Hakim Mereja ሀኪም መረጃ

Hakim Mereja ሀኪም መረጃ Sometimes take a LOSS for a bigger WIN.

ሰውነትን (አንጀትን) ዲቶክስ ማድረግ (ማጽዳት) [Body Detoxification (Cleansing)]አንጀት ይፀዳል?በምን ይፀዳል?ምን ጥቅም አለው?ባይፀዳ ምን ችግር አለው?ቢፀዳ ምን ችግር...
24/12/2025

ሰውነትን (አንጀትን) ዲቶክስ ማድረግ (ማጽዳት) [Body Detoxification (Cleansing)]
አንጀት ይፀዳል?
በምን ይፀዳል?
ምን ጥቅም አለው?
ባይፀዳ ምን ችግር አለው?
ቢፀዳ ምን ችግር አለው?
ትክክለኛውን መረጃ ካለማወቅ ከሚከሰት አደጋ ራሳችሁን ትጠብቁ ዘንድ ሙሉ መረጃውን በዩቲዩቭ ቻናላችን ላይ ታገኙታላችሁ ከታች ባለው ሊንክ ገብታችሁ ማየት ትችላላችሁ
👇🏿👇🏿👇🏿👇🏿👇🏿

...

24/12/2025

እባካችሁ በቻላችሁት አቅም ድምፅ ሁኑን በዛሬው ቀን ማለትም 14/04/2018ዓ.ም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በደቡብ ወሎ መስተዳድር ዞን በቃሉ ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ሥራ የምንሰራ የጤና ባለሙያዎች ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ የ2016ዓ.ም እና የ2017ዓ.ም የሰራንበት የዱቲ ብር ወይም የትርፍ ሰዓት ክፍያ ይከፈልን ብለን ስንጠይቅ በ2017ዓ.ም መጨረሻ እንከፍላችኅለን ተረጋጉ ብለው በጀት ዓመቱ መጨረሻ ላይ ሳይከፍሉን እንደ ህፃን ልጅ አታለሉን አሁንም በ2018ዓ.ም መንግስት ባወረደው መመሪያ መሰረት ጥቅማችን ይከበርልን እንዲሁም ወደም ሲል የክልሉ መንግስት ከዚህ በፊት ያልተከፈለ የዱቲ ከፍያ ካለም የባለፈውን አመትን ጨምሮ እንዲሁም የ2018ዓ.ም በቂ በጀት ተይዞ እንድከፈላቸው ብሎ በፃፈው ትእዛዝ እና መመሪያ መሰረት ራሳችንን እና ለሪስክ አጋልጠን የሰራንበትን የላባችንን ዉጤት ክፈሉን ብለን ብንጠይቅም ለጥያቂያችን ተገቢ እና አግባብ ያለው መልስ መመለስ ሲገባ በቀን 14/04/2018ዓ.ም የቃሉ ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት, የቃሉ ወረዳ አስተዳደር ፅ/ቤት እና የቃሉ ወረዳ ፀጥታ ፅ/ቤት በጋራ በመሆን ከደጋን ጤና አጠባበቅ ጣቢያ እና ከገርባ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ሁለት ባለሙያዎችን ለምን የሰራችሁበትን ክፈሉን ብላችሁ ትጠይቃላችሁ ሌሎች ባለሙያዎችንም የመብት ጥያቄ እንዲያነሱ ታደርጋላችሁ በማለት በፖሊስ መኪና (በፓትሮል) አፍነው ወዳልታወቀ ቦታ እስር ቤት ይዘዋቸው ሄደዋል:: መንግስት ባለበት አገር በደቡብ ወሎ መስተዳደር ዞን ስር የቃሉ ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት አመራሮች ምስኪኑን የጤና ባለሙያ እያሸማቀቁ ይገኛሉ እንደት በሕግ አግባብ መብትን የጠየቀ ባለሙያ ይታሰራል??? እንዴትስ መንግስት የሰጣቸውን ስልጣን መሰረት በማድረግ ሕግ እና ስርዓት ይከበር ብለው የሚጠይቁ ባለሙያዎችን ያስራሉ?? ስልጣን የተሰጠው ህዝብ እና መንግስትን ለማገልገል ነው እንጅ ከሕግ እና መመሪያ ዉጭ ህገ ወጥ ሥራ እንዲሰሩ ነው እንደ? እባካችሁ ለሚዲያ አዉሉልን ለደህንነት ሲባል ማንነታችን እንዳይገለፅ::የሀገር እና የወገን እንዲሁም የሙያ ግዴታችሁን እየተወጣችሁ ስለሆነ ከልብ እናመሰግናለን::

ይህንን ማንም አይነግርሽም ፤ ስለማህፀን ኢንፌክሽን ማወቅ ያሉብሽ ነገሮች ፤ መጥፎ የማህፀን ፈሳሽ ላስቸገራቸው መንስኤውና መፍትሔውን በዩቲዩቭ ቻናላችን ከታች ባለው ሊነክ በዩቲዩቭ ቻናላችን...
23/12/2025

ይህንን ማንም አይነግርሽም ፤ ስለማህፀን ኢንፌክሽን ማወቅ ያሉብሽ ነገሮች ፤ መጥፎ የማህፀን ፈሳሽ ላስቸገራቸው መንስኤውና መፍትሔውን በዩቲዩቭ ቻናላችን ከታች ባለው ሊነክ በዩቲዩቭ ቻናላችን ማግኘት ትችላላችሁ።
👇👇👇👇

🦠የማህፀን መጥፎ ፈሳሽ ከጤነኛው እንዴት መለየት ይቻላል?🦠የማህፀን መጥፎ ፈሳሽ በጊዜ ካልታከመ መካንነት ያስከትላል ፤ በቶሎ ከታከመ ግን ይድናል።🦠የማህፀን መጥፎ ፈሳሽ ምርመራው...

23/12/2025
statment from Tigray Medical Association ማሕበር ሕክምና ትግራይ   Briefing Regarding the Hitsats makeshift IDP camp Humanitarian...
23/12/2025

statment from Tigray Medical Association ማሕበር ሕክምና ትግራይ
Briefing Regarding the Hitsats makeshift IDP camp Humanitarian Crisis

A comprehensive health assessment conducted recently at the makeshift Internally Displaced Persons sites in Hitsats, a small village in the Northwestern Zone of Tigray, revealed several critical humanitarian and public health concerns. The total population in the assessed sites is estimated at 14,134 people, comprising 7,200 males and 6,943 females, organized into 4,625 households. Household leadership is nearly evenly distributed, with 2,253 males headed and 2,272 female headed households.
The assessment highlighted a substantial proportion of vulnerable populations. Children under five years of age number 4,342, while older adults above 60 years total 2,506. Of particular concern, 1,700 elderly individuals were identified as living without caregivers, indicating a severe gap in social and health support systems for this group.
In addition, the assessment identified 497 persons living with disabilities and revealed that more than 360 households are currently excluded from essential food assistance. * These findings point to critical protection, nutrition, and health service gaps that require urgent, coordinated humanitarian intervention to prevent further deterioration and loss of life at the Hitsats and other numerous makeshift IDPs camp across Tigray. (*data from the Tigray Regional Health Bureau)
Actions to Be Taken by the Tigray Medical Association
> 1. Support Vulnerable Groups
Coordinate organized meal preparation and distribution for elderly people, persons with disabilities, and others unable to prepare food independently.
> 2. Address Nutritional Gaps
Support malnutrition screening and advocate for targeted nutrition services for children, pregnant and lactating women, and other high-risk groups.
> 3. Restore Emergency Referrals
Advocate for and mobilize ambulance services to ensure timely emergency referrals from the camp.
> 4. Strengthen Health Service Delivery
Deploy medical professionals and advocate for essential medicines and supplies to maintain continuity of care.
> 5. Improve Diagnostic Capacity
Support the provision of basic diagnostic tools and point of care testing to strengthen clinical decision making.
Our association working with various stakeholders, including the Tigray Regional health Bureau to implement complementary response mechanisms that address these gaps, particularly in solutions not currently being conducted by other partners to avoid redundancy.
Stakeholders, partners, and health professionals are invited to support and collaborate with TMA.
Contact us via https://tmeda.org/
contact number +251944777711
email info@tmeda.org

የኢትዮጵያና የአሜሪካ መንግስታት በጤናው ዘርፍ ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር የ 1.6 ቢሊዮን ዶላር የጤና ትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ።————-የኢትዮጵያና የአሜሪካ መንግስታት የ 1.6 ቢሊዮን...
23/12/2025

የኢትዮጵያና የአሜሪካ መንግስታት በጤናው ዘርፍ ያላቸውን ትብብር የሚያጠናክር የ 1.6 ቢሊዮን ዶላር የጤና ትብብር ማዕቀፍ ተፈራረሙ።
————-

የኢትዮጵያና የአሜሪካ መንግስታት የ 1.6 ቢሊዮን ዶላር የጤና ትብብር ማዕቀፍ ስምምነቱ እስከ 5 ዓመት (እ.ኤ.አ ከ2026 እስከ 2030) የሚቆይ ሲሆን የትብብር ማዕቀፉ በኤችአይቪ/ኤድስ፣ ቲቢ፣ ወባ፣ የእናቶች እና ህጻናት ጤና፣ የወረርሽኝ ምላሽ እና ዝግጁነትን የነበረውን ድጋፍ ለማስቀጠል እንዲሁም የኢትዮጵያን የጤና ስርዓት የበለጠ ለማጠናከር ድጋፍ ለማድረግ ያቀደ ነው።

ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር የትብብር ማዕቀፉ ውስጥ የአሜሪካ መንግስት 1.16 ቢሊዮን ዶላር የሚያቀርብ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስትም የሀገር ውስጥ የጤናን ስርአት ፋይናንስ ለማሳደግ በያዘው ዘላቂ የፋይናንስ እቅድ መሰረት ቀሪውን ፋይናንስ የሚሸፍን ይሆናል።

የሁለቱ ሀገራት የረዥም ጊዜ የትብብር ማዕቀፉ፤ የተቀናጀና የማይበገር የጤና ስርዓትን ለማጠናከር፣ እንዲሁም የዜጎችን ጤና ለማረጋገጥ፣የጤና ባለሙያዎችን ብቃት እና ክህሎት ለማሳደግ፣ የሀገር ውስጥ የጤና ፋይናንስን እና የሃገር ውስጥ መድሀኒት አቅርቦት እና ምርትን በማሳደግ ዘላቂ የጤና ሰርእትን መዘርጋት ላይም እገዛ የሚኖረው ይሆናል።

ኢትዮጵያ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ፣ በማህበረሰብ አቀፍ ጤና እና በማህበረሰብ ጤና አገልግሎት ስኬታማ ውጤት ማስመዝገቧ በስምምነቱ ወቅት የተጠቀሰ ሲሆን የትብብር ማዕቀፍ ስምምነቱ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ክቡር አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ እና በኢትዮጵያ መንግስት በኩል በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ እና የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በተገኙበት ተፈርሟል።

NB:-
We need reform in Ethiopian health system including health professional livelihood ,health infrastructure ,health system digitalization

Ethiopian Health professionals.

22/12/2025

#ከካሳ ነፃ የቤት መስርያ ቦታ!
/ የተጋላጭነት/ ክፍያ ለሁሉም ጤና ባለሙያ!
#የነፃ ህክምና በሁሉም የሃገሪቱ ጤና ተቋማት እንዲሁም ከአገር ዉስጥ መታከም ማይቻል ከሆነ ዉጭ ሃገር ሂዶ ሚታከሙት ሁኔታ መመቻቸት አለበት።
#ጤና ባለሙያዎችን ማሳከም ግዴታ እንጂ የቅንጦት ጥያቄ አደለም!!

ጠቃሚ ጤና ነክ ትምህቶችን የምታገኙበት የዩቲዩቭ ቻናል ልጠቁማችሁ። ከታች ባለው ሊንክ በመግባት ሰብስክራይቭ አድርጉ።👇👇👇👇ጫት የሚቅሙ ወንዶች ላይ የወጣ አድስ እና አስደንጋጭ ጥናት ይፋ ሆ...
22/12/2025

ጠቃሚ ጤና ነክ ትምህቶችን የምታገኙበት የዩቲዩቭ ቻናል ልጠቁማችሁ። ከታች ባለው ሊንክ በመግባት ሰብስክራይቭ አድርጉ።
👇👇👇👇
ጫት የሚቅሙ ወንዶች ላይ የወጣ አድስ እና አስደንጋጭ ጥናት ይፋ ሆነ። ጫት የሚቅሙ ወጣቶች ላይ ያልተጠበቀ ጉዳት እያስከተለ ነው ተባለ።
👇👇👇👇

ለረጅም ጊዜ ጫት የቃሙ ወንዶች ላይ የተሰሩ ጥናቶች ይፋ እንዳደረጉት ከሆነ ለልብ በሽታ ፣ ለአእምሮ በሽታ እንዲሁም ለመካንነት የተጋለጡ ይተጋለጡ ይሆናሉ ተባለ ፤ ምክንያቱን ምን ይሆ.....

ከህንድ ሀገር የሚሰማ የጤና ባለሙያው የስቃይ ድምፅ ቢንያም በቀለ አይነኩሉ ይባላል፡፡ ላለፉት ዓመታት በተለያዩ የመንግስት ጤና ተቋማት ፤ በተለይ ላለፉት 8 ዓመታት ደግሞ በዱርቤቴ የመጀመሪ...
21/12/2025

ከህንድ ሀገር የሚሰማ የጤና ባለሙያው የስቃይ ድምፅ

ቢንያም በቀለ አይነኩሉ ይባላል፡፡ ላለፉት ዓመታት በተለያዩ የመንግስት ጤና ተቋማት ፤ በተለይ ላለፉት 8 ዓመታት ደግሞ በዱርቤቴ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በነርሲንግ ሙያ በተለይ ደግሞ ለ5 አመት ጨቅላ ህፃናት ክፍል ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ህዝብን እያገለገለ ይገኛል፡፡ ነገር ግን ከጥቅምት 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከአቅሙ በላይ የሆነ ህመም ገጥሞታል፡፡

✍ወንድማችን ቢንያም በቀለ Non hodgkin's Lmphoma በተባለ የካንሰር ህመም እየተሰቃዬ ይገኛል። ሀገር ውስጥ የኬሞቴራፒ ህክምና/ፈለገ ህይወትና ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል/ ሲያደርግ ቆይቶ ህመሙ እየተባባሰበት በመሄዱ ለትራንስፕላንት/Transplant/ ወደ ህንድ ሀገር የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሪፈር ፅፎለታል።

ህክምናው ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ ያስፈልገዋል። ከዚህ ቀደም 2.7 ሚሊዮን ብር ተሰብስቦለት ስለነበር ህንድ ሀገር ከትራንስፕላንት ቀድሞ የሚወሰደውን ሳልቬጅ ኬሞቴራፒ/Salvage Chemotherapy/ ወስዶ ጨርሷል።

✍ከሳልቬጅ ኬሞቴራፒ በሗላ የተመረመረው የምርመራ ውጤት በጣም ጥሩ ለውጥ እንዳለው ያሳያል። ነገር ግን Stem cell transplant ለማሰራት 1.3 ሚሊዮን ብር በላይ ሰለቀረው ህክምናው ተቋርጧል። ብሩ ካልገባልን ፈጽሞ አይሰራም ተብሏል።

ወንድማችን ቢንያም በቀለ ከህንድ ሀገር ሆኖ የድረሱልኝ የስቃይ ድምፅ እያሰማ ይገኛል።

✍ቢንያም በቀለ በጣም ወደ ሚወደው ሙያው በቶሎ ተመልሶ ህዝብን ለማገልገል የእናንተን እገዛ በእጅጉ ይሻልና ሁሉም ኢትዮጵያዊ እዲረባረብ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

✍አካውንት ቁጥር
CBE: 1000212172387 ቢንያም በቀለ አይነኩሉ

✍ስልክ ቁጥር: 0968684875 ብርሃኑ በቀለ

በሁለም ጤና ባለሞያዎች ቤት ያለ እውነተኛ ታሪክ እኔ የምለው የጤና ባለሙያ መሆን ግን የትዳር አጋራችንን የልጆቻችንን ፣ ባጠቃላይ የቤተሠባችንን  ጤና ዘወር ብለን ሣናይ ሌት ከቀን የሌላውን...
21/12/2025

በሁለም ጤና ባለሞያዎች ቤት ያለ እውነተኛ ታሪክ

እኔ የምለው የጤና ባለሙያ መሆን ግን የትዳር አጋራችንን የልጆቻችንን ፣ ባጠቃላይ የቤተሠባችንን ጤና ዘወር ብለን ሣናይ ሌት ከቀን የሌላውን ሠው ህይወት ለማዳን ስንሮጥ የቅርብ ቤተሠባችንን ህይወት አደጋ ላይ ጥለን በቸልተኝነት ዋጋ የምንከፍለው እስከመቼ ነው?
ከ3ቀን በፊት ከስራ አድሬ በጣም ደክሞኝ ሴቷ ልጄ በስስት እያየችኝ"እማ ሆዴን በጣም አሞኛል ሀኪም ቤት አትወስጅኝም"በማለት እምባ ባቀረሩ አይኖቿበትዝብት አየችኝ።እኔም "ቆይ አሁን ደክሞኛል ነገ አይሽና ከቻልኩ እወስድሻለሁ አልኳትና አልፌያት መኝታ ቤቴ ሥገባ ባለቤቴ ተከትሎኝ ገባና "ልጁቷን እኮ በጣም አሟታል 3ቀን ሆናት ለሥሙ የሀኪም ልጅ ትባላለች "ሲለኝ "አባ እሷ ከኛ በላይ የምታሥብላቸው ታካሚዎቿን ነው ሥለኛ ምንም ግድ የላትም ስትል ዝጊ አንቺ ስላት እና ምን ለመሆኑ ደብተራችንን እንኳን አይተሽው ታውቂያለሽ?በላን አልበላን አይተሽን ታውቂያለሽ ?ምን እንደሚሠማን እንኳን ጠይቀሽን ታውቂያለሽ?ካንቺ ይልቅ አክሥታችን ውቤ እህትሽ እንግድነት ስትመጣ ገላችንን አጥባን የቤት ስራችንን አሰርታን ምግባችንን አብልታን ትሄዳለች። እስኪ ገላችንን ያጠብሽበትን ቀን አስታውሺ ፣ ደብተራችንን አይተሽ ውሏችንን የጠየቅሽበትን ቀን ንገሪኝ?ደክሞኛል ትይንና እንትና ልትወልድ ነው ሲሉሽ ትሮጫለሽ፣እንትናን ለማሣከም ሄደን ተቸገርን እባክሽ ነይልን ስትባይ አሁንም ትሮጫለሽ እዛው ትውይና ማታ ላይ በዛው ስራ ገብቻለሁ ብለሽ ትደውያለሽ።ቆይ ንገሪኝ አንቺን እኮ እንደናት አይደለም እንደጎረቤትም ማግኘት አልቻልንም በቃ ስራሽ ከኛ ከበለጠብሽ አንዱን ምረጪ!!!በቃ እኔእናት እያለኝ እንደሌለኝ መቁጠር ሰልችቶኛል ወይ ለራስሽ አልሆንሽ ወይ ለኛ አልሆንሽ!!ባለቤቴ በዝምታ ካዳመጣት በኋላ "አየሽው የስራሽን ውጤት"በማለት አፈጠጠብኝ። እኔ ምንም መናገር አልቻልኩም ሁሉም እውነት ነው ግን ምን ላርግ?በተከታታይ 3ቀን ሙሉ እቤቴ ሳልገባ የቆየሁበት ጊዜም አለ ።ጓደኛዬ ልጇን ሆስፒታል አስተኝታ ስትቸገር ነበር የሷን ለመሸፈን ያደርኩት ።ያን ጊዜ እህቴ ታዝባኝ ለመሆኑ ብሩም እንዳረብ ሀገር ነው ወይስ ስራችሁ ብቻ ነው?ብላኝ ታውቃለች ።ግን ምን ዋጋ አለው፤ለቅሶ አለ ስባል ስራ ነኝ አይመቸኝም ፣ሠርግ አለ ስባል ሥራ ነኝ አይመቸኝም ፤እከሌን እንጠይቅ ስባል አሁንም ስራ ነኘ!!!!የሚገርመው ግን እናቴ ጋር እደውልና "እታዬ በርበሬ ካስፈጨሽ ፣ እታዬ ሽሮ ካዘጋጀሽ ስል እሷም እንደፈረደባት ቋጥራ ትልካለች።ግን እሰከመቼ!!?የልጄ የመጨረሻ ቃል ነበር ከቅዠቴ ያነቃኝ "ታውቂያለሽ ጓደኞቼ እናትሽ ሀኪም ነች ታድለሽ ሲሉኝ በጣም ደሥ ይለኝ ነበር እንዳንቺ ለመሆን ስል በጣም እያነበብኩ እንቅልፍ እንዳይወስደኝ ባዶ ሆዴን ቡና በጥብጬ እየጠጣሁ ጨንጓራዬን እስክታመም አጠናሁ ቀጣይ አመት ማትሪክ ወስጄ MEDICINE ለመማር ማቀዴ ስህተት መሆኑን አወቅሁኝ ።እማ እንዳንቺ ከምሆን ይቅርብኝ" ስትለኝ የምገባበት ጠፋኝ ።በቃ !!ብዬ ጮህኩባት አዎ ይሄ ሁሉ የኔ ጥፋት ነው ይቅርታ አስተካክላለሁ አንቺም ትማርያለሽ ስላት ታናሿ "ልጇ ስትታመም ኢግኖር ለማድረግ ስትለኝ የባሠ
ጮህኩኝ።ግን ሁሉም እውነት ነው ለራሴ ቃል ገባሁ። የጤና ው ሲስተም ካልተሻሻለ ለቅቄ ብወጣ ምንም አይጎልብኝ የጀበና ቡናም ቢሆን ሸጬ አድራለሁ።

You can view and join right away.

*"ወደፊት ለህክምና ትምህርት የሚመዘገብ  ጠፍቶ እንደወታደር ከየቤቱ እየታፈሠ የሚመለመልበት ሁኔታ ሊፈጠር ነው "*ወር ሙሉ ቀን ከሌት በደምና በእንሽርት ውሀ እየተጨማለቅን፣ ለማይድን በሽታ...
21/12/2025

*"ወደፊት ለህክምና ትምህርት የሚመዘገብ ጠፍቶ እንደወታደር ከየቤቱ እየታፈሠ የሚመለመልበት ሁኔታ ሊፈጠር ነው "*

ወር ሙሉ ቀን ከሌት በደምና በእንሽርት ውሀ እየተጨማለቅን፣ ለማይድን በሽታ እራሣችንን እና ቤተሠባችንን አሣልፈን እየሠጠን ።፣ብሎም ኮቪድና ማርበረግ ሲመጡ ከሁሉም ህብረተሠብ ቀድመን በሽታውንና ሞቱን እንደወጥ እየቀመሥን በየጊዜው ልጆቻችንን በትነን ለምንሞተው ለእኛ ለጤና ባለሙያዎች የተጋላጭነት ክፍያ ተብሎ ከ30 አመት በፊት የተመደበውን በወር ከ 470---1200 የኢትዮጵያ ብር የሚከፈልበትና ለካድሬ ውሎ አበል ሲሆን ግን በቀን ከ2500 በለይ የሚከፈልበትን ምክንያት ግልፅ አይደለም
ይሄን የጤናውን ስርአት የሚመሩት ስቪል ሰርቪሥ ባለሥልጣኖች ሥለ ጤና ጥቅሞችና ለአንድ ሀገር አሰፈላጊ መሆኑን ብትጠይቁት ምንም አይነት ግንዛቤ እንደሌላቸው ያሣያል።ሥለሆነም የጤናውን ስርአት ሥለ ጤና ግንዛቤ ያለው ሠው ካልመራውና በብሥለት ካልታዬ ወደፊት ለህክምና ትምህርት የሚመዘገብ ጠፍቶ እንደወታደር ከየቤቱ እየታፈሠ የሚመለመል ካልሆነ ማንም ለድህነትና ለበሽታ ህክምናን አይማርም።!!!!!

20/12/2025

— የ ሀላባ አጠቃላይ ሆስፒታል ባለሙያዎች ሀሙስ በተገባው ቃል በተገባው መሰረት እስከ ቅዳሜ የ 2 ወር duty እናስገባለን ባሉን መሰረት ህብረተሰብ ከሚጉላላ እስከ ቅዳሜ እንስራ እንታገስ ብለን ስራችንን እየሰራን ነበር በመሆኑም ቃላቸውን በማጠፍ ምንም አታመጡም በመለታቸው ከ ሰኞ ጀምሮ ምንም አይነት የ duty አገልግሎት የማንሰጥ እና ለሚፈጥረው ሀሉ ሃላፊነት እንደማንወስድ ልናሳውቅ እንወዳለን ማሳሰቢያ በድጋሜ ባለሙያ ላይ ማንኛውም እርምጃ ለመውሰድ መሞከር ሙሉ ለሙሉ ስራ ለማቆም የምንገደድ መሆኑን እናሳውቃለን። hakim mereja የኛ ድምጽ ስለምታደርጉልን ሀሉም ነገር እናመሰግናለን።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251934647389

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hakim Mereja ሀኪም መረጃ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Hakim Mereja ሀኪም መረጃ:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram