Defeat NTDs

Defeat NTDs This page is created to impact the fight against Neglected Tropical Diseases (NTDs) in Ethiopia.
(1)

‎የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ትኩረት የሚሹ የሃሩራማ አከባቢ በሽታዎች የምርምር እና ስልጠና ማዕከል ከ   ጋር በመተባበር የ2ተኛወን ዙር የመማህበረሰብ አቀፍ የመድኃኒት እደላ ሽፋን ጥናት (P...
07/08/2025

‎የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ትኩረት የሚሹ የሃሩራማ አከባቢ በሽታዎች የምርምር እና ስልጠና ማዕከል ከ ጋር በመተባበር የ2ተኛወን ዙር የመማህበረሰብ አቀፍ የመድኃኒት እደላ ሽፋን ጥናት (Post MDA Coverage Validation Survey for IoT Districts) የመስክ ስራው በተሳካ ሁኔታ እየሰራ ይገኛል።

‎የክረምቱ አየር አስቸጋሪ ቢሆንም በጤና ሚንስቴር እና ክልል ጤና ቢሮ አማካኝነት የሚተገበረው የአንጀት ጥገኛ ትላትል እና ብላሃርዚያ በሽታ ስርጭትን ለመግታት ታልሞ በተለዩ አከባቢዎች እየተሰጠ የቆየው የማህበረሰብ አቀፍ መድሃኒት እደላ ሽፋን ምን እንደሚመስል ለማወቅ ከአርባ ምንጭ ዩንቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የተወጣጡ ባለሙያዎች ነባራዊ ሁኔታውን በመቋቋም በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች በሚገኙ በተመረጡ ወረዳዎች መረጃውን በተሳካ ሁኔታ እየሰበሰቡ ይገኛሉ።

‎የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ትኩረት የሚሹ የሃሩራማ አከባቢ በሽታዎች የምርምር እና ስልጠና ማዕከል ከ   ጋር በመተባበር የ2ተኛወን ዙር የመማህበረሰብ አቀፍ የመድኃኒት እደላ ሽፋን ጥናት (P...
29/07/2025

‎የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ትኩረት የሚሹ የሃሩራማ አከባቢ በሽታዎች የምርምር እና ስልጠና ማዕከል ከ ጋር በመተባበር የ2ተኛወን ዙር የመማህበረሰብ አቀፍ የመድኃኒት እደላ ሽፋን ጥናት (Post MDA Coverage Validation Survey for IoT Districts) ለማድረግ ለባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ

‎በጤና ሚንስቴር እና ክልል ጤና ቢሮ አማካኝነት በሚተገበረው የአንጀት ጥገኛ ትላትል እና ብላሃርዚያ በሽታ ስርጭትን ለመግታት ታልሞ በተለዩ አከባቢዎች የማህበረሰብ አቀፍ መድሃኒት እደላ እየተሰጠ መቆየቱ ይታወቃል።

‎የማህበረሰብ አቀፍ መድሃኒት እደላ ፕሮግራም ከተካሄደባቸው የሀገሪቱ ክፍሎች በሶስት ክልሎች ዉስጥ በምገኙ በተመረጡ ወረዳዎች የመማህበረሰብ አቀፍ የመድኃኒት እደላ ሽፋን ጥናት (Post MDA Coverage Validation Survey for IoT Districts) ለማድረግ እና ለቀጣይ የፕሮግራሙ ትግበራ ለመሻሻል ግበአት የምሆኑ ጥናታዊ ሃሳቦችን ለማመንጨት ማዕከሉ ከ ጋር በመተባበር ከዩንቨርሲቲው ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለተወጣጡ ባለሙያዎች መረጃውን በ Kobo Toolbox መሰብሰቡን አስመልክቶ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል::

‎ከስልጠናው መልስ ባለሙያዎች ወደተመደቡበት ክልል በመሄድ የመስክ ጥናት መረጃ ማሰባሰብ ስራ እንደሚጀምሩ ይጠበቃል::

‎የቁንጭር /የቆዳ ላይ ሌሽማኒያሲስ/ ህክምናን የማስጀመር መርሃግብር በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሄደ ‎‎የደቡብ  ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ከወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ጋር በመሆን በወላይታ ሶዶ ...
20/07/2025

‎የቁንጭር /የቆዳ ላይ ሌሽማኒያሲስ/ ህክምናን የማስጀመር መርሃግብር በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሄደ

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ከወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ጋር በመሆን በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቁንጭር /የቆዳ ላይ ሌሽማኒያሲስ/ ህክምናን በሆስፒታሉ ለማስጀመር የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በሶዶ ከተማ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከዚህ በፊት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ብቻ ሲሰጥ የነበረው የበሽታው ህክምና በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እንዲሰጥ በማድረግ በበሽታው ለሚጠቁ የማህበረሰብ ክፍሎች እሴት እንደሚጨምር ይጠበቃል።

17/07/2025

Wuday imettanas bessiza gadha heera hargeta xomoosiza giigiso

09/07/2025
09/07/2025
የዓለም የቆዳ ጤና ቀን በተለያዩ መርሐ ግብሮች ተከበረየአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ትኩረት የሚሹ ሐሩራማ በሽታዎች ምርምርና ሥልጠና ማዕከል ከተለያዩ አጋር አካላት ባ...
09/07/2025

የዓለም የቆዳ ጤና ቀን በተለያዩ መርሐ ግብሮች ተከበረ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ትኩረት የሚሹ ሐሩራማ በሽታዎች ምርምርና ሥልጠና ማዕከል ከተለያዩ አጋር አካላት ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ2ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም የቆዳ ጤና ቀንን በተለያዩ መርሐ ግብሮች አክብሯል። የበዓሉ የማጠቃለያ መርሃ ግብር ዛሬ ሐምሌ 1 / 2017 ዓ/ም ተካሂዷል::

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ትብብር ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር ተክሉ ወጋየሁ ቆዳ ታሪካችንን፣ አካባቢያችንን፣ ጤናችንን ፣ እና የስሜታችንን ሁኔታ የሚያንጸባርቅ የሰውነታችን የመጀመሪያ መከላከያ ቢሆንም ብዙ ጊዜ ተገቢውን ትኩረት የማያገኝ የሰውነታችን ወሳኝ ክፍል መሆኑን ተናግረዋል። ሁልጊዜ ቆዳችን የሰውነታችን ውጫዊ ክፍል ብቻ ሳይሆን ውስጣችን የሆነውን ሁኔታ የሚያንፀባርቅ መሆኑን ማስታወስ ይገባል ያሉት ዶ/ር ተክሉ በትምህርትና ፈጠራ በመታገዝ ይህን አስደናቂ አካል የመንከባከብ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል። የቆዳ ጤና ቅድሚያ የሚሰጥበት የወደፊት ዘመን እንዲፈጠር የዚህ ዓይነት መድረኮችና የዘመቻ ሥራዎች ወሳኝ ሚና ያላቸው መሆኑን የገለጹት ም/ፕሬዝደንቱ ይህ ሁነት በአርባ ምንጭ እና በአካባቢው እንዲከበር የበኩላቸውን ለተወጡ የኮሌጁና የምርምር ማዕከሉ የሥራ ኃላፊዎችና ተመራማሪዎች ምስጋና አቅርበዋል።

የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ደስታ ጋልቻ በ 2017 የትምህርት ዘመን እንደ ኮሌጅ በሁሉም መስክ ስኬቶች የተመዘገቡ መሆናቸውን ገልጸው በቅርቡ በሁለት ፕሮግራሞች የተገኘውን ሀገር አቀፍ እውቅና ለአብነት ጠቅሰዋል። በኮሌጁ በዚህ ዓመት 50 የምርምር ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን የገለጹት ዶ/ር ደስታ ከነዚህም መካከል አስሩ የትብብር ፕሮጀክቶች መሆናቸውን ገልጸዋል:: ትኩርት የሚሹ የሐሩራማ አካባቢ በሽታዎች ምርምርና ሥልጠና ማዕከል በቆዳ በሚገለጹ የተዘነጉ የሐሩራማ አካባቢ በሽታዎች ላይ በማተኮር ዘርፈ ብዙ የምርምር እንዲሁም ማኅበረሰብ ተኮር ሥራዎችን እየሰራ ይገኛል ያሉት ዳይሬከተሩ ይህን በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከበርን በዓል ለማስተናገድ መቻላችን ትልቅ ዕድልና ስኬት እንዲሁም በቀጣይ በዘርፉ ሊሰሩ ለሚታሰቡ ትልልቅ ሥራዎች መሠረት የሚጥል መሆኑን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ የቆዳ ሐኪሞች ማኅበር ፕሬዝደንት ዶ/ር ሺመልስ ንጉሴ በዕለቱ ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት የቆዳ በሽታዎች ጉዳይ በጤና ሥርዓት ውስጥ ትኩረት የተነፈገው ዘርፍ ሲሆን ለዚህም ትክክለኛ የቆዳ በሽታዎች ጫና የሚታወቅ አለመሆኑን በምሳሌነት አንስተዋል። የቆዳ ጤና ቀንን ማክበር ብቻውን በቂ አለመሆኑን የገለጹት ዶ/ር ሽመልስ የቆዳ በሽታ ችግሮች በማኅበረሰብ ላይ የሚስከትሉትን ችግሮች ለመቅረፍ ከፍተኛ ጥረት የምናረግበትና ሰፋፊ የግንዛቤ ሥራዎችን የምንሰራበት ሊሆን እንደሚገባ አውስተዋል፡፡

በሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ትኩረት የሚሹ የሐሩራማ በሽታዎች ምርምርና ሥልጠና ማዕከል ዳይሬክተር ረ/ፕ አብነት ገ/ሚካኤል በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሁለተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከበር ሲሆን የምርምር ማዕከሉ በዓሉን የማክበር ዕድል ያገኘው በዓለም አቀፍ ደረጃ በተደረገ ውድድር አሸንፎ መሆኑን ገልጸዋል። በዓሉን ምክንያት በማድረግ በጋሞ ዞን ቆጎታ ወረዳ እና አርባ ምንጭ ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች መሰራታቸውን የገለጹት ዳይሬክተሩ በተጨማሪም የቆዳ በሽታ ልየታን ጨምሮ በሁለቱም አካባቢዎች 350 ለሚያህሉ ታማሚዎች ሕክምና መስጠቱን ተናግረዋል።

በምርምር ማዕከሉ ተባባሪ ተመራማሪ የሆኑት ዓለማየሁ በቀለ በቆዳ ላይ በሚገለጹ የሐሩራማ አካባቢ በሽታዎችን አስመልከተው ባቀረቡት ገለጻ በዓለማችን ከአንድ ቢሊዮን በላይ ሰዎች ትኩረት በሚሹ የሐሩራማ አካባቢ በሽታዎች የሚጠቁ ሲሆን የዓለም ጤና ድርጅት በዚህ ዘርፍ ከለያቸው 22 በሽታዎች መካከል 10 ከመቶው በቆዳ ላይ የሚከስቱ መሆናቸውን ገልጸዋል። እነዚህ በሽታዎች በአብዛኛው የኢኮኖሚ አቅማቸው ዝቅተኛ የሆኑ የገጠር የኀብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቁ መሆኑን የጠቀሱት ተመራማሪው ማዕከሉ ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመሆን በሽታዎቹን ከመለየት ባሻገር ተጨማሪ የተግባር ሥራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል::

የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የቆዳ ስፔሻሊስት ሐኪም ዶ/ር በረከት አድማሱ በዓለማችን ሶስት ሺህ የሚያህሉ የቆዳ ላይ በሽታዎች መኖራቸውን ገለጸው እ.አ.አ 2019፤ 98, 522 ሰዎች በቆዳ በሽታዎች ምክንያት ሕይወታቸውን አጥተዋል ብለዋል። በሀገራችን የቆዳ ጤና ጉዳይ ትኩረት የተነፈገው መስከ ሲሆን በኢትዮጵያ ያሉ የቆዳ ስፔሻሊስት ሐኪሞች ቁጥር 200 ብቻ መሆኑንና ከነዚህም መካከል 70 ከመቶው በአዲስ አበባ የሚሰሩ መሆናቸውን አስረድተዋል:: ይህም የዘርፉን ችግር የሚያሳይ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር በረከት የቆዳ ላይ በሽታዎች እንደ ሀገር እያስከተሉ ያሉትን የጤና ችግሮችን ከግንዛቤ በመስገባት ዘርፉ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አጽንዖት ሰጥተዋል።

በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ በቀረቡ ገለጻዎችን ተከተሎ የተለያዩ ጥያቄዎችን አስተያየቶች ተነስተው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን በመርሐ ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች ፣ ተመራማሪዎች ፣ ከአርባ ምንጭ ከተማ እና ከጋሞ ዞን አስተዳደር ጤና ጽ/ቤትና መምሪያ የተወጣጡ ባለድረሻ አካላት ተገኝተዋል።
ምንጭ፦ Arba Minch University

‎ከሰኔ 27-28/ 2017 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የውሃ፣ ሳኒተሽንና ሃይጅን ቅንጅታዊ ሥራዎችን በማጠናከር ትኩረት የሚሹ ሐሩራማ በሽታዎችን ለማጥፋት የታለመው የጋራ ምክክር መድ...
06/07/2025

‎ከሰኔ 27-28/ 2017 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የውሃ፣ ሳኒተሽንና ሃይጅን ቅንጅታዊ ሥራዎችን በማጠናከር ትኩረት የሚሹ ሐሩራማ በሽታዎችን ለማጥፋት የታለመው የጋራ ምክክር መድረክ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

‎መድረኩ በሀገርቱ ወጥ በሆነ መልኩ የWASH-NTDs Toolkit በተሻሻለ ሁኔታ እንዲተገበር ያለመ ሲሆን በ NALA በኩል በአማካሪዎች ተጠንቶ የቀረበው ሰነድን የማጥራት ተግባራት ተከናውነዋል።

‎በመድረኩ ከፌዴራል፣ ከሁሉም ክልልሎች እና የአለም አቀፍ መያድ ተወካዮች እንዲሁም ከሀገራችን NTDs አንባሳደሮች ጋር ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን በቀጣይ ሰነዱ በአገር ደረጃ ፀድቆ ከፌዴራል እስከ ወረዳ በከፍተኛ አመራሩ ዘንድ የጋራ ግንዛቤ ተፈጥሮ ወደትግበራ እንደሚገባ ይጠበቃል።

05/07/2025
27/06/2025

The Collaborative Research and Training Center for Neglected Tropical Diseases at Arba Minch University is honored to host the World Skin Health Day 2025 – Ethiopia Regional Event, with the valued support of the International League of Dermatological Societies (ILDS) and the International Society of Dermatology (ISD).

We are privileged to serve our communities through impactful pre-event outreach activities, reaching hundreds of individuals—particularly in underserved areas—with awareness, screening, and treatment for skin-related NTDs.

Together, we continue to promote equity in skin health and bring care to those who need it most.

Join us in commemorating the main event of World Skin Health Day 2025 – Ethiopia Regional Event on July 8!
World Skin Health Day CeraVe Skincare

International League of Dermatological Societies World Skin Health Day CeraVe Skincare
19/06/2025

International League of Dermatological Societies World Skin Health Day CeraVe Skincare

16/06/2025

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Defeat NTDs posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Defeat NTDs:

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Contact The Practice
  • Claim ownership or report listing
  • Want your practice to be the top-listed Clinic?

Share