Central Ethiopia Region Yem Zone Saja General Hospital

Central Ethiopia Region Yem Zone Saja General Hospital Saja General Hospital is Committed to provide Quality Healthy Care Up On Communicable and Noncommunicable Diseases in Hospital care.

 በሳጃ ከተማ አስተዳደር የሳጃ ሆስፒታልና የሳጃ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የጤና ስፖርት የመረብ ኳስ ቡድን በፎቶ
07/12/2025


በሳጃ ከተማ አስተዳደር የሳጃ ሆስፒታልና የሳጃ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የጤና ስፖርት የመረብ ኳስ ቡድን በፎቶ

የዓለም ኤድስ ቀን ተከበረ          ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።        ህዳር 22/2018 ዓም ሳጃ ሆስፒታል    ተግዳሮቶችን በመቋቋም የኤችአይቪ ኤድስ ምላሽ በዘላቂነት ...
03/12/2025

የዓለም ኤድስ ቀን ተከበረ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ህዳር 22/2018 ዓም ሳጃ ሆስፒታል

ተግዳሮቶችን በመቋቋም የኤችአይቪ ኤድስ ምላሽ በዘላቂነት እናረጋግጥ በሚል መሪ ቃል ተከበረ ።

በየዓመቱ ህዳር 22 የዓለም ኤድስ ቀን ተከብሮ ይውላል ።
ስለሆነም በተለይ ቀኑ ስታሰብ የኤችአይቪ ቫይረስ መተላለፊያ መንገድ እና መከላከያና ህክምናውን በተመለከተ ተጨማሪ ማንቅያ ግንዛቤ ይሰጣል ።

በመርሐ ግብሩ ላይ የክፍሉ ፎካል የሆኑት አቶ በልስቲ ልየው የኤችአይቪ ኤድስ ህክምና ክትትል ስራዎችን በሀገር ፣በክልል፣በዞን፣በሆስፒታሉ ነበራዊ ሁነታ በሪፖርት አቅርበዋሉ።

ከሪፖርቱ መነሻ የተነሱትን ችግሮች ከሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ አሚና ሙሳ አወያይነት ውይይት ተደርጓል ከውይይቱ መነሻ የተስተዋሉ ችግሮች በየደረጃው ትኩረት ተሰጥቶት መሰራት እንዳለበት አቅጣጫዎች ተቀምጧል ።
ምንጭ ፦ ART

አስቸኳይ ማስታወቂያለማዕከላዊ ኢትዮጰያ ክልል የሙያ ፍቃድ አመልካች የጤና ባለሙያዎች በሙሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የጤናና ጤናነክ አገልግሎቶች እና ግብዓቶች ጥራት ቁጥጥር ባለስ...
27/11/2025

አስቸኳይ ማስታወቂያ

ለማዕከላዊ ኢትዮጰያ ክልል የሙያ ፍቃድ አመልካች የጤና ባለሙያዎች በሙሉ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የጤናና ጤናነክ አገልግሎቶች እና ግብዓቶች ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የጤና ሚኒስቴር ባወረዳዉ የNo license, no practice ንቅናቄን መነሻ በማድረግ ላለፉት ሁለት ወራት ቅዳሜን ጨምሮ በሳምንት ለ 6 ቀናት የሙያ ፍቃድ አገልግሎት ስሰጥ መቆየቱ ይታወቃል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ የሙያ ፍቃድ አመልካች ባለሙያዎች ሲስተናገዱ ቆይቷል።

በመሆኑም የንቅናቄዉ ወቅት (ጥቅምት 30/2018) ማብቃቱን ተከትሎ ባለሰልጣን መስሪያ ቤቱ ሌሎች የቁጥጥሩ ዘርፍ ሥራዎችን በትኩረት ለማከናወን ይቻል ዘንድ ከቀን 19/3/2018 ጀምሮ ላልተወሰነ የጊዜ በአካል ይሰጥ የነበረዉ የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፍቃድ አገልግሎት የማይሰጥ መሆኑን እየሳወቅን አገልግሎቱ ዳግም ሲጀመር በማስታወቅያ የምንገልጽ መሆኑን እናሳዉቃለን።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የጤናና ጤናነክ አገልግሎቶች እና ግብዓቶች ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

ማርበርግ ቫይረስ በሽታ       Marburg Virus Disease     """"""""""""""""""""""""""""""""""""""" ህዳር 9/2018 ዓም ሳጃ ሆስፒታል       የማርበ...
18/11/2025

ማርበርግ ቫይረስ በሽታ
Marburg Virus Disease
"""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
ህዳር 9/2018 ዓም ሳጃ ሆስፒታል
የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በተመለከተ ለሆስፒታሉ ማህበረሰብ ስለ በሽታው ምንነት የግንዛበ ማብራርያ ተሰጠ።
ማብራሪያዉን ያስጀመሩት የሆስፒታሉ ሜድካል ዳረክተር ዶ/ር ዝናው እንዳሉት የማርበርግ በሽታ በጣም ጥንቃቄ የምፈልግ ስለሆነ በተለይ የሆስፒታሉ ማህበረሰብ አስፈላግዉን ጥንቃቄ እንያደርግ አሳስበዋል።
ስልጠናዉን የሰጡት የሆስፒታሉ RRT(Rapid responce team) ሰብሳቢ ዶ/ር ይትባረክ እና የሆስፒታሉ PHEM (የበሽታ ቅኝት) ፎካል አቶ ጋሻው በጋራ ስለ በሽታው ማብራሪያ /ገለፃ አድርገዋሉ።
የማብራሪያ ስልጠናው በተለይ የበሽታው አመጣት ታሪክ ፣ የመተላለፊያ መንገዱን ፣ የመከላከያና መቆጣጠሪያ ዘደዉን ፣የህክምና ዕርዳታውንና ለሎች አስፈላጊ የጤና ት/ት ተሰጠ።
ምንጭ፦ሆስፒታሉ

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምንነት፣ መተላለፊያ መንገዶችና መከላከያ ዘዴዎች  Website: moh.gov.etFacebook: facebook.com/EthiopiaFMoHTwitter: x.com/fmo...
15/11/2025

የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምንነት፣ መተላለፊያ መንገዶችና መከላከያ ዘዴዎች



Website: moh.gov.et
Facebook: facebook.com/EthiopiaFMoH
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት(EPHI) በተገኙ  ከፍተኛ ኤክስፐርቶችና ባለሙያዎች  ድጋፋዊ ክትትል በማድረግ  ያገኙትን ግኝት  ለሆስፒታሉ ማነጂሜንት አቅርቦዋል ። ...
15/11/2025

ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት(EPHI) በተገኙ ከፍተኛ ኤክስፐርቶችና ባለሙያዎች ድጋፋዊ ክትትል በማድረግ ያገኙትን ግኝት ለሆስፒታሉ ማነጂሜንት አቅርቦዋል ። የክልላችን ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በየጊዜው እያደረጉት ያለው ድጋፍ የሚመሰገን ሲሆን ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት መሆኑ ተነስቷል ።
ሆስፒታሉ ደረጃው ከማደጉ ጋር ተያይዞ የላቦራቶሪ ምርመራ መሳሪያዎችን ክፍተት የድጋፍ ትብብር እንድደረግ በማነጅመንት በኩልም ሀሳብ ቀርቦላቸዋል።
ሆስፒታሉ በሶስት የላብራቶሪ ምርመራ ዕውቅና ለማግኘት (accreditation) በተለይም የሳንባ ነቀርሳ ምርመራ( Microscope, and Genexpert) እና የወባ ምርመራ ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራት ላይ ነው። አሁን የተከሄደባቸው ሂደቶች እጅግ በጣም ጥሩ ሁኔታ ላይ ሲሆን ቀታይ መከድ ያለበትንም በገለፃቸው ወቅት አብራርቷል።
ጎን ለጎን የሳጃ አጠቃላይ ሆስፒታል የአራት ወራት የሥራ አፈፃፀም ሂደትንም መገምገም ተችሏል ። የሥራ ኤክስፐርቶች ሥራዎቻቸውን በማቅረብ የተገመገመ ሲሆን ከአፈፃፀም ጋር ከባለፈው ተመሳሳይ ዓመት ጋር መሻሻል መኖሩ ተገልጿል።
በውይይቱም በጥንካሬ የተለየውን ለማስቀጠል መሻሻል የሚገባቸውን አቅጣጫ ተቀምጧል።
በመጨረሻም በክፍተት የተገመገሙት ሥራዎችን በመከለስ ፈጥኖ ማሻሻል የሚገባ መሆኑ ተነስቷል።
የዘገባው ምንጭ -የሳጃ አጠቃላይ ሆስፒታል የጥራት ማሻሻያ ክፍል
(ሳጃ :ህዳር 6/2018 ዓ;ም)

ማርበርግ  ቫይረስ1) በሽታው ምንድን ነው? #የቫይረሱ አይነት: ማርበርግ ቫይረስ የፋይሎቫይረስ (Filoviridae) ቤተሰብ አባል ሲሆን ይህም ኢቦላ ቫይረስ የሚገኝበት ቤተሰብ ነው። ለዚህ...
15/11/2025

ማርበርግ ቫይረስ

1) በሽታው ምንድን ነው?

#የቫይረሱ አይነት: ማርበርግ ቫይረስ የፋይሎቫይረስ (Filoviridae) ቤተሰብ አባል ሲሆን ይህም ኢቦላ ቫይረስ የሚገኝበት ቤተሰብ ነው። ለዚህም ነው ሁለቱም በሽታዎች ተመሳሳይ የሕመም ምልክቶች እና የሞት መጠን ያላቸው።

#ክብደት: በሽታው ከባድ እና ከፍተኛ የሞት መጠን ያለው ሲሆን፣ በቅርብ ጊዜ በተከሰቱ ወረርሽኞች በበሽታው ከተያዙት ውስጥ እስከ 88% የሚደርስ ሰዎች ሞተዋል (እንደ ወረርሽኙ ሁኔታ ሊለያይ ይችላል)።
#ታሪክ: በሽታው ለመጀመሪያ ጊዜ በ1967 ዓ.ም በጀርመን ማርበርግ እና በፍራንክፈርት እንዲሁም በሰርቢያ ቤልግሬድ ከተሞች ተከስቷል። ቫይረሱ የመጣው ከዩጋንዳ በመጡ የላብራቶሪ ምርምር ዝንጀሮዎች አማካኝነት ነው ይባላል።

2) ስርጭት (በሽታው እንዴት ይተላለፋል?)
+++ ዋናው #ምንጭ: የማርበርግ ቫይረስ ተሸካሚዎች ፍራፍሬ ላይ የሚያዘወትሩ የሌሊት ወፎች (Rousettus bats) ናቸው። ሰዎች በቫይረሱ ሊያዙ የሚችሉት በእነዚህ የሌሊት ወፎች ባሉበት ዋሻዎች ወይም ማዕድናት ውስጥ በመገኘት ነው።

+++ ከሰው ወደ ሰው የሚኖረው #ስርጭት: ቫይረሱ ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፈው በበሽታው የተያዘ ሰው ወይም እንስሳት በሚወጡ ፈሳሾች (ደም፣ ምራቅ፣ ማስታወክ፣ ሰገራ፣ ሽንት፣ የዘር ፈሳሽ እና ሌሎች) ጋር በቀጥታ በመገናኘት ነው።
3) #ምልክቶች
የበሽታው ምልክቶች በአብዛኛው ከ2 እስከ 21 ቀናት ባለው ጊዜ ውስጥ ይታያሉ።

የሚከተሉትን እንመልከት
#የመጀመሪያ ደረጃ ላይ : ከፍተኛ ትኩሳት፣ ከባድ ራስ ምታት፣ ከባድ የጡንቻና የመገጣጠሚያ ህመም፣ ድካም ስሜት።
#ሁለተኛ ደረጃ (ከጥቂት ቀናት በኋላ): ከባድ ተቅማጥ፣ የሆድ ቁርጠት፣ ማቅለሽለሽ፣ ማስታወክ፣ የደረት እና የጉሮሮ ህመም።
#የከፋ ደረጃ (ከ5-7 ቀናት በኋላ) ከባድ የደም መፍሰስ (ከአፍንጫ፣ ከድድ፣ ከዓይን እና የቆዳ ስር)፣ የጉበት እና የኩላሊት ድካም፣ የንቃተ ህሊና መሳት፣ የብዝሃ-አካል ስራ መቆም (Multi-organ failure) እና ሞት። ከዚህ በተጨማሪ የዓይን መቅላት፣ የቆዳ ሽፍታ (በተለይ በደረት፣ ጀርባና ሆድ አካባቢ)።

4)የሚሰጠው ህክምና እና መከላከያ መንገዶች
#ፈውስ: ለጊዜው ቫይረሱን የሚያጠፋ የተረጋገጠ መድኃኒት ወይም ክትባት የለም።
#ህክምና: የሚሰጠው ህክምና ምልክቶችን ለማስታገስ (Supportive Care) ነው።
#ፈሳሽ መተካት (IV fluids): በከፍተኛ ተቅማጥ እና ማስታወክ የጠፋውን ፈሳሽ መሙላት ነው።
#የደም መፍሰስ ቁጥጥር: የደም ግፊትን ማረጋጋት እና የደም መርጋት መከላከል/ማከም።
#የተጎዱትን የአካል ክፍሎች (ኩላሊት፣ ጉበት) ድጋፍ መስጠት።

በጣም #አስፈላጊው ነጥብ
-) የግል መከላከያ ቁሳቁስ (PPE): የጤና ባለሙያዎች የታመሙ ሰዎችን ሲያክሙ ጓንት፣ ጋውን፣ ጭንብል እና የዓይን መከላከያ የግድ መጠቀም አለባቸው።
_) ንጽህና: እጅን በአግባቡ በሳሙና መታጠብ፣ በተለይ የታመመ ሰው የነካን ወይም የጎበኘን ከሆነ።

የበለጠ መረጃ ለማግኘት ከፈለጉ
1) የዓለም ጤና ድርጅት (World Health Organization - WHO): Marburg Virus Disease (MVD)

2) የአሜሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከላት (Centers for Disease Control and Prevention - CDC : Marburg Hemorrhagic Fever (Marburg HF)

ባምላኩ አበባው
ፕሮፌሽናል ነርስ እና የማህበረሰብ ጤና ባለሞያ
ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ህክምና ማዕከል

በሳጃ ከተማ አስተዳደር የሳጃ ጤና ጣቢያ አገልግሎት አሰጣጥ ከሳጃ አጠቃላይ ሆስፒታል ከተለያዬ ሥራ ክፍል የተወጣጡ  ባለሙያዎች ድጋፋዊ ክትትል  አካሂደዋል።       ዓላማውም የእርስ በርስ...
14/11/2025

በሳጃ ከተማ አስተዳደር የሳጃ ጤና ጣቢያ አገልግሎት አሰጣጥ ከሳጃ አጠቃላይ ሆስፒታል ከተለያዬ ሥራ ክፍል የተወጣጡ ባለሙያዎች ድጋፋዊ ክትትል አካሂደዋል።
ዓላማውም የእርስ በርስ በመደጋገፍ የመማማርና የሙያ ሽግግር ለመፍጠር ታሳብ ያደረገ ነው።
አጠቃላይ በጥንካሬ የታዪትን በማስቀጠል መሻሻል የሚገባቸው የሪፎርም ሥራዎችን ጤና ጣቢያው አጠናክረው መቀጠል የሚገባው መሆኑን ተሰምሮበታል። ጤና ጣቢያው አገልግሎት የጀመረ በቅርብ ከመሆኑ ጋር ተይይዞ የሚታዪ የግባአት እጥረቶች ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ ለመፍታት ጥረት መደረግ ያለበት መሆኑ የውይይት አካል ነበር።
የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ችግር ፈቺና እያንዳንዱ ታላሚ ማህበረስብ የሚጠቀምበትን በመለየት መሰራት የሚገባ መሆን ተበራርቷል።
በመጨረሻም የጋራ ድርግት መርሃግብር በማዘጋጀት የዕለቱ ውይይት ተጠናቋል ::
ምንጭ -የሆስፒታሉ አገልግሎት ጥራት ማሻሻያ
(ሳጃ :ህዳር 5/2018)

13/11/2025

ወቅታዊ የጤና ጉዳይን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

Website: moh.gov.et
Facebook: facebook.com/EthiopiaFMoH
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

ሳጃ አጠቃላይ ሆስፒታል የማህበረሰብ  ዉይይት         (community forum)  አካሄደ ==================================               ህዳር    2/2...
11/11/2025

ሳጃ አጠቃላይ ሆስፒታል የማህበረሰብ ዉይይት (community forum) አካሄደ
==================================
ህዳር 2/2018 ዓ,ም :ሳጃ
የሳጃ አጠቃላይ ሆስፒታል በየሶስት ወር የሚያካሂደው የማህበረሰብ ውይይት ህዳር 2/2018 የም ዞን የጤና መመሪያ ኃላፍ እና የሆስፒታሉ ሥራ አመራር ቦርድ አባል አቶ ሰናዬ ረጉ አወያይተዋል ።
አጠቃላይ የሆስፒታሉ አገልግሎት ያለበትና ቀደም ሲል በነበረው እንድሻሻል በማህበረሰብ ደረጃ የተነሱትን ጉዳዮች የተከናወኑ ተግባራት በወ/ሮ አሚና ሙሳ በሆስፒታሉ ዋና ሥራአስኪያጅ አማካይነት ቀርቧል።
በመቀጠልም አስተያየት ሰጪዎች የአገልግሎት አሰጣጥ ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻሉ ገልጸዋል። ከመድሃኒት ጋር ተያይዞ እየገጠመ ያለውን እጥረት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅተው በመስራት ለመቅረፍ ጥረት የሚደረግ መሆኑ ተሰምሮበታል።
የወባን ወረረሽን ከመከላከያና ከመቆጣጠር አንፃርም ሁሉም ነዋር አጎበር አጠቃቀምና የመድሃኒት አወሳሰድ ችግሮችን ጤና ባለሙያዎች በሚሰጡት ምክርና ትምህርት ትኩረት አድርጎ መጠቀም እንደሚገባቸዉ ተበራሪቷል።
ምንጭ፦የሆስፒታሉ ጥራት ቁጥጥር

Address

Yem Saja
Saja
2212009

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Ethiopia Region Yem Zone Saja General Hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Category