Akaki kality Executive werda 9 youth lege

Akaki kality Executive  werda 9 youth lege "Akaki kality w_9 youths League_ብልፅግና"

"የተከልናቸዉን ችግኞችን የማንከባከብ ግዴታችንን እንወጣለን"          ወጣት ማቴዎስ ጌታቸውበቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ከከተማ ዉበት እና አረንጕዴ ልማት ጽ/ቤት ...
11/11/2023

"የተከልናቸዉን ችግኞችን የማንከባከብ ግዴታችንን እንወጣለን"

ወጣት ማቴዎስ ጌታቸው

በቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ከከተማ ዉበት እና አረንጕዴ ልማት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በመንገድ አካፋይ የተተከሉ ችግኞችን የማንከባከብ ተግባር አከናዉነዋል።

ህዳር 1/3/2016ዓ.ም

በፕሮግራሙ ከ12ቱም ወረዳ የተወጣጡ የሊጉ አባላት የተገኙ ሲሆን ችግኞች በፀሐይ እንዳይደርቁ ለማድረግ ዉሃ የማጠጣት እና አረምን የማረም ስራ ተሰርተዋል::

የአቃቂ ቃሊቲ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ ወጣት ማቴዎስ ጌታቸው እንደገለፀው ወጣቱ ኃይል የተተከሉ ችግኞችን በማንከባከብ ዓርአያ መሆን አለበት ብለዋል:: ወጣት ማቴዎስ አክለዉም ብልፅግና ፓርቲ ከወጣቶች ጋር በመሆን የተለያዩ ዉጥኖችን እስከ ግብ ለማድረስ አቅዶ እየሰራ ይገኛል በማለት ገልፀዋል:: ከዚህ አኳያ የአረንጕዴ አሻራ ስራ ዉጤታማ እንዲሆን በየአከባቢ የሚገኘው ወጣት የበኩሉን አወንታዊ አስተዋፅዖ እንዲያደርግም ጥሪ አስተላልፈዋል::

በእለቱም የከተማ ዉበት እና አረንጕዴ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው በላይ በእግድነት የተጋበዙ ሲሆን በክረምት መርሀ ግብር የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብና ውሀ በማጠጣት ከተማችንን እንደ ስሟ ውብ ማድረግ የሁላችንም ሀላፊነት ነው ብለዋል::

"Biqiltuuwwan dhaabne kunuunsuun dirqama keenya haa baanu!"

Dargaggoo Maatiwoos Geetaachoo

Liigiin Dargaggoo Badhaadhinaa Kutaa Magaala Aqaaqii Qaallittii waajjira Magariisuu fi Miidhagina Magaalaa waliin ta'uun sagantaa kunuunsa biqiltuuwwan walakkessa daandiitti dhaabamanii raawwataniiru

Sagantaa kana irratti miseensonni Liigichaa Aanaawwan 12 irraa walitti bobba'ani kan hirmaatan yoo ta'u, biqiltoota bishaan obaasuun kunuunsaniiru.

Walitti qabaa Liigii Dargaggoo Kutaa Magaalichaa Obbo Maatiwoos Geetaachoo ergaa dabarsaniin,dargaggoonni biqiltoota dhaabuu qofa osoo hin taane kunuunsuu irrattis fakkeenya adda duree ta'uu qaba jedhaniiru.
Paartiin Badhaadhinaa dargaggoota waliin karoorfatee hojiiwwan hedduu galmaan gahuuf kan hojjetu ta'uu eeranii,kaayyoon Ashaaraa magariisaa akka milkaa'u dargaggoonni nannoo jiran hundatti shoora isaanii akka bahan waamicha dabarsaniiru.

Dura bu'aan waajjira Magariisummaa fi miidhaginaa Kutaa Magaalaa Aqaaqii Qaallittii Obbo Geetaachoo Balaay saganticha irratti argamuun, biqiltoota yeroo gannaa dhaabaman bishaan obaasuun,aramuufi kunuunsuun miidhagina Magaalaa eeguun qoodha hunda keenyaati jechuun ergaa dabarsaniiru.

Akaki kality prosperity

09/09/2022

አዲሱ ዓመት ኢትዮጵያውያን ያጋጠሟቸውን ፈተናዎች በአንድነት የሚያልፉበት እንደሚሆን እምነታችን ነው - የሀገራት አምባሳደሮች

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲሱ ዓመት ኢትዮጵያውያን ያጋጠሟቸውን ፈተናዎች በማለፍ ለሰላምና ልማት በአንድነት የሚሰሩበት እንደሚሆን ያላቸውን እምነት ተቀማጭነታቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች ገለጹ፡፡

ተቀማጭነታቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች ለኢትዮጵያውያን የመልካም አዲስ ዓመት ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

አምባሳደሮቹ በመልዕክታቸው÷ ኢትዮጵያውያን በመጪው አዲስ ዓመት በተባበረ መንፈስ አንድነቷ የተጠበቀ ጠንካራ ሀገርን ለማስቀጠል የሚሰሩበት እንደሚሆን እምነታችን ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተርክሂን አዲሱ ዓመት ለመላ ኢትዮጵያውያን የሰላም፣ የጤና፣ የብልጽግና፣ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆን የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላልፈዋል።

ኢትዮጵያውያን ያገጠሟቸውን ፈተናዎች በብቃት የመወጣት አቅም ያላቸው ህዝቦች ናቸው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

በኢትዮጵያ የኢንዶኔዥያ አምባሳደር አል ቡሲራ ባስኑር በበኩላቸው÷ አዲሱ ዓመት ኢትዮጵያውያን ያላቸውን መልካም ገጽታና እሴት የሚያስተዋውቁበትን አጋጣሚ እንደሚፈጥር አንስተዋል፡፡

በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በጋራና በትብብር መንፈስ የተሻለች ሀገር እንዲገነቡ እድል እንሚፈጥርም አመላክተዋል፡፡

“የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ኢትዮጵያውያን አዲስ ተስፋ የሚሰንቁበት ጊዜ ነው” ያሉት ደግሞ በኢትዮጵያ የአየር ላንድ አምባሳደር ኒኮላ ብሬናን ናቸው።

ዓመቱ የኢትዮጵያውያን ሰላምና መረጋጋትን እንዲሁም አንድነታቸውን ይበልጥ የሚያጠናክሩበት እንዲሆን ያላቸውን መልካም ምኞት ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ የጀርመን ኤምባሲ ምክትል ኃላፊ ሄይኮ ኒትስሽኬ ÷በአዲሱ ዓመት የተሟላ ሰላምና መረጋጋት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ማየት ምኞታቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያውያን በአዲሱ ዓመት ሀገራቸውን በተባባረ ክንድ ወደ ተሻለ ፖቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የሚያሸጋግሩበት እንዲሆንም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

በተመሳሳይ በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ኢቶ ታካኮ÷ አዲሱ ዓመት ለመላ ኢትዮጵውያን የሰላምና የብልጽግና እንዲሆንላቸው የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላልፈዋል።

30/08/2022
25/08/2022
24/08/2022

የትግራይ ህዝብ ችግሮችን ለመፍታት ሰላማዊ አማራጭ ዛሬም፤ ነገም ብቸኛዉ መፍትሄ ነዉ!

መንግስት ተገዶ የገባበትን የሰሜኑን ጦርነት በሰላም ለመቋጨት ያስችላሉ ያላቸውን እርምጃዎች ሲወስድ መቆየቱ ይታወቃል። የሽብር ቡድኑ ህወሃት ከወረራቸው የአማራና የአፋር አብዛኞቹ አካባቢዎች ተገፍቶ እንዲወጣ ከተደረገ በኋላ መንግስት፤

• ሙሉ የሰራዊትና ሎጂስቲክስ አቅም እያለው ወደ ትግራይ ክልል ከመግባት መቆጠቡ

• የተሳለጠና ያልተቋረጠ የሰብአዊ ድጋፍ ወደ ትግራይ ክልል እንዲገባ የተናጠል ተኩስ አቁም ማድረጉና ምቹ ሁኔታን መፍጠሩ

• ለሰላም በር ይከፍታል በሚል እስረኞችን መፍታቱ

• የሰላም አማራጭንም አሟጦ ለመጠቀም እንዲቻል የሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴን በይፋ ወደ ስራ አስገብቶ ግልጽ አቅጣጫንም ማስቀመጡ

• አስፈላጊ የሆኑ መሰረታዊ ቁሳቁሶች ወደ ትግራይ እንዲጓጓዝ ማድረጉ

• በአሸባሪዉ ቡድን የወደሙ አገልግሎት መስጫዎችን በመጠገን በሶስተኛ ወገን በኩል ስራ ለማስጀመር እንቅስቃሴ እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡

ሆኖም አሸባሪው ቡድን ከውጪ ደጋፊዎቹ ጋር በመሆን ጦርነቱን የመቀጠል ከፍተኛ ፍላጎትን ሲያንጸባርቅ ቆይቷል፡፡
ከበባውን እንሰብራለን፣ መተማመኛችን ክንዳችን ነው፣ የትግራይ መሬቶች ተወረዋል፣ እናስለቅቃለን፣ ወዘተ በሚል ፉከራ ታጅበው ባለፉት ስድስት ወራት የተለያዩ ትንኮሳዎችን ሲያደርጉ ቆይተዋል። በምዕራብ በኩል በተደጋጋሚ ሞክረው ሽንፈትን እየተከናነቡ ተመልሰዋል።

በደቡብ ትግራይ በኩልም ተደጋገሚ ሙከራ ቢያደርጉም መንግስት ሙከራቸውን እያከሸፈ ዋናው መፍትሔ የሰላም መንገዱ ነው በሚል ጉዳዩ እንዳይባባስ አድርጓል።

ሆኖም ከመንግስት በኩል የቀረቡለትን በርካታ የሰላም አማራጮች ሁሉ ወደጎን በመተው የሽብር ቡድኑ ህወሃት ታጣቂ ቡድን ሰሞኑን ሲፈጽም የሰነበተዉን ትንኮሳ ገፍቶበት ዛሬ ንጋት ላይ በምስራቅ ግንባር በቢሶበር፣ በዞብል እና በተኩለሽ አቅጣጫዎች ከለሊቱ 11 ሰአት ጀምሮ ጥቃት ፈጽሟል። በወሰደዉ እርምጃም ተኩስ ማቆሙን በይፋ አፍርሷል፡፡

የፈጸመው ጥቃትም ሆነ እሱን ተከትሎ ያወጣው መግለጫ አሰቀድሞ ለትንኮሳው ሲዘጋጅ እንደነበር ግልጽ ማሳያ ነው።

ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችንና መላው የጸጥታ ሃይላችን ከሽብር ቡድኑ የተሰነዘረውን ጥቃት በተቀናጀ መልኩ በድል እየመከቱት ይገኛሉ።

የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ከአሸባሪው ቡድን ለመጠበቅም በወትሮ ዝግጁነት ሁሉም የጸጥታ ሃይላችን በተጠንቀቅ ቆሟል።

ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል እንደሚባለው ቀድሞም በተካኑበት የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ስራ ራሳቸዉ ተንኩሰዉ ራሳቸዉ እየጮሁ ይገኛሉ፡፡

ለሰላም እጁን የዘረጋዉን መንግስት በሃሰት በመወንጀል “ድርድሩ አስቀድሞ ከሽፏል” በሚል ለተለያዩ ወገኖች ጦርነቱ እንደማይቀር ሲያደርጉ የነበረዉን ቅስቀሳ በማጠናከር የትግራይን ወጣት ዳግም ሊማግዱት በይፋ አዉጀው ወደ ጦርነት እየተንደረደሩ ነዉ፡፡

ሰሞኑን አለም አቀፍ አጫፋሪዎቻቸው ካሸለቡበት ብቅ ብቅ ማለታቸውም የጦርነት ዝግጅቱን በፕሮፓጋንዳ ዘመቻ የማጀብ አካል መሆኑ ግልፅ ሆኗል።

ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የትግራይን ወጣት ለማስጨረስ ሕወሓት የሚያደርገውን የጦርነት ጉሰማ እንዲያቆም ጠንካራ ግፊት ማድረግ ይኖርበታል፡፡
በሃገር ውስጥም ሆነ በመላው አለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ከዚህ የጥፋት ሃይል የሚሰነዘረውን ጥቃት ለመመከትና ኢትዮጵያን የመበተን ግልጽ አላማ የያዘውን ይህንን የሽብር ቡድን የጥፋት ሙከራ ለማምከን በጋራ እንድንቆም መንግስት ጥሪውን ያቀርባል።

የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጥያቄ መፍትሄ ማግኘት የሚችለው በሰላማዊ መንገድ ብቻ መሆኑን በመገንዘብ ዛሬም ነገም የሰላም አማራጭ የመጀመሪያ መፍትሔ እንደሆነ መንግሥት ፅኑ እምነት አለዉ፡፡

ሆኖም አሸባሪዉ የሕወሓት ቡድን በትንኮሳው ከገፋበት፤ መንግስት ሀገር የማዳን ሕጋዊ፣ ታሪካዊና ሞራላዊ ግዴታ ስላለበት እንዲሁም የሽብር ቡድኑ ወደደም ጠላም ወደ ሰላም አማራጭ እንዲመጣ ለማድረግ አስፈላጊውን እርምጃ ሁሉ ይወስዳል፡፡

ይህንን ለማስፈፀም ደግሞ መንግስትና መላው የፀጥታ ሃይላችን ከነሙሉ ብቃትና ቁመናቸዉ በተጠንቀቅ ላይ ናቸው።

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

25/07/2022
21/07/2022
21/07/2022
16/07/2022

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Akaki kality Executive werda 9 youth lege posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category