26/06/2024
አስደሳች ዜና
በኢትዮጲያ የመጀመሪያ የሆነው የሙሉ ዳሌ መገጣጠሚያ ቅየራ ከፍተኛ ቀዶ ጥገና በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በኘራይቤት ዊንግ በተሳካ ሁኔታ ተከናወነ ።
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ሰኔ 19/2016 ዓ.ም
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በሚሰጠው ዘርፈ ብዙ የጤና አገልግሎት በርካታ የማህበረሰቡ ክፍልን እያገለገለ ይገኛል።
በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ከዚህ በፊት በኘራይቤት ዊንግ የመሉ ዳሌ እና ጉልበት መገጣጠሚያ ቅየራ ከፍተኛ ቀዶ ጥገና መጀመሩ ይታወሳል
በዛሬው እለትም በኢትዮጲያ የመጀመሪያ የሆነው የሙሉ ዳሌ መገጣጠሚያ ቅየራ ከፍተኛ ቀዶ ጥገና በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በኘራይቤት ዊንግ በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል ።
ከፍተኛ ቀዶ ጥገናውን ያከናወኑት የአጥንት ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት እና የመገጣጠሚያ ቅየራ እንዲሁም የአርትሮስኮፒ ህክምና ሰብ ስፔሻሊስት የሆኑት
ዶ/ር ሰኢድ መሃመድ ቀዶ ጥገናው የተሳካ እንደነበር ገልፀው በቀጣም አገልግሎቱን ለማግኘት የሚጠባበቁ ታካሚዎች ስለሚገኙ ስራውን በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል ።