Hakim Mereja ሀኪም መረጃ

Hakim Mereja ሀኪም መረጃ Sometimes take a LOSS for a bigger WIN.

24/07/2025

ትግል ፅናት(consistency) ይፈልጋል ፣ ትግል አንድነት (unity) ይፈልጋል ፣ ትግል አስጨናቂ መሆንን (ጥሩ የሚዲያ ዘመቻ ማድረግ እና ህዝብን ከጎን ማሰለፍን) ይፈልጋል።

ለታላቁ አድማ 53 ቀናት ብቻ ቀርተውታል። ጥያቄያችን ካልተመለሰ ሌሎች ሰራተኞችንም ከጎናችን የምናሰልፍበት ፣ እኛም ተጠናክረን የምንመለስበት ይሆናል።

Stay United!
መልካም ቀን!

Hakim Mereja ሀኪም መረጃ

23/07/2025

Join our Telegram Channel 👉🏻

23/07/2025

እኛን ለመሸወድ እና ጥያቄያችንን ለማድበስበስ መሞከር የጤና ባለሙያውን ጥያቄ መናቅ ነው‼️

ዋናው ጥያቄያችን መኖር አቅቶናል መሰረታዊ የሚባሉ ነገሮችን ማሟላት አልቻልንም። በቀን 2 ጊዜ መብላት አልቻልንም። የቤት ኪራይ መክፈል አልቻልንም። ልብስ እና ጫማ በአመትም መቀየር አልቻልንም። ልጆቻችንን መመገብም ሆነ ማስተማር አልቻልንም። ለተለያዩ ተላላፊ በሽታዎች ተጋላጭ ነን ነው።

ስለዚህ ደሞዛችን እንደ ሌሎች አቻ የአፍሪካ ሀገራት ይስተካከልልን ፣ ጥቅማ ጥቅሞች የስራችንን ሁኔታ ታሳቢ ባደረገ መልኩ በአመርቂ ሁኔታ ይሰጠን፣ በቂ የተጋላጭነት ክፍያ ይከፈለን ነው። ‼️

እስከ ሰኞ መስከረም 5 ጥያቄዎቻችንን የመመለሻ ጊዜ ሰጥተናችኋል። 54 ቀናት ይቀራሉ!

አንድነት ሀይል ነው‼️
አሁን ካልሆነ መቼ?

   If we want our demands to be met in less than a week, all health institutions, from health centers upwards, must go o...
23/07/2025


If we want our demands to be met in less than a week, all health institutions, from health centers upwards, must go on a full strike. This requires preparation starting now.
Since there will be some cadre health professionals who won't fight for their rights and will hinder the ongoing struggle, I believe it's necessary to organize a covert force and take action. If there isn't a full national strike, a disorganized approach (some working, some protesting) will not only fail to bring about change but will also allow those fighting for our rights to be consumed by dirty politics.
I believe we can learn from the last strike and bring about better change this second time around.
Stay united 💪💪

Teferi Mekonnen

23/07/2025
ኢትዮጵያ ውስጥ ሆነን አንድ ሀገር እየኖርን አንዱ ከላይ ሌላው እንደባሪያ እያገለገለ የሚንኖርበት ሁኔታ ማብቃት አለበት። እኛ ጤና ባለሙያዎች ከሀገሪቷ አቅም በላይ ወይም የሌለ ያልተለመደ ጥ...
23/07/2025

ኢትዮጵያ ውስጥ ሆነን አንድ ሀገር እየኖርን አንዱ ከላይ ሌላው እንደባሪያ እያገለገለ የሚንኖርበት ሁኔታ ማብቃት አለበት። እኛ ጤና ባለሙያዎች ከሀገሪቷ አቅም በላይ ወይም የሌለ ያልተለመደ ጥያቄ አልጠየቅንም። ፍትሃዊና ህጋዊ ጥያቄ ነው የጠየቅነው። ይህን መብታችንን ካልተመለሰልን ደግሞ እንደሀገር ዳግም የስራ ማቆም አድማ ልናደርግ እንገደዳለን።

ለመብታችን መታገል አለብን። ክብራችንን አጥተንም ፣ ጊዚያችንንም አጥተን ፣ ተመጣጣኝ ክፍያና ዋጋም ሳናገኝ እስከመቼ???

እኛ ዝም ካልንስ ማን ነው ሚቆረቆርልን?! ጊዜው አሁን ነው መተባበር አለብን!

በርቱ ✊ እንበርታ

23/07/2025

💥💥💥54 Days Left💥💥💥

ኢትዮጵያ ውስጥ ሆነን አንድ ሀገር እየኖርን አንዱ ከላይ ሌላው እንደባሪያ እያገለገለ የሚንኖርበት ሁኔታ ማብቃት አለበት። እኛ ጤና ባለሙያዎች ከሀገሪቷ አቅም በላይ ወይም የሌለ ያልተለመደ ጥያቄ አልጠየቅንም። ፍትሃዊና ህጋዊ ጥያቄ ነው የጠየቅነው። ይህን መብታችንን ካልተመለሰልን ደግሞ እንደሀገር ዳግም የስራ ማቆም አድማ ልናደርግ እንገደዳለን።

ለመብታችን መታገል አለብን። ክብራችንን አጥተንም ፣ ጊዚያችንንም አጥተን ፣ ተመጣጣኝ ክፍያና ዋጋም ሳናገኝ እስከመቼ???

እኛ ዝም ካልንስ ማን ነው ሚቆረቆርልን?! ጊዜው አሁን ነው መተባበር አለብን!

በርቱ ✊ እንበርታ

ሕይወት ስናድን ኖረናል! አሁን ግን የራሳችንንም ሕይወት ማዳን ይኖርብናል! ሰዓቱ እያለቀ ነው! 54 ቀናት ብቻ ቀርተዋል ! ዝምታው አሁን ያብቃ!

We save lives! Now it's time to save ours too! The Clock is Ticking! 54 Days to Hold the System Accountable. The Silence Should End Now!

lubbuu baraaraa jiraanne! Amma garuu lubbuu ofii keenyaas baraaruu qabna!
Sa'aatiin lakkaawaa jira! Guyyoota 54 qofatu hafe! Amma booda hin callisnu!

ህይወት እናድሓና ፀኒሕና ኢና! ሕጂ ንዓርስና ነድሕነሉ ግዜ እዩ!
እቲ ሰዓት ይውዳእ ኣሎ! 54 መዓልቲ ጥራሕ ቀርየን! ሱቕታ ሕዚ ይኾናኖ!

shemppuwa ashiidi gam'ida,ha'i nu shemppuwa ashanaw bessees




Welcome home Dr Daniel
23/07/2025

Welcome home Dr Daniel

22/07/2025

ጥያቄያችን አታስርቡን ፣ አትሰሩን ነው ፣ የወንበር (የስልጣን) ጥያቄ የለንም።

(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዶክተር ዳንኤል ፈንታነህ በዋስ ተፈታ፡፡ ‹‹ዶክተር ደቦል›› በሚል በስፋት የሚታወቀው ዶክተር ዳንኤል ፈንታነህ በባህር ዳር መታሰሩን ከዚህ ቀደም በዘ-ሐበሻ ዜና መዘገባችን...
22/07/2025

(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዶክተር ዳንኤል ፈንታነህ በዋስ ተፈታ፡፡ ‹‹ዶክተር ደቦል›› በሚል በስፋት የሚታወቀው ዶክተር ዳንኤል ፈንታነህ በባህር ዳር መታሰሩን ከዚህ ቀደም በዘ-ሐበሻ ዜና መዘገባችን ይታወሳል፡፡

በህክምና ላይ የሚያተኩሩ የተለያዩ መፅሀፍትን ያሳተመውና በጤና ባለሙያዎች መብት ንቅናቄ ላይ ንቁ ተሳታፊ የሆነው ዶክተር ዳንኤል በዛሬ እለት በ15 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር የተለቀቀ ሲሆን የጤና ባለሙያዎች ንቅናቄ ይህንን በተመለከተ ባወጣው መግለጫ የዶክተሩን መፈታት አዎንታዊ እርምጃ ካለው በኋላ ‹‹ማንኛውም ጤና ባለሙያ በሰላማዊ መንገድ መብቱን በመጠየቁ ወይንም ለጤና ስርአት ማሻሻያዎች በመሟገቱ ያለ ፍትህ የሚደረግ እስራትን እናወግዛለን›› ብሏል፡፡

ጨምሮም ‹‹የዶክተር ደቦል እስር በሙያችን ውስጥ ለፍትህ የሚታገሉ ሰዎች የሚያጋጥማቸውን ጭቆና አጉልቶ የሚያሳይ ነው›› ያለው ንቅናቄው ሲቀጥልም ‹‹መሰረታዊ መብቶችን መጠየቅ ወንጀል አይደለም፡፡ ለጤና ባለሙያዎ የህልውና ወሳኝ ጉዳች ወቅታዊና ተጨባጭ መፍትሄዎች ይገባቸዋል፡፡ እነዚህ ጥያቄዎች ትርጉም ባለው መልስ እስከሚሟሉ ድረስ የጋራ ትግላችን ይቀጥላል›› በማለት አሳስቧል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ንቅናቄው ለጥያቄዎቹ መልስ እንዲሰጠው ጥሪ አቅርቦ መልስ ካልተሰጠው በመጪው መስከረም 5 ሁለተኛ ዙር የጤና ባለሙያዎች ስራ ማቆም አድማ እንደሚጠራ ማሳሰቡን መዘገባችን አይዘነጋም፡፡

ወቅታዊ መግለጫዶ/ር ዳንኤል ፈንታነህ በ15,000 ብር ዋስ እንዲለቀቀ ፍርድ ቤት ወስኗል በስፋት  ዶክተር ደቦል በመባል  የሚታወቀው ዶ/ር ዳንኤል ፈንታነህ፤ የዶክተር ደቦል የፌስቡክ ገፅ ...
22/07/2025

ወቅታዊ መግለጫ

ዶ/ር ዳንኤል ፈንታነህ በ15,000 ብር ዋስ እንዲለቀቀ ፍርድ ቤት ወስኗል

በስፋት ዶክተር ደቦል በመባል የሚታወቀው ዶ/ር ዳንኤል ፈንታነህ፤ የዶክተር ደቦል የፌስቡክ ገፅ መስራች ፣ የደቦል የቀዶ ጥገና የተማሪዎች መርጃ መፅሐፍ አዘጋጅ፣ የደቦል የክሊኒክ አከፋፈት መርጃ መጽሐፍ አዘጋጅ እንዲሁም የ MAC ኢትዮጵያ ተባባሪ መስራች እና የጤና ባለሙያዎች መብት እና ህልውና ተከራካሪ ዛሬ በዋስ መፈታቱን ስናበስር በታላቅ ደስታ ነዉ።

ይህንን አዎንታዊ እርምጃ እያበረታታን ማንኛውም የጤና ባለሙያ ሰላማዊ በሆነ መንገድ መብቱን በመጠየቁ ወይም ለጤና ስርዓት ማሻሻያዎች በመሟገቱ ያለ ፍትህ የሚደረግ እስራትን አጥብቀን እያወገዝን ነው ።
የዶ/ር ደቦል መታሰር በሙያችን ውስጥ ለፍትህ የሚታገሉ ሰዎች የሚያጋጥማቸውን ጭቆና አጉልቶ የሚያሳይ ነው።

ለእሱ እና ለሌሎች የታሰሩ የጤና ባለሙያዎች ድምፃቸውን ላሰሙ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ፣ ለእስረኛ ቤተሰቦች እና ጓደኞቹ ፣ ለሥራ ባልደረቦቹ ፣ ለመገናኛ ብዙሃን ፣ ለጋዜጠኞች እና በእስር ላይ በነበረበት ወቅት እሱን በመጎብኘት እና ለነፃነቱ ጥሪውን በማጉላት ከእርሱ ጋር አብረው ለተሰለፉ ሁሉ ጥልቅ ምስጋናችንን እናቀርባለን ።
ቆራጥነታችሁ እና አንድነታችሁ ለዚህ ውጤት ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል።
ዶክተር ዳንኤል እንኳን ለቤትህ አበቃህ!በእውነትም የጀግንነት ተምሳሌት ነህ!

አቋማችን ግልፅ ነው!

- መሰረታዊ መብቶችን መጠየቅ ወንጀል አይደለም።
- ለጤና ባለሞያዎች የህልውና ወሳኝ ጉዳዮች ወቅታዊ እና ተጨባጭ መፍትሄዎችን ይገባቸዋል

- እነዚህ ጥያቄዎች ትርጉም ባለው መልስ እስከሚሟሉ ድረስ የጋራ ትግላችን ይቀጥላል።

አንድነት ኃይል ነው።
ለለውጥ ጊዜው አሁን ነው ! አማራጭ የለም።

©️EHPM የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቡድን

ሰበር ከአንድ ወር በላይ በእስር ላይ የቆየው ዶ/ር ዳንኤል ፈንታነህ በዛሬው ዕለት በ15,000 ብር ዋስ ከእስር እንደተፈታ ታውቋል።
22/07/2025

ሰበር

ከአንድ ወር በላይ በእስር ላይ የቆየው ዶ/ር ዳንኤል ፈንታነህ በዛሬው ዕለት በ15,000 ብር ዋስ ከእስር እንደተፈታ ታውቋል።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251934647389

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hakim Mereja ሀኪም መረጃ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Hakim Mereja ሀኪም መረጃ:

Share