Janmeda Health Center

Janmeda Health Center Janmeda primary Health Care Unit

 #ስኳር ያለባቸው ነፍሰ ጡር እናቶች ኢንሱሊንን ሆድ ላይ መወጋት ይችላሉን?  አብዛኛዎቹ ነፍሰ ጡር እናቶች ኢንሱሊን ሆድ ላይ ለመወጋት ይፈራሉ፣ መርፌው ጽንሱን ይጎዳዋል ብለው ይጨነቃሉ። ...
26/05/2024

#ስኳር ያለባቸው ነፍሰ ጡር እናቶች ኢንሱሊንን ሆድ ላይ መወጋት ይችላሉን?
አብዛኛዎቹ ነፍሰ ጡር እናቶች ኢንሱሊን ሆድ ላይ ለመወጋት ይፈራሉ፣ መርፌው ጽንሱን ይጎዳዋል ብለው ይጨነቃሉ። የስኳር ህመም ላለባቸው ነፍሰ ጡር እናቶች ኢንሱሊን ለመውጋት ተመራጩ ቦታ ሆድ ነው። በእርግዝና ወቅት ኢንሱሊንን ሆድ ላይ መውጋት ደህንነቱ የተጠበቀ ነው። ሆድ ኢንሱሊንን ለመውሰድ ቀላልና አመቺ ቦታ ብቻ ሳይሆን ኢንሱሊን ወደ ሰውነት በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲገባ (predictable insulin absorption rate) ስለሚረዳ ለኢንሱሊን አወሳሰድ የሚመከር ቦታ ነው። የኢንሱሊን መርፌው ለጽንሱ ምንም አይነት ስጋት አይፈጥርም ምክንያቱም ማህፀኑ ጽንሱን በበቂ ሁኔታ ከለላ ይሰጠዋል። ስለዚህ, የመጀመሪያ ጥያቄያችንን ለመመለስ, አዎ, በእርግዝና ወቅት ኢንሱሊን ሆድ ላይ መውጋት በአጠቃላይ ደህንነቱ የተጠበቀ ነው።
በእርግዝና ወቅት ኢንሱሊንን ሆድ ላይ መውጋት ደህንነት ካረጋገጥን በመቀጠል በተለያዩ የእርግዝና ወቅቶች መደረግ ስላለባቸው የተወሰኑ ምክሮችን ስናይ
1. በመጀመሪያው ሶስት ወር የእርግዝና ጊዜ (first trimester) የኢንሱሊን መርፌ በየትኛውም የሰውነት ክፍል ላይ መወጋት ይቻላል:: ከእርግዝና በፊት የነበረ ስኳር ያለባቸውና ኢንሱሊን የሚወስዱ እናቶች የመጀመሪያው ሶስት ወር የኢንሱሊን መውጊያ ቦታ ወይም ቴክኒክ ለውጥ አያስፈልግም።
2. በሁለተኛው ሶስት ወር (second trimester) ጊዜ ሲደርስ የሆድ ገጽታ መለወጥ ይጀምራል፤ ጽንሱ ያድጋል እና ሆድም እንዲሁ። ይሁን እንጂ ኢንሱሊን ሆድ ላይ መውጋት መተው አለብን ማለት አይደለም። ይልቁንስ የመርፌ መወጊያ ቦታን መጠነኛ ማስተካከያ ማድረግ ይችላሉ።በእምብርት ዙሪያ ከጽንሱ ፊት ለፊት ያለውን የሆድ ክፍል ይልቅ ጽንሱ ካለበት በደንብ ራቅ ብለን ከጎን ያሉት የሆድ ክፍሎች ኢንሱሊንን ለመወጋት መጠቀም ይቻላል።
3. በመጨረሻ ሶስተኛው ወር (third trimester) ልጁ እያደገ የመርፌ መወጊያ ቦታ እየጠበበ ይሄዳል እንዲሁም ቆዳ በሆድ ላይ በጣም ጥብቅ ሊል ይችላል። እንዳንዴ ለኢንሱሊን መርፌ መወጊያ የሚሆን ምቹ ቦታ ማግኘት ሊከብድ ይችላል። እንዲህ ሲያጋጥም አይጨነቁ ፣ መፍትሄ አለ ።
መምረጥ ያለብን ቦታ በጎን የሆድ ክፍል ያለውን መሆን አለበት። ቦታውን በአውራ ጣት እና ጠቋሚ ጣት መሀል ቆንጠጥ በማድረግ ቆዳውን ትንሽ በማንሳት መወጋት ይቻላል:: ከሆድ ጋር ጥብቅ ያለውን ሳይሆን በጣቶች መሃከል ላይ ቆዳን ከፍ ማድረግ የሚቻልበት ቦታ በሆድ ጎን ላይ ያግኙ። ከዚያም መርፌውን ከቆዳ በ90 ዲግሪ ቀጥታ አስገብቶ መውጋት ይቻላል።
ይህ ዘዴ ምቹ እና ውጤታማ ሲሆን የኢንሱሊን መርፌን ለመወጋት ተመራጭ መንገድ ነው። ከተገኘ በጣም አጭር የኢንሱሊን መርፌ (በ4 ሚሊ ሜትር) መጠቀም ጥሩ ነው። ይህን የማይመርጡ እና ጽንሱን እንዳልውጋው የሚል ከፍተኛ ፍርሃት ያለባቸው እናቶች እንደአማራጭ ክንድ፣ ታፋ ወይም መቀመጫ ላይ ሊወጉ ይችላሉ።

30/01/2024
የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ፖሊሲ አቅጣጫ፣  የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ሪፎርም እና ስታንዳርድ  እንዲሁም በጤናው ዘርፍ የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ  ረቂቅ ማዕቀፍ ላይ የምክክር መድረ...
28/01/2024

የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ፖሊሲ አቅጣጫ፣ የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ሪፎርም እና ስታንዳርድ እንዲሁም በጤናው ዘርፍ የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ረቂቅ ማዕቀፍ ላይ የምክክር መድረክ ተካሂዷል።
___________

የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ፖሊሲ አቅጣጫ፣ የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ሪፎርም እና ስታንዳርድ እንዲሁም በጤናው ዘርፍ የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ረቂቅ ማዕቀፍ ላይ የጤና ሙያ ማህበራት፣ አጋር ድርጅቶች ፣ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት እና የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር የምክክር መድረክ ተካሂዷል።

መድረኩ የተካሄደው በብቃትና ምዘና ሪፎርም ላይ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ሲሆን በተቋሙ የተዘጋጀውን የጤናው ዘርፍ ብቃት ምዘና ማረጋገጫ ረቂቅ ማዕቀፍ ላይ ተጨማሪ ግብዓት ለማሰባሰብ መሆኑ ታውቋል።

በጤና ሚኒስቴር የብቃትና የሰው ሀብት አስተዳደር ስራ አስፈጻሚ አቶ ሀብታሙ ደምሴ መድረኩን ባስጀመሩ ጊዜ እንደተናገሩት መንግስት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም እንደ አንድ አጀንዳ ይዞ እየሠራ ነው። ከሪፎርሙ ሰባት ምሶሶዎች መካከል አንዱ የሆነውን የሲቪል ሰርቪስ የብቃት ማረጋገጫ ሪፎርም፣ ተወዳዳሪና ብቁ የሆነ ሠራተኛ በተገቢው ቦታ ተመድቦ የሚፈለገው ዓይነት አገልግሎት መሥጠት እንዲችል እንዲሁም ሠራተኛውን የማብቃት አላማ ያደረገ ነው።

አቶ ሀብታሙ የጤና ዘርፍ የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕቀፍ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር በመድረግ ላይ መሆኑን ጠቅሰው በዚህ መድረክ የጤና ሙያ ማህበራት፣ አጋር ድርጅቶች፣ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት እንዲሁም የስራና ክህሎት ሚኒስትር በማዕቀፉ ዙርያ ትክክለኛ ግንዛቤ እንዲይዙ እና የሚሰጡትን ግብዕት በመሰብሠብ የማዕቀፍ ሠነዱን ለማዳበር ታስቦ መድረኩ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።

አቶ ሀብታሙ የባለድርሻ አካላቱ የጋራ ግንዛቤ በመጨበጥ ለረቂቅ ማእቀፉ ግብአት የሚሆኑ አስተያየቶች እንዲሰጡ ጠይቀዋል፡፡

በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የመንግስት ሠራተኞች ብቃትና ምዘና ስራ አመራር ፕሮጀክት ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ይማነ ሀይሉ ከተሳታፊዎች በተነሱ ሃሳቦች ላይ ማብራሪያ በሠጡበት ጊዜ እንደተናገሩት የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ሪፎርም ጉዳይ በፈተና የመውደቅና የማለፍ ጉዳይ ሳይሆን የመፈጸም አቅም ጉዳይ ነው። የፈጻሚውን የብቃት ክፍተት የመለየት፣ በአፈጻጸም የሚታይ ክፍተትን በስልጠና የመሙላት አላማ ያለው መሆኑን አስረድተዋል።

የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ፖሊሲ አቅጣጫ፣ የብቃት ምዘና ማረጋገጫ ሪፎርም እና ስታንዳርድ እንዲሁም በጤናው ዘርፍ የሰው ሀብት ብቃትና ምዘና ማረጋገጫ ረቂቅ ማዕቀፍ በመድረኩ የቀረቡ ሠነዶች ሲሆኑ ሠፋ ያለ ውይይት ተደርጓባቸዋል።

24/12/2023
24/12/2023

በኢትዮጵያ የመጀመርያው የአንጎል የደም ስር “ክሊፒንግ” በስኬት ተከናወነ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያው ነው የተባለለት የአንጎል የደም ስር “ክሊፒንግ” በተሳካ ሁኔታ መከናወኑ ተገለጸ፡፡

ሕክምናው የተደረገላቸው ታካሚ ድንገት በዕለት ሥራቸው ላይ ሳሉ ከፍተኛ የራስ ሕመም ይሰማቸው እንደነበረና ከዚያም እራሳቸውን ስተው መውደቃቸውን የህክምና ታሪካቸው ያስረዳል።

ሕክምና ተቋም እንደደረሱም በተደረገላቸው ምርመራ በአንጎላቸው ውስጥ የደም ቧንቧ መፈንዳት ምክንያት የደም መፍሰስ እንደተከሰተና የፈነዳውን የደም ቧንቧ በቀዶ ጥገና ሕክምና ባስቸኳይ ካልተስተካከለ ለሞት የሚዳርጋቸው እንደነበረም ተነግሯል።

በሆስፒታሉ “በኒውሮሰርጀሪ” ዲፓርትመንት አስተባባሪነትና የአንጎል ደም ቧንቧ ቀዶ ጥገና ሕክምና ከፍተኛ ልምድ ባካበቱት ዶክተር ቶማስ ቦጋለ የተመራ የሕክምና ቡድን ባካሄደው ቀዶ ህክምና ታካሚዋ የተስተካከለ የአንጎል የደም ዝውውር እንዲኖራቸው ማድረግ እንደተቻለ ተገልጿል፡፡

ታህሳስ 10 ቀን 2016 ዓ.ም የተካሄደው ይህ የተሳካ ቀዶ ህክምና ሶስት ሰዓት ተኩል መፍጀቱም ተነግሯል።

ከዶክተር ቶማስ በተጨማሪ ዶክተር መሃሪ፣ ዶክተር ፒኔል፣ ዶክተር ዳዊት፣ ዶክተር ብዙአየሁ፣ ነርስ ኢብራሂም፣ ሲስተር ሶስና እና ሲስተር መንበረ፣ እንዲሁም ዶክተር ቦንሳ፣ ዶክተር ማህደር፣ ዶክተር እየሩስ፣ ዶክተር ውበት የተባሉ የህክምና ባለሙያዎች በሂደቱ መሳተፋቸው ተጠቅሷል፡፡

ሕክምናው ከዚህ ቀደም በሀገር ውስጥ ደረጃ በመንግስት ሆስፒታሎች ሲሰራ የመጀመሪያው መሆኑንም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

ታካሚዋ በተደረገላቸው ሕክምና እንደተደሰቱ በመግለጽ ባሁኑ ወቅት ከሕመማቸው አገግመው ወደ ቤታቸው ተመልሰዋል ተብሏል፡፡

24/12/2023

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Janmeda Health Center posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram