Artist Wonte Agegnu Kutcha Memorial Road

Artist Wonte Agegnu Kutcha Memorial Road

18/02/2025

የቁጫ ሕዝብ ሲተርት "እፍረት ከሌለ እህል አይታጣም" ይላል። ተረቱም ለሆዳም የተተረተ ነበር !!!
====+=+++++++++

የጋሞ ዞንና የቁጫ መዋቅር አመራሮች በተለይም ከ6ቱ ቀበሌያት የተውጣጡና የነሱ ተላላኪዎች በቁጫ ሦስቱ መዋቅሮች ውስጥ ምን እየሠሩ ነው?

1. ሕዝቡን የዱቡሻ ባህል ነው ብለው የመቃብር አፈር በጥብጠው አጠጥተዋል፣
2. የኃይማኖት መሪዎችንና ተከታዮቻቸውን በኃይል ለጣዖታቸው አሰግደዋል፣
3. የሕዝቡን ሀብትና ንብረት ያለምንም ሕግ መሠረት ዘርፈዋል፣
4. ለጣዖታቸው አልሰግድም ያለውን እጅና እግር ሰብረዋል፣
5. ራስህን ቁጫ ነኝ ትላለህ ብለው ከቤቱ፣ ሀብቱና ንብረቱ አፈናቅለዋል፣
6. የማኅበራዊ ማግለልን ፈፅመዋል፣
7.በሕዝብ ተወካዮች ላይ የግድያ ሙከራ ፈፅመዋል፣
8. ሌሎች በሰው ልጅ ላይ ሊፈፀሙ ቀርቶ ሊታሰቡ የማይገቡ ተግባራትን ፈፅመዋል።

ከላይ በተጠቀሱትና በሌሎች ሲዖላዊ ድርጊቶቻቸው ለተጎዳውና በሕይወት ላለው የቁጫ ሕዝብ ያበረከቱት አስተዋፅዖ:-

1. የሰላምበር ከተማን አመዳም ማድረግና በስሙ የማምለኪያ አፀድ ወይም ጣዖት መትከል፣
2. የሰላምበር ከተማን ከየትኛውም የፈርጅ ደረጃ እንዲወጣ ማድረግና ለማዘናጊያና ገንዘብ ዝርፊያ በመብራት ስም ዘመቻ መክፈት፣
3. የሰላምበር ከተማ ሕዝብ በሰቆቃና በግዳጅ የጣዖት አምልኮ ውስጥ እንዲገባ ተደርጎ ገንዘቡን እየተዘረፈ ግን በንፁህ ውኃ እጦት እንዲሰቃይ ማድረግ፣
4. በቁጫ አልፋ ወረዳ የጫባ ሦንባ ቀበሌ በሠራው ዳስ ምረቃ ላይ የዞኑን ዋና አስተዳዳሪን ጨምሮ በ20 መኪና ከ100 በላይ ሰው መታደምና የሕዝቡን ጥሪት መበዝበዝ፣
5. ሦስቱንም የቁጫ መዋቅሮች ከየትኛውም ልማት ዳር ማውጣትና የሕዝቡን ኪስ ማራቆት፣
6. በየወሩ ዞኑ በሚያመርተው ዋንጫ ቢንበሻበሽም ምንም የሚጨበጥና የሚዳሰስ ነገር መጥፋት፣
7. የሕዝብና የመንግሥት እንዲሁም የከተማና የገጠር መሬት መቸብቸብና መክበር፣
8. በሕገወጥ ቅጥር የ6 ቀበሌያት ሰዎችን መቅጠርና ከሌሎች የቁጫ መዋቅሮች ለወጉ ማኖ ማስነካት፣
9. የመንግሥት ሠራተኛውን ሆነ ብሎ ማስራብ፣ ከሥራ ማፈናቀል፣ ከደመወዝና ደረጃ ዝቅ ማድረግ፣
10. በሁሉም ተቋማት ሙስናና ብልሹ አሠራር መደበኛ ሥራ ማድረግ፣
11. ሌሎች ኢሰብዓዊ ተግባራትን እየፈፀሙ መኖራቸውን ለመደበቅና አጀንዳ ለማስቀየስ እንዲሁም ከተጠያቂነት ለመዳን በመከጀል የ2005 ነጠላ ዜማ "ደባል አጀንዳ" የሚል ማቀንቀን ይገኙበታል።

ይህንን ሁሉ ኢሰብዓዊ እና ኢሞራላዊ ድርጊት የፈፀሙት የብልፅግና ፓርቲ አባላትና አመራሮች ነን በሚል ነው። ነገር ግን የብልፅግና ፓርቲ እንደዚህ አይነት የወረደ ተግባር ፈፅሞ እኔ የብልፅግና ፓርቲ አባል ነኝ የሚለውን አላውቅም እያለ ነው።

ስለዚህ በቁጫ በሦስቱ መዋቅሮች ግልፅ የሆነ የሕግ ተጠያቂነት እንዲሰፍን ይጠበቃል።

አብረው ያስተኟቸውና የቀበሯቸው የቁጫ መዋቅሮች!
የብልፅግና ተሀድሶ/Reform/ ያነሳቸው ይሆን? የምናየው ይሆናል፥ ይጠበቃልም።

19/01/2025

በቁጫ ሦስቱም መዋቅሮች የቀጠለው የዘፈቀደ እሥራትና የዜጎች ስቃይ:-
____________________________________________

ስማቸው ከዚህ በታች የተዘረዘረው በዘፈቀደ ታሣሪዎች የታሠሩት ከቀን 01/05/2017 ዓ/ም ጀምሮ ነው።

ከቁጫ ወረዳ ገላ ታዳጊ ማዘጋጃ

1. አቶ እንግዳ ቃኘው :- የፓርቲያችን የአካባቢው አመራርና አባል በአካባቢው ፍትሕ በመጨለሙ በስደት ላይ ቆይተው ወደቤታቸው የተመለሱ ሲሆን አሣሪው በቅርቡ ሹመት የተሰጠውና ሕዝብን ለረጅም ዓመታት በቀበሌ ሊቀመንበርነት ሲያሰቃይ የኖረው አቶ ግዛቸው ቦረና ነው።

ከቁጫ አልፋ ወረዳ

1. አቶ ዘለቀ ኮዮ:- የፓርቲያችን የአካባቢው አመራርና አባላችንና በስደት ቆይተው ወደቤታቸው የተመለሱ ሲሆን አሳሪዎች:-
ከቁጫ አልፋ ወረዳ እና ከጫባ በለስ ታዳጊ ማዘጋጃ:-
1. አቶ ተስፋዬ አላዛር የቁጫ አልፋ ወረዳ አፈ- ጉባዔ እና
2. አቶ ሞላ መኮንን፣ የጫባ በለስ ታዳጊ ማዘጋጃ ኃላፊ ናቸው።

ከሰላምበር ከተማ አስተዳደር

1. ተማሪ ቤተልሔም ዓለሙ ከቀጠና አምስት ስትሆን የቁጫ ሕዝብን ባህላዊ ዘፈን ደርሰሻል በሚል አሥረዋታል።
2. አቶ ታሪኩ ተስፋዬ ከቁጫ ወረዳ ውዜቴ ቀበሌ ሆኖ በተደጋጋሚ እያሳደዷቸው በስደት ቆይተው የተመለሱ ናቸው።

ይህ ከባድ የሆነው የፍትሕ ልሽቀት መፍትሔ እንዲያገኝ ቁሕዴፓ ለመንግሥት አካላት ጥሪውን ያቀርባል።

15/07/2024

Artist Wonte Agegnu Kutcha Timeless Music ወንቴ አገኙ ቁጫ ዘመን የማይሽረው ሙዚቃ

15/07/2024
እውነተኛ የህዝብ መሪ የሆኑት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በቁጫ ምድር እውነት መናገሩን ተከትሎ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕስ መስተዳደር አቶ ጥላሁን ከበደ በሰጠው ትዕዛዝ...
12/07/2024

እውነተኛ የህዝብ መሪ የሆኑት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በቁጫ ምድር እውነት መናገሩን ተከትሎ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕስ መስተዳደር አቶ ጥላሁን ከበደ በሰጠው ትዕዛዝ መሠረት የጋሞ ዞን አመራሮች ንፁሃን የቁጫ ብሔረሰብ ላይ የሚፈፀሙትን በደል ማቋቋም ተስኗቸው ዜጎች ከአከባቢው እየተፈናቀሉ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የቁጫን ብሔረሰብ በስሙ ያለ ቅጥያ በመጥራቱና አካባቢው ላይ ብልፅግና ፓርቲ መሸነፉን በአደባባይ ስላመኑ ሽንፈታቸውን አምነው መቀበል ያልቻሉ የጋሞ ዞን አመራሮች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕስ መስተዳደር አቶ ጥላሁን ከበደ ትዕዛዝ ተላላኪ የቁጫ ብልፅግና አመራሮች አማካኝነት ንፁሃን የቁጫ የሶስቱም መዋቅር ህዝብ ያለአግባብ በህገወጥ ገንዘብ መዋጮ እና በስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ የቁጫ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እንዲያሸንፍ አድርጋችኋል ብሎ በመቅጣት በማሰርና በማሳደድ ከአከባቢው እያፈናቀሉ ይገኛሉ።

ከቁጫ አልፉ ወረዳ ከዶጌ ጱላ አካባቢ ሁለት መቶ ሰባ (270) ሰዎች ተፈናቅሎ ጎፋ ዞን መላ አካባቢ ሰፍሯል። ምክንያቱም ህገወጥ የመጻፍ መዋጮ እያንዳንዱ ሰው እስከ አስር ሽህ ብር(10,000) እየከፈሉ ይገኛሉ። ለአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሁለት ሽህ ብር (2,000) እና ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እስከ አምስት ሽህ ብር (5,000) ድረስ ተገዶ እየከፈሉ ይገኛሉ። ዛሬ ደግሞ ማገዶ ቁጠባ ብሎ ለምድጃ እስከ ሁለት ሽህ ብር (2,000) ድረስ እያስገደዱ ይገኛሉ።

በቁጫ ወረዳ ስቆለ እና አካባቢው ላይ ለመንገድ ልማት እያንዳንዱ ሰው በግዴታ እስከ አስራ አምስት ሽህ ብር (15,000) እንዲሰጡ ተገዶ ሰፊ ቁጥር ያላቸው አባወራዎች እየተሰደዱ ይገኛሉ።

ስለዚህ የኢትዮጵያ መንግሥት ቁጫ ህዝብ ላይ የሚደርሰውን በደልና ግፍ በአስቸኳይ እንዲያስቆም እና ዘላቂ ሰላም እንዲያሰፍን ጥርያችንን እናቀርባለን።

ወ/ሮ አለምፀሐይ ጳዉሎስን በሰባዊነት እንደ ሰዉ በሰዉነቷ እናከብራታለን  ።ከዛ ባሻገር ከቁጫ ጋር በተገኘ በህዝባችን ስም ስትነግድ የነበረች እና የጥንት ከተማ የሆነች ሰላምበር እንድሁም የ...
07/07/2024

ወ/ሮ አለምፀሐይ ጳዉሎስን በሰባዊነት እንደ ሰዉ በሰዉነቷ እናከብራታለን ።

ከዛ ባሻገር ከቁጫ ጋር በተገኘ በህዝባችን ስም ስትነግድ የነበረች እና የጥንት ከተማ የሆነች ሰላምበር እንድሁም የንጉሥ ፓሻ ጎባና ቁጫ አመዳም እንድትሆን ዋና ተዋናይ የነበረችውን እችን አዉሬ እስከ ዘላለም አጋንንት መሆኗን እንዘክራለን።

Address

Kutcha
Sodo
KUTCHAZONE

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Artist Wonte Agegnu Kutcha Memorial Road posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Artist Wonte Agegnu Kutcha Memorial Road:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram