16/03/2026
#⤵️
ለይለቱል ቀድር🌹🌹🌹
አሏህ በቁርአኑ በሱረቱል ቀደር ላይ እንዲህ ብሏል፦
إِنَّا أَنْزَلْنَاهُ فِي لَيْلَةِ الْقَدْرِ)) القدر: ١))
እኛ (ቁርኣኑን) በመወሰኛይቱ ሌሊት አወረድነው፡
وَمَا أَدْرَاكَ مَا لَيْلَةُ الْقَدْرِ)) القدر: ٢))
መወሰኛይቱም ሌሊተ ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?🇪🇹
لَيْلَةُ الْقَدْرِ خَيْرٌ مِنْ أَلْفِ شَهْرٍ)) القدر: ٣))
መወሰኛይቱ ሌሊት ከሺሕ ወር በላጭ ናት፡፡
تَنَزَّلُ الْمَلَائِكَةُ وَالرُّوحُ فِيهَا بِإِذْنِ رَبِّهِمْ مِنْ كُلِّ أَمْرٍ)) القدر: ٤))
በርሷ ውስጥ መላእክትና መንፈሱ በጌታቸው ፈቃድ በነገሩ ሁሉ ይወርዳሉ፡፡
سَلَامٌ هِيَ حَتَّى مَطْلَعِ الْفَجْرِ)) القدر: ٥))
እርስዋ እስከ ጎህ መውጣት ድረስ ሰላም ብቻ ናት፡
በዚህ አያ ለይለቱል ቀድር ከሺ ወራቶች በላይ በላጭ እንደሆነች ተገልፃል። ታዲያ ማነው ከእኛ መካከል ይችን ሌሊት በኢባዳ በማሳለፍ የዚችን ሌሊት ሙሉ በረካዋን ለማግኘት የሚተጋ?🌿
በሶሂህ ሙስሊም በተዘገበው ሐዲስ ነብዩ(ﷺ) በመጨረሻዎቹ አስር ሌሊቶች ለይለቱል ቀድርን ሻቱ (ፈልጉ) ብለዋል።
በመጨረሻዎቹ የረመዷን ምሽቶች አብዝተን ቁርአን መቅራት ፣ አሏህን ማውሳት እና ዱአ ማብዛት ይኖርብናል። ምክኒያቱም የመጨረሻዎቹ አስር ቀናት ሶደቃ ወይም ዘካ የምንሰጥበት ፣ ነፍስያችነን የምንመረምርበት ፣ ዱአ አብዝተን የምናደርግበት ፣ መሃርታን የምንለምንበት ፣ ፆማችነን ሙሉ የምናደርግበት ጊዜ ነውና።
በመጨረሻዎቹ አስር ቀናት ጥረታችነን ወይም ኢባዳችነን እጥፍ እናደርግ ዘንድ አሏህ(ሱ.ወ.ተ) የለይለቱል ቀድር ቀን መቼ እንደሆነ ደብቆታል።
ነብዩ(ﷺ) በለይለቱል ቀድር አምኖበትና ከአሏህ ምንዳ እንደሚያገኝ ተስፋ አድርጎ ለሶላት የቆመ ሰው ያለፉት ወንጀሎቹ ሁሉ ይማሩለታል ብለዋል።🌾
በሰኺህ ሙስሊም በተዘገበው ሐዲስ ነብዩ (ﷺ) ከሌላው ጊዜ በበለጠ በመጨረሻዎቹ አስር ሌሊት በኢባዳ ላይ ይተጉ ነበር።
በዚህ ጊዜ ከሰዎች ጋር ያላቸውን ግኑኝነት በመገደብ ዱአቸውን ያጧጡፉ ነበር። ነብዩ(ﷺ) ይህን ያደርጉ የነበረው ልባቸው የበለጠ አሏህ ጋር እንዲሆንና ህሊናቸውን ከአለማዊ ጉዳይ ለማላቀቅ ነበር።🍁
በቡኻሪ በተዘገበው ሐዲስ የረመዷን የመጨረሻዎቹን አስር ቀናት መጀመሩን ተከትሎ ነብዩ(ﷺ) ጠንክረው ይሰራሉ፤ ሌሊቱን ሙሉ ሶላት ይሰግዳሉ። ቤተሰባቸውንም ለሶላት ይቀሰቅሱ ነበር።🌹🌹🌹