጹት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በ ጉባዔው ከሌሎች ሀገሮች የምንማርበት እና እኛም ደግሞ ወደ ተግባር የተሸጋገርንበትን መንገድ ለሌሎች የምናሳይበት ነዉ ብለዋል።

በፈረንጆቹ 2021 በተደረገው የመጀመሪያው ጉባዔ ላይ ተሳታፊ የነበረችው ኢትዮጵያ፤ የምግብ ሥርዓት ጉዳይን በዕቅድ ውስጥ በማስገባት ልትተገብራቸው ቃል ከገባችባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ መሆኑን የጠቀሱት ሚኒስትሯ በዚህም በሰቆጣ ቃልኪዳን ፕሮግራም የተገኙ ዉጤቶችን በማስፋት በአሁኑ ወቅት ከ340 በላይ ወረዳዎች እየተተገበረ መሆኑን ገልጸዋል። ምግብ እና ሥርዓተ ምግብ ለጤና ትልቅ ፋይዳ አለው ያሉት ዶ/ር መቅደስ፤ በሥርዓተ ምግብ ውስጥ ያለፈ ትውልድ ጤናማ እና ምርታማ እንዲሁም ትልቅ ውጤት ማምጣት የሚችል ነው ብለዋል።

ነገ በይፋ በአዲስ አበባ የሚጀመረዉ የተባበሩት መንግስታት የምግብ ሥርዓት ጉባዔ የምግብ እና ሥርዓተ ምግብ ጉዳዮችን በስፋት የሚዳስስ ትልቅ ጉባዔ ነዉ ያሉት ዶ/ር መቅደስ ከዚህ አንጻር ከሌሎች ሀገሮች የምንማርበት፣ እንዲሁም እኛም ደግሞ ከቃላት ወደ ትግበራ የተሸጋገርንበትን መንገድ ለሌሎች የምናሳይበት ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia

በማህበራዊ ዘርፋ የጤናው ልማት ለጤና ስርዓት ጥራት ፍትሃዊነትና ደህንነት በተመለከተ፦ *******************የክልሉ መንግስት በክልሉ የጤና አገልግሎት ጥራት እና ፍትሃዊነትን ለማርጋ...
27/07/2025

በማህበራዊ ዘርፋ የጤናው ልማት ለጤና ስርዓት ጥራት ፍትሃዊነትና ደህንነት በተመለከተ፦
*******************
የክልሉ መንግስት በክልሉ የጤና አገልግሎት ጥራት እና ፍትሃዊነትን ለማርጋግጥ የተለያዩ አዳዲስ አሰራሮችን እየተገበረ ይገኛል፡፡

ጤና ጣቢያዎች ለነፍሰ-ጡር እናቶች ክትትል የአልትራሳውንድ አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል። በ32 ጤና ጣቢያዎች የመሰረታዊ ድንገተኛ ቀዶ ህክምና አገልግሎት እየተሰጠ ነዉ።

180 ሆስፒታሎቸ እና ጤና ጣቢያዎቸ ኦዲቴብል የሆነ የፋርማሲ አገልግሎት ተግበረዋል። በ10 ጤና ተቋማት የሙሉ ወይም ከፊል ኤሌክትሮኒክ የህክምና መረጃ አያያዝ ስርዓት ማስጀመር ተችሏል፡፡

በ79 ወረዳዎቸ ኤሌክትሮኒክ የማህበረሰብ ጤና መረጃ ስርዓት ተግብረዋል፡፡ በክልሉ 50 የማህበረሰብ መድኃኒት ቤቶች ተከፍትው አገልግሎት እየሰጡ ነዉ፡፡

በተጨማሪም በክልላችን የጤና ኤክስቴንስሽን ፕሮግራሙን ለማጠናከር ዘርፈ ብዙ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ በዚህም 518 አጠቃላይ የጤና አግልግሎት የሚሰጡ ጤና ኬላዎችን የተለዩ ሲሆን ከነዚህ ዉስጥ 66 ወይም 12.74 በመቶ ጤና ኬላዎች በቂ ግንባታ ያላቸዉ በተጨማሪ ለጊዜው 66 ጤና ኬላዎች ጤና ኤክስቴንሽን እና ከጤና ጣቢያ ባለሙያዎች ተመድቦላቸው አጠቃላይ የጤና ኬላ ጤና አግልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡


#አብክመጤናቢሮ

የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልከሪም መንግስቱ በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የጤናው ዘርፍ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ  መዋቅር 15ኛው ዓመታዊ ጉባኤ ተገኝ...
27/07/2025

የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልከሪም መንግስቱ በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የጤናው ዘርፍ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ መዋቅር 15ኛው ዓመታዊ ጉባኤ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት እንደሀገርም ሆነ በክልል ደረጃ የሴቶች በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚና ፖለቲካ መስክ ተጠቃሚ እንዲሆኑ አበረታች ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።

የሴቶች የአመራር ሰጭነት እንዲጎለብት የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች መሰጠቱን ገልጸዋል።

በጤና ተቋማት የሚሰጡ የጤና አገልግሎቶች ለሴቶች፣ ለህጻናት፣ለወጣቶችና ለአካል ጉዳተኞች የተመቹ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብለዋል።

በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጾታዊ ጥቃት ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት ቢሮ ኃላፊው በጤና ተቋማት የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላት የማስፋፋት ተግባር በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

የጤና ሚንስቴር ጉባኤው በአማራ ክልል መዲና ባህር ዳር ከተማ እንዲካሄድ መወሰኑ ፋይዳው የጎላ መሆኑን የገለጹት አቶ አብዱልከሪም መንግስቱ ለጉባኤ ተሳታፊዎች ማስታወሻ አበርክተዋል።

ሀምሌ 20/2017 ዓ.ም

''በጎ ፍቃደኝነት ለጤናማ ማህበረሰብ'' በሚል መሪ ቃል በባቲ ከተማ አስተዳደር የባቲ ጤና ጣብያ እና የባቲ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለአቅመ ደካሞችና ነዋሪዎች በነፃ የህክምና አገልግሎት እ...
25/07/2025

''በጎ ፍቃደኝነት ለጤናማ ማህበረሰብ'' በሚል መሪ ቃል በባቲ ከተማ አስተዳደር የባቲ ጤና ጣብያ እና የባቲ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለአቅመ ደካሞችና ነዋሪዎች በነፃ የህክምና አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል።

በባቲ ከተማ አስተዳደር ''በጎ ፍቃደኝነት ለጤናማ ማህበረሰብ'' በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፍቃዱ የባቲ ጤና ጣብያ እና የባቲ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ባለሙያዎች በቅንጅት በመሆን ለባቲ ከተማ አቅመ ደካሞችና ነዋሪዎች በመንገድ ዳር እንዲሁም ቤት ለቤት በመሄድ የተለያዩ የጤና ምርመራና ህክምና አገልግሎት በነፃ እየተሰጠ ይገኛል።

የሚሰጡ አገልግሎቶች:-
- የደም ግፊት ምርመራና ህክምና
- የስኳር በሽታ ምርመራና ህክምና
- የተላላፊ በሽታዎች ምርመራና ህክምና
- ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ምርመራና ህክምና
- የአይን ምርመራና ህክምና
- የአዕምሮ ጤና ምርመራና ህክምና
- የጤና ት/ትና የምክር አገልግሎት
- ሌሎች የጤና አገልግሎቶች በነፃ ይሰጣሉ...!

ባቲ ከተማ ኮሙኒኬሽን

ከ1.5 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ የተደረገበት የማህበረሰብ አቀፍ መድሃኒት ቤት  አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ የአርጡማ ፋርሲ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ገለፀ****በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር በአርጡ...
24/07/2025

ከ1.5 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ የተደረገበት የማህበረሰብ አቀፍ መድሃኒት ቤት አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ የአርጡማ ፋርሲ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ገለፀ
****
በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር በአርጡማ ፋርሲ ወረዳ በ1.5 ሚሊየን ብር የማህበረሰብ አቀፍ መድሃኒት ቤት መክፈት ተችሏል።

የአርጡማ ፋርሲ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ካሳሁን አለሙ እንደገለፁት የሚስተዋሉ የመድኃኒት እጥረቶችን በዘላቂነት ለመቅረፍ በ1.5 ሚሊየን ብር የማህበረሰብ አቀፍ መድሃኒት ቤት መክፈት መቻሉን የገለፁት ሀላፊው ለማህበረሰቡ መድሀኒት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል ብለዋል።

በወረዳው ከ70 ሺ በላይ የቤተሰብ አባላት የጤና መድህን ተጠቃሚ ናቸው በዚህም የህብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ለማርካት ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

በወረዳው ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ የተከፈተው ሞዴል ማህበረሰብ አቀፍ ፋርማሲ የህዝብን ችግር እንደሚያቃልል እና ለተጠቃሚው ህብረተሰብ እርካታን የሚጨምር መሆኑን ገልፀዋል።

በወረዳው ጤና ተቋማት የተሻለ አገልግሎት እያገኙ እንደሚገኝ የገለፁት የአርጡማ ፋርሲ ወረዳ ነዋሪዎች የመድሃኒትና ሌሎች የህክምና ግብአቶችን በማሟላት ለህብረተሰቡ እርካታ እንዲያገኙ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

Baga Bammaddan ! Baga Gammadne! Madaallii Ministeera Fayyaan Buufatni Fayyaa Magaalaa Kamisee Badhaafamaa Abbaa Urjii Af...
24/07/2025

Baga Bammaddan ! Baga Gammadne!

Madaallii Ministeera Fayyaan Buufatni Fayyaa Magaalaa Kamisee Badhaafamaa Abbaa Urjii Afurii ta'eera.
Buufatichi har'a irraa kaasee Tajaajila Altiraa saawondii kennuu eegaleera.

እንኳን ደስ አላችሁ / እንኳን ደስ አለን /

ከግዜ ወደግዜ ለህዝባችን በሚሰጡት አገልግሎት በተለያዩ መድረኮች ተሸላሚ የሆነው ፣ ባለ አራት ኮከብ ባለቤቱ የከሚሴ ከተማ ጤና ጣቢያ በዛሬው እለት የአልትራሳውንድ አገልግሎት በይፋ አስጀምሯል።

በጤና አገልግሎት የህብረተሰቡን ፍላጎት ለማሟላት ተግባራትን በእቅዱ መሰረት በግዜ እና በቦታ ከፋፍሎ መፈጸም ይገባል።አቶ ኡስማን አሊ የኦሮሞ ዞን ጤና መምሪያ ዋና ኃላፊየኦሮሞ ዞን ጤና መም...
24/07/2025

በጤና አገልግሎት የህብረተሰቡን ፍላጎት ለማሟላት ተግባራትን በእቅዱ መሰረት በግዜ እና በቦታ ከፋፍሎ መፈጸም ይገባል።
አቶ ኡስማን አሊ የኦሮሞ ዞን ጤና መምሪያ ዋና ኃላፊ

የኦሮሞ ዞን ጤና መምሪያ በ90 ቀናት እቅድ በትኩረት በሚሰሩ የጤና ተግባራት ዙሪያ አጠቃላይ ሰራተኞች ውይይት አካሂደዋል፦
***
ሀምሌ 17/2017 ዓ.ም/ከሚሴ/የኦሮሞ ዞን ጤና መምሪያ

የዞን ጤና መምሪያ በጤናው ዘርፍ የተዘጋጀውን ዓመታዊ እቅድ በጊዜ በመከፋፈል አፈፃፀምን ለማሻሻል ይረዳ ዘንድ ሁሉም ኦፊሰር የ 90 ቀናት(የሩብ ዓመት) እንዲያዘጋጅ በማድረግ በእቅድ ክፍል በኩል የተጠቃለለ የ90 ቀናት እቅድ አጠቃላይ ሰራተኞች በተገኙበት በአቶ መላኩ ግርማ የጤና መምሪያው የእቅድ፣ ክትትልና ግምገማ ኦፊሰር ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

የውይይት መድረኩን የመሩት አቶ ኡስማን አሊ የኦሮሞ ዞን ጤና መምሪያ ዋና ኃላፊ በሰጡት ማጠቃለያ ሁሉም ኦፊሰር ለ90 ቀናት ለመፈጸም የያዛቸውን ተግባራት በየደረጃው ለሚገኙት ፈጻሚ አካላት በማውረድ የጋራ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

የምንሰራቸው የጤና ተግባራት የህብረተሰቡን የጤና ፍላጎት ለማሟላትና ውጤታማ እንዲሆኑ ያልተቋረጠ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

አቶ ኡስማን አክለውም ወቅቱ ክረምት እንደመሆኑ ክረምቱን ተክትለው ሊከሰቱ የሚችሉ ተላላፊ በሽታዎችንና ድንገተኛ የህብረተሰብ ጥና አደጋዎችን መከላከል የሚያስችሉ ተግባራትን ፈጥነን መፈጸም እና የግንዛቤ ፈጠራ፣ የህዝብ ንቅናቄያችን ማድረግ ይገባል ብለው ከዚህ ጎን ለጎን የክረምት የበጎ ፍቃድ ተግባርን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።

በመጨረሻም ለእቅዶቻችን ትግበራ የማስፈፀሚያ ስልቶች የድጋፍ እና ክትትል(በፕሮግራማቲክ እና በተቀናጀ) በማድረግ፣ ስልጠናና አቅም ግንባታ ለሚሹ ተግባራት በጀት በማፈላለግና በማሰጠን፣ ️የሴቶች አደረጃጀትን ማጠናከር እና መጠቀም፣ መማማርና እድገት፣ የመረጃ አያያዝ ስርአት መዘርጋት፣ አዳዲስ አሰራሮችን መተግበር፣ ሜንተርሽፕ ማጠናከር፣ ግምገማ ማካሄድን በመተግበር መሆኑን አሳስበዋል።

በፋብሪካ የተቀነባበሩና በውስጣቸው ከፍተኛ ጨው፣ ስኳርና ቅባት ያላቸውን ምግቦች ለልጅዎ ባለመስጠት የልጅዎን ጤና ይጠብቅ!
24/07/2025

በፋብሪካ የተቀነባበሩና በውስጣቸው ከፍተኛ ጨው፣ ስኳርና ቅባት ያላቸውን ምግቦች ለልጅዎ ባለመስጠት የልጅዎን ጤና ይጠብቅ!

Address

Kemise

Telephone

+251335540266

Website

https://arhb.gov.et/

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Qajeelcha Fayyaa G/S/Oromoo የኦሮሞ ዞኑ ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Qajeelcha Fayyaa G/S/Oromoo የኦሮሞ ዞኑ ጤና መምሪያ:

Share