Woldia Genral Hospital/ወልዲያ አጠቃላይ ሆስፒታል

  • Home
  • Ethiopia
  • Woldia
  • Woldia Genral Hospital/ወልዲያ አጠቃላይ ሆስፒታል

Woldia Genral Hospital/ወልዲያ አጠቃላይ ሆስፒታል Woldia Comprehensive Specialized Hospital/ ወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል !!

ሁሉም  ሰው  ሸር  በማድረግ  ለሁሉም  አድርሱ*እንደሚታወቀው  ወልዲያ  አጠቃላይ  ስፔሻላይዝድ  ሆስፒታል  ከCBP(cure blindness project) ከተባለ  ግብረ ሰናይ  ድርጅት  ...
16/11/2025

ሁሉም ሰው ሸር በማድረግ ለሁሉም አድርሱ

*እንደሚታወቀው ወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከCBP(cure blindness project) ከተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ከህዳር 22/03/18--27/03/18 ዓ .ም የሚቆይ የአይን ሞራ ግርዶሽ ላለባቸው ወገኖቻችን የነፃ ህክምና ስለሚሰጥ ችግሩ ያለባችሁ ወገኖቻችን ሁሉ በተጠቀሰው ቀን በመገኘት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ስንል በታላቅ ደስታ እናሳውቃለን!!!

Big shout out to my newest top fans! 💎 Nurye Belay, Desale Maereg, Wubshet Belay Yimer, Ali Tgabu Weloyew, Habtamu Tesfa...
24/10/2025

Big shout out to my newest top fans! 💎 Nurye Belay, Desale Maereg, Wubshet Belay Yimer, Ali Tgabu Weloyew, Habtamu Tesfaye, Zainb Mohamed, Alemnesh Getnet, Nuradis Zewdu, Habtemariam Melaku, Aster Enbelew, Berbir Mereja Press, Adisis Wolloyawa

Drop a comment to welcome them to our community, fans

26/08/2025

ደም በመለገስ የሰውን ሂወት እንታደግ !!!

CT scan!!!!
25/08/2025

CT scan!!!!

የእናቶችና የጨቅላ ሕፃናትን ሞት የመቀነስ የጤና ፖሊሲን አፈጻጸም ለማሻሻል የሚያስችል አጋዥ ስልጠና ማግኘታቸውን ሰልጣኞች ተናገሩ፡፡ (ወልድያ ከተማ)  በEngender Health አማራ ክል...
22/08/2025

የእናቶችና የጨቅላ ሕፃናትን ሞት የመቀነስ የጤና ፖሊሲን አፈጻጸም ለማሻሻል የሚያስችል አጋዥ ስልጠና ማግኘታቸውን ሰልጣኞች ተናገሩ፡፡ (ወልድያ ከተማ)

በEngender Health አማራ ክልል ቅርንጫፍ ፕሮግራም ፊልድ ኦፊስ RMNCH+ ፕሮጀክት ለወልድያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በእናቶችና ሕፃናት የሕክምና ዘርፍ ለተሰማሩ ሁሉም ባለሙያዎች የወላድ እናቶችን የድኅረ ወሊድ የደም መፍሰስን መከላከልና ማከም ትኩረት ያደረገ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

በዚህ ሥልጠና ከተሳተፉትና አስተያየታቸውን ካጋሩን መካከል በወልድያ ሆስፔታል የእናቶችና ሕጻናት ክፍል አስተባባሪ የሆኑት ካሳሁን ማርአበይ የድኅረ ወሊድ ደም መፍሰስ እናቶችን አንድም ለሞት ወይም ደግሞ ለረዝም ጊዜ በሆስፒታል በህክምና ድጋፍ እንዲቆዩ የሚያደረግ ከፍተኛ ችግር ነው፡፡ ይህን ችግር ለመፍታትም የድኅረ ወሊድን የደም መፍሰስ መጠንን የምንለካው በግምት ነበር፡፡ አሁን ግን Engender Health ፕሮግራም የፈሰሰውን የደም መጠን ግምታዊ ሥራ ያስቀረ የህክምና ቴክኖሎጅ ይዞ መጥቷል፡፡ ይህም ተገቢውን መድኃኒት በመስጠት የእናቶችንና የጨቅላ ሕጻናትን ሞት ለመቀነስ የሚያስችል ከነበረው አሠራር አንድ ደረጃ ከፍ ያለ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

ሌላኛዋ የሥልጠናው ተሰሳታፊና የሆስፒታሉ የዘርፉ ባለሙያ የሆኑት ወርቅነሽ ቢሰጥ ሥልጠናው የነበረንን ሙያ ማደስ ብቻ አይደለም፡፡ ብዙ ነገሮችን ያገኘንበት ሥልጠና ነው፡፡ ካዋለድናት በኋላ እየደማች ያለችን እናት እንዴት አድርገን ማዳን እንዳለብን ከነበረን እውቀት ላይ አዳዲስ ሲስተሞችን አሳውቆናል ብለዋል፡፡

ባለሙያዋ አክለውም ሥልጠናው በአሳታፊነቱም ይለያል፡፡ ከአሁን በፊት የሚሰጡ ሥልጠናዎች ብዙ ጊዜ አንድ ወይም ሁለት ባለሙያ ተመርጦ ነበር የሚሰጠው፡፡ ይኽ ስልጠና ግን ሁሉንም የዘርፉ ባለሙያዎች ያሳተፈ በመሆኑ ለአተገባበር አያስቸግርም በማለት የሥልጠናውን አሳታፊነት አድንቀዋል፡፡

በEngender Health አማራ ክልል ቅርንጫፍ ፕሮግራም ፊልድ ኦፊስ RMNCH+ ፕሮጀክት ሲኒየር ፕሮግራም አስተባባሪ የሆኑትና ሥልጠናው የሰጡት አምባዬ ጥላሁን ፕሮጀክቱ የእናቶችንና ሕጻናትን ጤና አገልግሎት በማሻሻል ሞትን ለመቀነስ በሚደረገው ጥረት አስተዋጽኦ ማድረግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የዛሬው ሥልጠናም በዓለም እንዲሁም በሀገራችን የመጀመሪያውና ቀዳሚው ለእናቶች ሞት ምክንያት የሆነውን የድኅረ ወሊድ የደም መፍሰስ ሁሉም ባለሙያ ቀድሞ ለመከላከል፣ ለመለየትና አስተማማኝ ህክምና ለመስጠት የሚያስችል ሥልጠና ነው ብለዋል የፕሮግራሙ አስተባባሪ፡፡

ለዚህ ፕሮግራም ውጤታማነትም ውስጣችንን በእናቶች ቦታ አድርገን ማሰብ አለብን፡፡ የእናቶች ጤና ትብብር ያስፈልገዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ በየደረጃው ያለው የጤና ተቋማት መሪ እስከ ታችኛው አገልግሎት ሰጭ ባለሙያ ሁሉም መተባባር አለበት፡፡ የሰለጡኑ የሆስፒታል ባለሙያዎችም መሥራት ብቻ ሳይሆን በሥራቸው በሚገኙ ጤና ተቋማት ባለሙያዎችን ያገኙትን እውቀት ያጋሩ ሲሉ አቶ አምባየ አሳስበዋል፡፡

በሥልጠና መርሐ-ግብሩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የወልድያ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ባልደረባ የሆኑት አቶ ይመር የሱፍ ሥልጠናው ሀገራችን ኢትዮጵያ በ2030 የእናቶችንና የጨቅላ ሕጻናትን ሞት በከፍተኛ ሁኔታ የመቀነስ ግብ አስተዋጽኦ ታላቅ ነው ብለዋል፡፡

Enigender Health Ethiopia PMNCH+ፕሮጀክት የ4 ዓመት ቆይታ ያለው፤ አማራ ክልልን ጨምሮ በ6 ክልሎችና በአጠቃላይ በዙር 900 አካባቢ የሚሆን ጤና ተቋማት የሚደግፍ፤ አሁን ላይ በአማራ ፕሮግራም ፌልድ ኦፊስ ሥር 189 ጤና ተቋማት በትግበራ ቅደም ተከተል የታቀፉና በአሁኑ ጊዜም በፕሮጀክትቱ ከታቀፉት መካከል 27ቱ የጤና ተቋማት ከሚያዝያ ወር 2017 ጀምሮ የተለያዩ ድጋፎችን ማድረግ የጀመረ ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት መሆኑን ከሥልጠና አመቻቾች ያገነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ነሀሴ 16 ቀን 2017 ዓ.ም
ወልድያ ከተማ አስተዳደር መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን

ከዚህ በታች  እንደሰፈረው  አይነትን ችግር    በጊዜ  ለመቆጣጠር  ነፍሰ  ጡር  እናቶች  የእርግዝና  ክትትል በጊዜ  ወይም ከሶስት  ወር  በታች  እያላችሁ  መጀመር  ለጤናችሁ  ወሳኝ ...
22/08/2025

ከዚህ በታች እንደሰፈረው አይነትን ችግር በጊዜ ለመቆጣጠር ነፍሰ ጡር እናቶች የእርግዝና ክትትል በጊዜ ወይም ከሶስት ወር በታች እያላችሁ መጀመር ለጤናችሁ ወሳኝ ስለሆነ ክትትል በጊዜ መጀመር አስፈላጊ መሆኑን ያስረዳል!! ይህ ከትንሿ ስሪንጅ💉 ያነሰ ቁመት ያለው የ 3 ወራት ዕድሜ ያለው ህፃን ልጅ [ፅንስ] ነው።

ልጁ ከማህፀን ውጭ የተፀነሰ ፅንስ [ectopic...]ሲሆን በቀዶ ህክምና የወጣ ልጅ ነው። በጊዜ ባይወጣ ኖሮ የእናትም የልጅም ህይወት ላይተርፍ ይችል ነበር ፤በየጊዜው የፅንስ ክትትል ማድረግ ዋና ጥቅሙ አንዱ ለዚህ ነው።

ከየት ተነስተን የት እንደ ደረስን ቆም ብለን ማየት እንችላለን፤ኩራት ለሰው ልጅ ፈፅሞ አይገባውም!

ፈጣሪ የፈለገውን እንደፈለገ አድርጎ መስራት ይችላል።

Eli Jah እንዳሰፈረው

21/08/2025

I got over 500 reactions on my posts last week! Thanks everyone for your support! 🎉

ለሁሉም  የሆስቲፒታሉ  ተገልጋዮች  በሙሉ  ከዚህ  በሃላ  የታካሚዎችን  መብት  ከማክበር  እና  የመጡበትን  ከመፈፀምም  አንፃር  የታማሚ  ጠያቂዎችን  እንደሚከተለው  የመጠየቂያ  ሰአት...
18/08/2025

ለሁሉም የሆስቲፒታሉ ተገልጋዮች በሙሉ ከዚህ በሃላ የታካሚዎችን መብት ከማክበር እና የመጡበትን ከመፈፀምም አንፃር የታማሚ ጠያቂዎችን እንደሚከተለው የመጠየቂያ ሰአት ስለተመቻቸ በተገለፀው ሰአት በመምጣት አላስፈላጊ እንግልትን በጋራ እንከላከል እንላለን። ከታች ያለውን የሰአት ሽግሽግ አብዛኛውን ማህበረሰብ ይስተካከል ባላችሁን መሰረት አስተካክለናል።
የመጠየቂያ ስዓት
ጧት 12:00- 2:00 ከስዓት 6:00-8:00 ማታ 10:30-12:30 የተሻሻለ መሆኑን እንገልፃለን።

ሁላችንም  ሸር  በማድረግ  ይሄን  መረጃ  አጋሩልን !!!         በአብክመ ጤና ቢሮ ግዥ ተፈፅሞ ለወልዲያ ሆስፒታል ገቢ ተደርጎ የነበረው ሲቲ ስካን ማሽን በጥሩ ሁኔታ ኢንስቶል ተደር...
17/08/2025

ሁላችንም ሸር በማድረግ ይሄን መረጃ አጋሩልን !!! በአብክመ ጤና ቢሮ ግዥ ተፈፅሞ ለወልዲያ ሆስፒታል ገቢ ተደርጎ የነበረው ሲቲ ስካን ማሽን በጥሩ ሁኔታ ኢንስቶል ተደርጎ የሙከራ ስራ ተሰርቶ ለባለሞያዎች አጭር ግንዛቤ ተፈጥሯል። በአጭር ቀን ሙሉ ስልጠና ተሰጥቶ ወደ ተሟላ አገልግሎት የሚገባ ሲሆን በዛሬው ዕለት ለሶስት ታካሚዎች ሙከራ ተደርጎበት ደሴ ከመሄድ መዳን ችለዋል።የሆስፒታላችን ተገልጋዮቾ በአጭር ጊዜ ሙሉ አገልግሎ የሚጀምር መሆኑን እያሳወቅን እንኳን ደስ አላችሁ ይላል ወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ።

በከፍተኛ  ሁኔታ  ሆስፒታላችን  ላያ  እየተሰራ  ያለው  መሰረተ  ልማት  ተጠናክሮ  እንዲቀጥልና  የሲቲስካኑን  ገጠማ  አፋጥኖ  ለማህበረሰባችን  የተሟላ  የህክምና  አገልግሎት  በመስጠ...
31/07/2025

በከፍተኛ ሁኔታ ሆስፒታላችን ላያ እየተሰራ ያለው መሰረተ ልማት ተጠናክሮ እንዲቀጥልና የሲቲስካኑን ገጠማ አፋጥኖ ለማህበረሰባችን የተሟላ የህክምና አገልግሎት በመስጠት የጤናውን ፍላጎት የመለሰ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ሁሉም የሆስፒታሉ ማህበረሰብ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የበኩሉን አስተዋፆ ማድረግ ይጠበቅብናል!! የተሻሻለ የጤና አገልግሎት ለሁሉም!!!!

Big shout out to my newest top fans! 💎 Desale Maereg, Wubshet Belay Yimer, Ãłî Tgåbû, Nurye Belay, Habtemariam Melaku, A...
09/07/2025

Big shout out to my newest top fans! 💎 Desale Maereg, Wubshet Belay Yimer, Ãłî Tgåbû, Nurye Belay, Habtemariam Melaku, Aster Enbelew

Drop a comment to welcome them to our community, fans

Address

North Wollo/Ethiopia
Woldia

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woldia Genral Hospital/ወልዲያ አጠቃላይ ሆስፒታል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Woldia Genral Hospital/ወልዲያ አጠቃላይ ሆስፒታል:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram