22/08/2021
የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከልና ለመቆጣጣር ተሻሽሎ በወጣ መመሪያ (መመሪያ ቁጥር 803/2013) ዙሪያ የተሰጠ መግለጫ ‼️
• ለልደት፣ ምረቃ፣ማህበር፣ሀዘንን መሰረት የሚያደርጉ ዝግጅቶች (ከቀብር እና ከቀብር መልስ ያሉ ስነስርዓቶች ውጭ) እና መሰል በቤት ውስጥ የሚዘጋጁ ማህበራዊ በዓላት ከቤተሰብ አባላት ከሆኑ ውጭ ተጠራርቶ ማክበር የተከለከለ ነው፣
• ከላይ የተጠቀሰው እንዳለ ሆኖ ማንኛውም ሰው ከ50 በላይ የማይበልጡ ሰዎች በመሆን እና ሁለት የአዋቂ እርምጃ (ሁለት ሜትር) ተራርቆ፣ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ በማድረግ እና ተገቢውን የኮቪድ 19 መከላከያ የንጽህና እርምጃዎች በመተግበር የሰርግ ስነስርዓት ማካሄድ ይችላል፡፡
◾️የአደባባይ በዓላት አከባበርን በተመለከተ
• ህዝብን በብዛት የሚያሳትፉ የአደባባይ ላይ በዓላት የወረርሽኑ ስርጭት መረጋጋት እስኪጀምር ድረስ በታቸለ አቅም ባይደረጉ ይመከራል፣
• ማንኛውም በአደባባዮች ላይ የሚከበሩ በዓላትን የሚታደምም ሆነ አከባበሩን የሚያስተባበር ሰው የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ የማድረግ እና በአከባበርም ወቅት ሁለት ሜትር ርቀትን ጠብቆ የመቆምና መቀመጥ ግዴታ አለበት፣
• ማንኛዉም በአደባባይ የሚከበሩ በዓላትን የሚያስተባብር አካል በዓላት የሚከበሩባቸው አደባባዮች የሚሸፍኑትን ጠቅላላ ቦታ ከግምት ውስጥ በማስገባት ቦታው ሊይዝ ከሚችለው ሰው ብዛት አንድ አራተኛውን የማይበልጥ ሰው በመያዝ ስርዓቱን ማካሄድ ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል፡፡
◾️አገልግሎት የሚሰጡ እንደ ካፌዎች፣ ባርና ሬስቶራንቶች፣መጠጥ ቤቶች፣ የመዝናኛ እና መጫዎቻ አገልግሎት የሚሰጡ ስፍራዎች በተመለከተ
• በአንድ ጠረጴዛ ከሶስት ሰው በላይ ማስተናገድ የተከለከለ ሲሆን በእያንዳንዱ ጠረጴዛ መካከል የሁለት ሜትር ርቀት ሊጠበቅ ይገባል፣
• አገልግሎትን የሚሰጡ ሰዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛን የማድረግ ግዴታ አለባቸው፣
• የሚስተናገዱ ሰዎች ከሚመገቡበት እና ከሚጠጡበት ወቅት ውጭ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛን የማድረግ ግዴታ አለባቸው፡፡
◾️ሲኒማ ቤቶች፣ ቲያትር ቤቶች እና የስዕል ጋላሪ ቤቶች በተመለከተ
አገልግሎቱ የሚሰጥበት አዳራሽ ወይም ስፍራ ስፋት ከግምት ውስጥ በማስገባት ቦታው ሊይዝ ከሚችለው ሰው ብዛት አንድ አራተኛውን የማይበልጥ ሰው በመያዝ፣ ሁለት የአዋቂ እርምጃ (ሁለት ሜትር) በማራራቅ እና የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ በማስደረግ አገልግሎቱን መስጠት ይኖርባቸዋል፡፡
◾️ስፖርታዊ ውድድሮች በተመለከተ
• ማንኛዉም የስፖርት ዉድድር የስፖርት ዉድድሩ ስፍራ የሚይዘው የታዳሚ ብዛት ታሳቢ በማድረግ ከአንድ አራተኛዉን ታዳሚ የማይበልጥ እንዲታደም በማድረግ ማከናወን ይቻላል፣
• እነዚህ ውድድሮች ወረርሽኙን ባገናዘበ መልኩ መከናወን መቻላቸውን በማረጋገጥ ፈቃድ የመስጠት እና በውድድር ወቅቶችም የጥንቃቄ እርምጃዎች የማይተገበሩ ከሆነ አስፈላጊውን እርምጃ የመውሰድ ኃላፊነት አግባብ ባላቸው የመንግስት አካላት የሚፈጸም ይሆናል።
በከፍተኛ ሁኔታ ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚገኙባቸው ተቋማት ላይ የተጣሉ ክልከላዎች እና መደረግ ያለባቸው
◾️የጥንቃቄ እርምጃዎች በተመለከተ
• የወረርሽኙ ስርጭት ያለበት ሁኔታ በየጊዜው እየታየ በሌላ መመሪያ እስኪወሰን ድረስ በሚከተሉት ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ሰዎችን በአካል መጠየቅ የተከለከለ ነው:: ነገር ግን እርዳታ ሰጭዎች ከተቋሙ አስተዳደር ድረስ በመቅረብ ማንኛውንም ድጋፍና መሰል ተግባራትን ማድረግ ይችላሉ
i. የአረጋዊያን መጦሪያዎች ስፍራዎች እና
ii. የማገገሚያ ማዕከላት
• በማረሚያ ቤቶች ላይ የሚደረግ የታራሚን በአካል የመጎብኘት ሂደት በታራሚው እና በጠያቂው መሀል ሁ