Chief medical and Health Offecer, Distt-Barwani

Chief medical and Health Offecer, Distt-Barwani Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Chief medical and Health Offecer, Distt-Barwani, Barwani.

23/09/2022

ጋብቻ ሳይመሰረት እንደ ባልና ሚስት መኖር ምን ማለት ነዉ ❓ ከጋብቻ ጋር ምን ልዩነት አለዉ ❓



💥🇪🇹

🎯 #ተጨማሪ ሰነዶች በPDF ለማግኘት 👇
👉 t.me/joinchat/AAAAAExPP_EV3XyLKhhCpw ✅
👉 t.me/joinchat/AAAAAExPP_EV3XyLKhhCpw ✅

🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹


#ጠበቃ #ሕግ #ሳሙኤልግርማ #ህግ #ጠበቃሳሙኤል
#ጠበቃሣሙኤል #ሣሙኤልግርማ
0911-190-299

#ሀበሻ

23/09/2022

የዋስትና ውል | ለሠራተኛ ተያዥ የሚያገለግል 🇪🇹
ሳሙኤል ግርማ
የሕግ አማካሪና ጠበቃ

🛑 በቴሌግራም ይቀላቀሉን 👇👇
👉 t.me/joinchat/AAAAAExPP_EV3XyLKhhCpw
👉 t.me/joinchat/AAAAAExPP_EV3XyLKhhCpw

#ጠበቃ #ሕግ #ሳሙኤልግርማ #ህግ #ጠበቃሳሙኤል #ሀበሻ 🇪🇹 +251-911-190-299 🇪🇹

21/09/2022

ዲያቆን ድንግል ያልሆነችውን ሴት ማግባት ይችላል?

የዲያቆን ጋብቻን በተመለከተ የእኔ ድንግልና ለአንቺ ይበቃል የሚል ሐሳብ ያላቸው ሰዎች አሉ። ይህ ንግግራቸው እንደ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ እንዴት ይታያል። ዲያቆን ድንግልና የሌላትን ሴት ማግባት ይችላል? ድንግልና የሌላት ሴት ቢያገባስ በክህነቱ መቀጠል ይችላል?

ካህን የሚለው ቃል አገልጋይ የሚል ትርጉም አለው። እንደ ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ የክህነት ደረጃዎች በሦስት ይከፈላሉ። ከእነዚህ የክህነት ደረጃዎች መካከል አንደኛው ዲቁና መሆኑን በክህነት ዙሪያ የተጻፉ የቤተ ክርስቲያን መጽሐፍቶችን በማንበብ የምንረዳው ጉዳይ ነው።

ዲያቆን የሚለው ቃል ዲያኮኖስ ከሚለው የግሪክ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ረዳት አገልጋይ ማለት ነው። ዲያቆን ከእርሱ በላይ ላሉት የክህነት ደረጃዎች ላይ ላሉ አባቶች የሚረዳ የሚላክ በቤተ መቅደስ የሚያገለግል የክርስቶስን ደም ለምዕመናን የሚያቀብል መንፈሳዊ አገልጋይ ነው።

ዲያቆንነት ወደ ሌሎቹ መንፈሳዊ የክህነት ደረጃዎች ለመግባት በር እንደመሆኑ መጠን ለዲያቆን የሚነገረው ሥርዓት ሁሉ ወደ ሌሎቹ የክህነት ደረጃዎች መወጣጫ መሰላል መሆኑን ማወቅ ይገባናል። ዲያቆን ሳይሆኑ ቅስና ቁምስና ከዚህም በላይ ያሉ መንፈሳዊ የአገልግሎት ደረጃ ላይ መድረስ አይቻልም። በመሆኑም ዲያቆን ወደ ሚቀጥለው መንፈሳዊ ማዕረግ ለማደግ ወይ ሊመነኩስ ወይም ሊያገባ ያስፈልገዋል። ጋብቻን ከመረጠና በዚህ መንፈሳዊ ተቆም /ትዳር/ ውስጥ ሁኖ እግዚአብሔር ማገልገል ከፈለገ ጋብቻውን እንደ እንደ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ሊመሰርት ይገባዋል።

ጋብቻን በተመለከተ ለካህናት የተሰራው ሥርዓት ለምዕመናን ከተሰራው ሥርዓት ይለያል። ካህን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አገልጋይ ተንስኡ ለጸሎት እያለ ለአምልኮተ እግዚአብሔር የሚያነቃቃ ለምዕመናን የክርስቶስን ሥጋና ደም የሚያቀብል ነውና ከምዕመናን የተለየ ሥርዓት ቢሰራለት ብዙም አይገርምም። ከአገልግሎቱ ክቡርነት አንጻር ለምዕመናን የተፈቀደ ለእርሱ ይከለከላል።

ለምሳሌ ምዕመናን በሞት ምክንያት ወይም በዝሙት ሚስቶቻቸውን ወይም ባላቸውን ቢያጡ ሌላ ሁለተኛ መግባት ተፈቅዶላቸዋል። ይህንንም ፍትሃ ነገሥት ሲናገር እንዲህ ይላል ፦ ለወንዶች ግን ተክሊል የማይደርስበት ሁለተኛ ጋብቻ ይገባቸዋል /ይፈጸምላቸዋል/። 24:901 ለካህናት ግን ሁለተኛ ጋብቻ አልተፈቀደላቸውም። አንድ ካህን ሚስቱ ብትሞትበት ሌላ ሴት ቢያገባ ከክህነቱ እንጂ ወደ ቤተ መቅደስ ለአገልግሎት አይገባም። ይህንን በተመለከተ ፍትሃ ነገሥት እንዲህ ይላል ፦ " ሁለተኛ የሚያገቡት ወንዶች ካህናት ቢሆኑ ከሹመታቸው ይሻሩ።" 24:902

ሰለዚህም የካህናት ጋብቻ ከምዕመናን የጋብቻ ሕግ ልዩ መሆኑን መረዳት ተገቢ ይሆናል። ቤተ ክርስቲያን ከመጽሐፍ ቅዱስ የቀዳችው በብሉይና ሐዲስ የተቀመመ ሥርዓት አላት። የካህናት ጋብቻንም በተመለከተ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥርዓትና ድንጋጌ አላት።

የካህናት ጋብቻን በተመለከተ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል ፦" የአምላኩም ቅባት ዘይት ቅዱስነት በላዩ ነውና ከመቅደስ አይውጣ የአምላኩንም መቅደስ አያርክስ እኔ እግዚአብሔር ነኝ። እርሱም ሚስትን በድንግልናዋ ያግባ። ባልዋ የሞተባትን ወይም የተፋታችውን ወይም ጋለሞታይቱን አያግባ ነገር ግን ከሕዝቡ ድንግሊቱን ያግባ።" (ኦሪት ዘሌዋውያን 21:12-14 ) ካህን ሰለ ክብር ክህነቱ ሲባል ድንግሊቱን እንጂ ጋለሞታይቱን (ፈት የሆነችውን) እንዳያገባ በሕግ ተከልክሏል። ሰለዚህም ዲያቆን ካህን እንደመሆኑ መጠን ከኦርቶዶክሳዊያን አንስት መካከል አንዷን መርጦ በማግባት የእግዚአብሔር ቃል እና ሥርዓት ሊያከብር ይገባዋል።

ይህንን ቃል አክብረን በሕይወታችን ልፈጽመው ሲገባን አንዳንድ ዲያቆናት ግን " የእኔ ድንግልና ለአንቺ ይሆናል" በማለት ከዚህ የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ፈቀቅ ለማለት የግል ፍልስፍናቸውን በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ሲያራምዱ ይሰማሉ። በእውነት ይህ ስንፍና ነው የሥጋ ሐሳብን ለመፈጸም ይህንን ያህል መድከም ሳያንስ ከቤተ ክርስቲያን ሥርዓት የወጣን ሐሳብ የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት አስመስሎ መናገር ስንፍና ካልተባለ ሌላ ምን ይባላል?

እነዚህ ሰዎች ያነሱት ሐሳብ የግል ፍልስፍናቸው ቢሆንም በዚህ ሐሳባቸው የሚሳብ ይኖራልና ላነሱት ሐሳብ እንደ የቤተ ክርስቲያን የድንግልና አስተምህሮ መሰረት በማድርግ ምላሽ ልንሰጣቸው ይገባናል።

በግዙፍ ያለ ድንግሌ ሥጋ አንድ ብቻ ነው። ድንጋሌ ሥጋ አንዴ በኃጢአት ምክንያት ከጠፋ እንደ ተሰበረ የሸክላ እቃ እንደ ሞተ ሰው ነው። በባሕታዊ ጸሎት በፓትርያርክ ብራኬ እንኳን አንመለስም። ታዲያ በምን ምክንያት ነው የሥጋ ድንግልና የሌላት ሴት ድንግል ከሆነ ዲያቆን ጋር በመጋባቷ ብቻ ድንግል ሳትሆን ለደናግልና የሚፈጸመው ተክሊል የሚፈጸምላት? የዲያቆኑስ ድንግልና በምን ሒሳብ ነው ለእርሷ የሚሆነው?

ድንግልና የግል ሩጫ ነው። ቤተ ክርስቲያን ይህንን የንጽሕና ሩጫ እስከ ጋብቻ ድረስ የጠበቀ ልጇን ተክሊል ሸልማ ታከብረዋለች እንጂ የአንተ ድንግልና ለምታገባት ሚስትህም ይበቃል የሚል አስተምህሮ የላትም። የአንዱ ድንግልና ለሌላዋ ይሆናል የሚል የመጽሐፍ ምስክርም የለም። ይልቁንም ድንግልና የግል እንጂ ለሌላው የምናጋራውም አለመሆኑን ፍትሃ ነገሥት እንዲህ ሲል ይመሰክራል ፦ " የሚያገቡ ፈቶች ቢሆኑ ተክሊል አያድርጉላቸው። ይህ ተክሊል በጋብቻ ጊዜ ለድንግል ወንድና ለድንግል ሴት ይገባቸዋልና። ከሚያገቡት አንዱ ድንግል ቢሆን ብቻውን ይባረክ።" 24:906

በዚህ የፍትሃ ነገሥት አንቀጽ ወደ ቤተ ክርስቲያን ጋብቻ ለመፈጸም ሦስት አይነት ጥንዶች እንደሚመጡ መረዳት እንችላለን። የመጀመሪያዎቹ ሁለቱም ድንግልና የሌላቸው ሲሆኑ ለእነዚህ ጥንዶች ቤተ ክርስቲያን ተክሊል ሳይሆን የማአስባን የጋብቻ ሥርዓት እንዲፈጸምላቸው ያዛል። ሁለተኞቹ ደግሞ ሁለቱም ድንግልና ያላቸው መሆናቸውን ጠቅሶ " ይህ ተክሊል በጋብቻ ጊዜ ለድንግል ወንድና ለድንግል ሴት ይገባቸዋልና" ብሎ ለእነዚህ ደናግላን ጥንዶች ተክሊል እንዲፈጸምላቸው ይደነግጋል።

በሦስተኛ ደረጃ አንዱ ድንግል ሁኖ ሌላይቱ ድንግል ባትሆን የእርሱ ድንግልና ለእርሷም ይሆናልና ተክሊል ለሁለቱም ይፈጸምላቸው አይልም። የሚለው "ከሚያገቡት አንዱ ድንግል ቢሆን ብቻውን ይባረክ።" ከጥንዷቹ መካከል ድንግል የሆነ በተክሊል ጸሎቱ ተባርኮ ያግባ በማለት የድንግልና ብድር እንደሌለ ያስገነዝባል።

ሰለዚህ ምክንያት እየፈለግን የአባቶቻችን የድንበር ምልክት ከምናፈርስ ዲያቆን ድንግልና ያላትን ያግባ የሚለውን የቤተ ክርስቲያንም ሥርዓት አጥብቀን እንያዝ።

ወስብሃት ለእግዚአብሔር

ቴሌ ግራም 👉 https://t.me/Abelltefera

20/09/2022

ተጨማሪ መረጃዎችን በቴሌግራም ይከታተሉ 👇👇
👉 t.me/+RWRJyXhToJr7bgzI
👉 t.me/+RWRJyXhToJr7bgzI

20/09/2022
18/09/2022
18/09/2022

Address

Barwani

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Chief medical and Health Offecer, Distt-Barwani posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram