25/04/2026
ቤቴል ሜዲካል ኮሌጅ ተማሪዎቹን በዓድዋ ድል መታሰቢያ አስመረቀ!
አዲስ አበባ - በጤናው ዘርፍ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የማስተማር ልምድ ያለው ቤቴል ሜዲካል ኮሌጅ በዛሬው እለት በዓድዋ ድል መታሰቢያ ተማሪዎቹን አስመርቋል፡፡ የ20ኛ ዙር የምረቃ ስነ-ሥርዓቱን ያከናወነው ኮሌጁ፣ በአጠቃላይ 92 ተማሪዎችን ለምርቃት ያበቃ ሲሆን በሜዲሲን፣ በነርሲንግና በሕዝብ ጤና (Public Health) ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመርቋል፡፡
ከተመራቂዎቹ መካከል 42ቱ በሜዲሲን፣ 32ቱ በነርሲንግ እንዲሁም ቀሪዎቹ 17 ተማሪዎች በሕዝብ ጤና (Public Health) ዘርፍ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ናቸው። ለተመራቂዎች እንዲሁም ለተመራቂ ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ:: 🎉