Doc Book

Doc Book � Writer only

27/03/2026

" የቲቢ መድኃኒት በነፃ ነው፤ ከፍሎ የሚወስድ የተሰረቀ መድኃኒት እየገዛ ነው " - ጤና ሚኒስቴር

በኢትዮጵያ በየአንድ ሰዓቱ የሁለት ሰዎች ሕይወት በቲቢ በሽታ ምክንያት እንደሚቀጠፍና ሀገራችን የበሽታው ከፍተኛ ጫና ካለባቸው 30 የዓለም ሀገራት ውስጥም አንዷ መሆኗ ተገለጸ።

ይህ የተገለጸው የዓለም የቲቢ ቀንን ምክንያት በማድረግ በጤናው ዘርፍና በሚዲያ ባለሙያዎች መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር ጤና ሚኒስቴር ባዘጋጀው የሚዲያ ፎረም ላይ ነው።

በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ህይወት ሠለሞን እንደገለጹት ፤ መንግሥት ለአንድ የቲቢ ታካሚ በዓመት ከ6 እስከ 8 ሺህ ዶላር ወጪ እያደረገ ይገኛል።

" የቲቢ መድኃኒት ለታማሚዎች በነፃ ነው የሚሰጠው ፤ ከዚህ ውጭ መድኃኒቱን ከፍሎ የሚወስድ ሰው ካለ እየገዛ ያለው የተሰረቀ መድኃኒት ነው " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

በአሁኑ ወቅት ከ2,000 በላይ የግል ጤና ተቋማት ምርመራና ሕክምና እየሰጡ ሲሆን ለ1,000 ተቋማት መመርመሪያ መሣሪያዎች መሰራጨታቸውን ገልጸዋል። በገጠሩ አካባቢ ለሚገኙ 690 ላቦራቶሪዎች የሶላር ፓነል ዝርጋታ መከናወኑን አመልክተዋል።

በሚኒስቴሩ የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዴስክ ኃላፊ አቶ ታዬ ለታ በበኩላቸው ፥ ባለፉት 6 ወራት ብቻ የሶማሌ ክልልን ሳይጨምር ለ138,000 ሰዎች በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) የታገዘ ምርመራ ተደርጎ 3,500 ያህል የቲቢ ተጠቂዎች መገኘታቸውን ተናግረዋል።

አክለውም ፥ በሀገራችን ከሚከሰቱ የቲቢ አይነቶች 70% ሳምባን የሚያጠቁ ሲሆኑ፣ 30% ደግሞ ሌሎች ሁሉንም የሰውነት ክፍሎችን እንደሚያጠቁ ተናግረዋል።

ምልክቶቹ ፦
• ለሁለት ሳምንትና ከዚያ በላይ የሚቆይ ሳል፣
• ትኩሳት፣
• ማታ ማታ ማላብ፣
• የሰውነት ክብደት መቀነስ፣
• አልፎ አልፎ ደም የቀላቀለ አክታ ናቸው።

አቶ ታዬ በዓለም ላይ በየዓመቱ 10.7 ሚሊዮን ሰዎች በቲቢ እንደሚያዙ ከ1.2 እስከ 1.3 ሚሊዮን የሚደርሱትም ሕይወታቸውን እንደሚያጡ ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ በዓመት 19,000 ሰዎች ይሞታሉ።

" አንድ የታመመ ሰው ሲያስል ወይም ሲያስነጥስ እስከ 40,000 ሚደርሱ ጥቃቅን ጠብታዎችን ፤ ለ5 ደቂቃ ብቻ ሲያወራ ደግሞ 3,000 ጠብታዎችን ወደ አየር በመልቀቅ በሽታውን በቀላሉ ከሰው ወደ ሰው ያሰራጫል " ብለዋል።

ሰዎች ሲያስነጥሱ ወይም ሲያስሉ አፍና አፍንጫቸውን በክንድ ወይም ባማስክ መሸፈን አለባቸው ሲሉ አስገንዝበዋል።

በየዓመቱ የብዙ ሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ ቢሆንም ብዙ ሰው ግድ አይሰጠውም ብለዋል።

እስካሁን 150,000 ታካሚዎች ወደ ሕክምና ማስገባት ቢቻልም አሁንም 30,000 "የተደበቁ" ታማሚዎችን ለማግኘት የጤና ባለሙያዎች ቤት ለቤት ፍለጋ እያደረጉ እንደሚገኙ አመልክተዋል።

ለቲቢ ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑት ፦
- ከታካሚ ጋር የሚኖሩ፣
- ስኳርና ኤችአይቪ ያለባቸው
- የአየር ዝውውር በሌለው ቤት የሚኖሩ ናቸው።

በሌላ መረጃ ፥ ባለፉት 6 ወራት 1,460 አዳዲስ የሥጋ ደዌ ታማሚዎች ተለይተዋል። በአሁኑ ወቅት 1,800 ሰዎች በሕክምና ላይ ናቸው። ይህ ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በዚህ በሽታ በዓመት እስከ 3000 ሰዎች ይሞታሉ።

አዲስ መረጃአዲሱ የአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ሠራተኞች አዋጅ (87/2017) ምን ይዞ መጣ?  ስለ ቅጥር፣ የብቃት ምዘና እና ጥቅማጥቅሞችየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት አገልግ...
14/03/2026

አዲስ መረጃ

አዲሱ የአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ሠራተኞች አዋጅ (87/2017) ምን ይዞ መጣ?
ስለ ቅጥር፣ የብቃት ምዘና እና ጥቅማጥቅሞች
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት አገልግሎቱን ለማዘመንና በብቃት ላይ የተመሰረተ አሠራር ለመዘርጋት አዲስ አዋጅ አውጥቷል። እነዚህን ነጥቦች ይዘንላችሁ ቀርበናል፦
🔹 ቅጥር በብቃት ብቻ! ከእንግዲህ ቅጥር፣ የደረጃ ዕድገት እና ዝውውር የሚፈጸመው በዘፈቀደ ሳይሆን በ"ብቃት ምዘና እና ማረጋገጫ" ውጤት ላይ ተመስርቶ ብቻ ይሆናል። ብቃትን የሚመዝን ራሱን የቻለ ተቋምም በአዋጁ ተቋቁሟል።
🔹 የሙከራ ጊዜ ማሻሻያ አዲስ ተቀጣሪ የ6 ወር የሙከራ ጊዜ ይኖረዋል። ውጤቱ ዝቅተኛ ከሆነ ለተጨማሪ 3 ወራት ሊራዘም ይችላል፤ ከዚያም ካልተሻሻለ ስንብት ይሆናል።
🔹 ደመወዝ እና ጥቅማጥቅም
• እኩል ክፍያ፦ ተመሳሳይ ዋጋ ላላቸው ሥራዎች እኩል መነሻ ደመወዝ ይከፈላል።
• የዕርከን ጭማሪ፦ በየ2 ዓመቱ የሚደረገው የደመወዝ ጭማሪ በሥራ አፈጻጸም ውጤት ላይ የተመሠረተ ይሆናል።
• አበል፦ የመስክ ውሎ፣ የአየር ፀባይ እና የትርፍ ሰዓት ክፍያዎች በግልጽ ተደንግገዋል።
🔹 ልዩ ፈቃዶች ለጋብቻ፣ ለሐዘን እና ለፈተና በበጀት ዓመት ውስጥ 7 የሥራ ቀናት የሚከፈልበት ፈቃድ መፈቀዱ ለሠራተኛው ትልቅ እፎይታ ነው።

 ስለ ሥነ-ምግባር፣ ስንብት እና ልዩ ድጋፎች

ለሴት ሠራተኞች የተሰጠ ልዩ ትኩረት
• በቅጥር እና በሥልጠና ሴቶች ቅድሚያ (Affirmative Action) ያገኛሉ።
• እያንዳንዱ መሥሪያ ቤት ለሴት ሠራተኞች የሕፃናት ማቆያ የማቋቋም ግዴታ አለበት።
• የወሊድ ፈቃድ በአግባቡ እንዲከበር ተደንግጓል።
 ዲሲፕሊን እና ተጠያቂነት
• አገልግሎት ማዘግየት፣ ባለጉዳይ ማጉላላት እና ከሥራ ገበታ መቅረት ከባድ የዲሲፕሊን ቅጣት ያስከትላሉ።
• በሙስና ወይም በሥልጣን አለአግባብ መጠቀም የተገኘ ሠራተኛ አስተዳደራዊ እና የወንጀል ተጠያቂነት ይኖርበታል።
 ከሥራ ስለመሰናበት
• በጤና እክል፣ በብቃት ማነስ (ተከታታይ ዝቅተኛ ውጤት) ወይም በዲሲፕሊን ምክንያት ስንብት ሊኖር ይችላል።
• የጡረታ መውጫ ዕድሜ 60 ዓመት መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በአስተዳደሩ ውሳኔ እስከ 5 ዓመት ሊራዘም ይችላል።
 የቅሬታ አፈታት ሥርዓት ማንኛውም ሠራተኛ መብቴ ተጥሷል ካለ ለቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ወይም ለከተማው አስተዳደር ፍርድ ቤት አቤቱታ የማቅረብ መብቱ የተጠበቀ መሆኑን አዋጁ ይደነግጋል።

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው እለት በተለያዩ የሕክምና ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 263 አዳዲስ ባለሙያዎችን ሲያስመርቅ ዶ/ር ሜሮን ለገሰ ከህክምና ትምህርት ቤት 3.95 CGPA በማምጣት የከፍ...
14/03/2026

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው እለት በተለያዩ የሕክምና ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 263 አዳዲስ ባለሙያዎችን ሲያስመርቅ ዶ/ር ሜሮን ለገሰ ከህክምና ትምህርት ቤት 3.95 CGPA በማምጣት የከፍተኛ ውጤት እና የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ለመሆን በቅታለች። በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሴት ተማሪዎች ውጤታማነትና ተሳትፎ እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቅሳ በዘርፉ ያገኘችውን እውቀትም ለሀገሯና ለወገኖቿ በቅንነት ለማገልገል ዝግጁ መሆኗን ገልፃለች።
: Center of Excellence for Medical Education

የአፋልጉኝ ማስታወቂያከዚህ በታች በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ወጣት  ወንድማችን በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል  በህክምና ላይ ይገኛል።ወደ ሆስፒታላችን ከመጣ ከአንድ ሳምንት  በላይ የሆነው ሲሆ...
11/02/2026

የአፋልጉኝ ማስታወቂያ

ከዚህ በታች በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ወጣት ወንድማችን በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል በህክምና ላይ ይገኛል።ወደ ሆስፒታላችን ከመጣ ከአንድ ሳምንት በላይ የሆነው ሲሆን ወጣቱ ስለ እራሱም ሆነ ስለቤተሰቡ በደንብ መናገር ስለማይችል ማንነቱን ማወቅ አልተቻለም። በዚህም ምክንያት ቤተሰቡን ማግኘት ስለአልተቻለ ይህንን ወጣት የምታቁት ወይም ቤተሰቦቹን የምታቁ ካላችሁ እንድትተባበሩን ስንል በትህትና እንጠይቃለን።እንዲሁም ደሞ ቤተሰቡን እንዲያገኝ ሼር በማድረግ ተባበሩን።

የዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ሶሻል ወርክ ክፍል

06/02/2026

እየሞከርኩኝ ነው

👉ይህ የጤና ባለሙያው የዕለት ተዕለት ጥረቱ ድምፁ ነው አንብቡት የያሲኖን ቪዲዮም ተመልከቱት

👉level lv አለኝ ዲግሪየን ለመያዝ ለመማር እየሞከርኩኝ ነው

👉ዲግሪየን ይዣለሁ ሁለተኛ ዲግሪየን ለመያዝ እየሞከርኩኝ ነው

👉አሁን ደግሞ 3ኛ ዲግየን ለመያዝ እየሞከርኩኝ ነው

👉ያለውበትን የትምህርት ደረጃ ሰብ ስፔሻለይዝድ ለማድረግ ለመማር እየሞከርኩኝ ነው

👉በጤናው ዘርፍ ተመርቄ ስራ አጥቸ ስራ ለማግኘት እየሞከርኩኝ ነው

👉ስራ አግኝቻለሁ ግን የሚከፈለኝ ወራዊ ደመወዝ ኑሮን ለመግፋት አላስችል ስላለኝ ተጨማሪ ስራ ለማግኘት እየሞከርኩኝ ነው

👉ቀን ቀን ብቻ ሰርቸ ኑሮ ስለከበደኝ ዲዩቲ የሚያሰራ ጤና ተቋም ለማግኘት እየሞከርኩኝ ነው

👉እኔ ያለውበት አካባቢ በጤናው ዘርፍ ያለው የስራ ዘርፍ የተቀዛቀዘ በመሆኑ ራቅ ያለ የኢትዮጵያ ክፍል ሄጀ ለመስራት እየሞከርኩ ነው

👉የመንግስት ስራ ወራዊ ደመወዝ በቂ ስላልሆነ ኑሮን ለመቋቋም በጋራም ሆነ በግሌ ክሊኒክ ከፍቸ ለመስራት እየሞከርኩ ነው

👉የግል ጤና ተቋሜ ያለው ደረጃ አነስተኛ በመሆኑ ደረጃውን ከፍ አድርጌ ማሽኖችን አሟልቸ ለመስራት እሞከርኩኝ ነው

👉ወቅታዊው የህክምና ዕቃ ዋጋ መናርና ኑሮ መወደድ የግል ጤና ተቋም ለመክፈት ቢከብድም ይሳካልኝ ዘንድ እየሞከርኩኝ ነው

👉ከግልም ከመንግስትም ጤና ተቋም የስራ ዕድል በማጣቴ ወይም አመርቂ ክፍያ ባለመኖሩ የራሴን ለመክፈት እየሞከርኩኝ

👉የምኖርበት የስራ ቦታ ከቤተሰብ የራቀ የአየር ንብረቱ ፈታኝ በመሆኑ መፍትሄ ለማግኘት እየሞከርኩኝ ነው

👉የጤናው ዘርፍ ቢዝነሱ የተቀዛቀዘ በመሆኑ ከምወደው ሙያየ ውጭ ለመስራት እየሞከርኩ ነው

በቃ ለመኖር ለማደግ በህይወቴ ለውጥ ለማምጣት እየሞከርኩኝ ነው,,,,,,,,

04/02/2026

🏥 Invitation for Pharmacy Partners in Ethiopia

Join us in creating a more connected healthcare system and directly reach patients actively searching for medications.

📱 Partner with MyDrugLocator – Ethiopia's trusted platform for real-time drug availability.

Deliver value to your community by:
✅ Increasing Visibility: Be found by patients in your area who need your specific stock.
✅ Providing Critical Access: Help people locate essential medicines quickly.
✅ Using Professional Tools: Manage your listings through our dedicated platform.

📋 Simple Onboarding:

Register at mydruglocator.com/register

Set up your verified profile.

Start listing medications to connect with patients.

Become a key partner in a vital network to make essential medicines easier to find.

Connect with us:
📍 Website: mydruglocator.com
📍 Bot:
📍 Updates: t.me/MyDrugLocator
📍 Community: t.me/MyDrugLocatorCommunity

አሜሪካ ከዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ለቀቀች።አሜሪካ ከዓመት በፊት በሰጠችው ቅድመ ማስጠንቀቂያ መሠረት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አካል ከሆነው የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) አባልነት ...
23/01/2026

አሜሪካ ከዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ለቀቀች።

አሜሪካ ከዓመት በፊት በሰጠችው ቅድመ ማስጠንቀቂያ መሠረት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አካል ከሆነው የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) አባልነት በይፋ ለቅቃ ወጣች።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሁለተኛ ዙር የሥልጣን ዘመናቸውን በጀመሩበት ዕለት ካስተላላፏቸው ፕሬዝዳንታዊ ውሳኔዎች መካከል አንዱ የሆነው ከዓለም ጤና ድርጅት መውጣት ተግባራዊ ሆኗል።

ይህንን ውሳኔ ተከትሎ የአሜሪካ ሰንደቅ ዓላማ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ከሚገኘው የዓለም የጤና ድርጅት ዋና መሥሪያ ቤት እንዲነሳ ተደርጓል።

ከዚህ በኋላ አገሪቱ ከዓለም ጤና ድርጅት ጋር የሚኖራት ግንኙነት ውስን እና ከተቋሙ መውጣቷን ለማጠናቀቅ በሚያስፈልጉ ጉዳዮች ላይ እንደሚሆን ተነግሯል።

አንድ ከፍተኛ የአሜሪካ መንግሥት የጤና ባለሥልጣን " በድርጅቱ ውስጥ በታዛቢነት የመሳተፍም ሆነ መልሶ አባል የመሆን ዕቅድ የለንም " ሲሉ ተናግረዋል።

በበሽታዎች ቁጥጥር እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው በሌሎች የኅብረተሰብ ጤና ጉዳዮች ላይ በዓለም አቀፍ ድርጅት በኩል ሳይሆን በቀጥታ ከአገራት ጋር ለመሥራት አቅዳለች።

በኢትዮጵያዊው ዶ/ር ቴድሮስ አድኃኖም የሚመራው እና ከ190 በላይ አገራትን በአባልነት ከያዘው ተቋም አሜሪካ ለመውጣት መወሰኗ በአሜሪካ እንዲሁም በቀሪው የዓለም ክፍል የሚከናወኑ የጤና ሥራዎችን የሚጎዳ መሆኑ እየተነገረ ነው።

 #ማስታወሻየ2018 ዓ.ም የብሔራዊ ህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና (Ethiopian Residency Matching Program/ERMP) ምዝገባ ከታህሳስ 06/2018 ዓ.ም ጀምሮ በመካሔድ ላይ ይ...
27/12/2025

#ማስታወሻ

የ2018 ዓ.ም የብሔራዊ ህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና (Ethiopian Residency Matching Program/ERMP) ምዝገባ ከታህሳስ 06/2018 ዓ.ም ጀምሮ በመካሔድ ላይ ይገኛል፡፡

ጤና ሚኒስቴር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በህክምና ዲግሪ ያላቸውንና የስፔሻሊቲ ስልጠና በ2018 ዓ.ም መከታተል የሚፈልጉ አመልካቾችን በብሔራዊ የህክምና ስፔሻሊቲ መግቢያ ፈተና አወዳድሮ ለማሰልጠን ምዝገባ እያደረገ ነው፡፡

የዘንድሮው ስልጠና በ22 የማሰልጠኛ ተቋማት እና በ23 የህክምና ስፔሻሊቲ ፕሮግራሞች ይሰጣል፡፡

የምዝገባ ጊዜ የሚያበቃው፦
ታህሳስ 20/2018 ዓ.ም

ፍላጎት ያላችሁ አመልካቾች በጤና ሚኒስቴር ድረ-ገፅ (https://www.moh.gov.et) ላይ በመግባት በምትፈልጉት የጤና ስፔሻሊቲ መስክ ማመልከት ትችላላችሁ ተብሏል፡፡

25/12/2025

መዲናዋን የጤና ቱሪዝም ማዕከል የማድረግ ውጥንን በተመለከተ ከአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዮሐንስ ጫላ ጋር የተደረገ ቆይታ

የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ______________ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ...
24/12/2025

የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
______________

ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ፤ ፈተናው በታህሳስ 23 እና 24/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን እየገለፅን፦

1. የፈተናው መርሃ-ግብር
- በ23/04/2018 ዓ.ም…… Public Health, Pharmacy, Medical Laboratory Science, Medical Radiology Technology, Environmental Health እና Human Nutrition
- በ24/04/2018 ዓ.ም…… Medicine, Nursing, Anesthesia, Midwifery, Dental Medicine, Psychiatric Nursing, Emergency and Critical Care Nursing, Pediatric and Child Health Nursing, Surgical Nursing እና Physiotherapy

ሁሉም ተፈታኝ ታህሳስ 22/2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (orientation) መከታተል፤ የቅድመ ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን መስራትና፤ የመፈተኛ ክፍሉን መለየት ይኖርበታል::

2. በፈተናው ዕለት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ (የቀበሌ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ መንጃ ፍቃድ ወይም ሌላ በግልጽ የሚታይ ህጋዊ መታወቂያ) ይዛችሁ መገኘት ይኖርባችኋል፡፡

21/12/2025
20/12/2025

ከተሻሻለ ከሁለት አሰርት ዓመታት በላይ የሆነው #የጤና #ባለሞያዎች #ጥቅማጥቅሞች #ፓኬጅ ( Health Benefit package ) ጊዜውንና የኢኮኖሚ ሁኔታ ታሳቢ ባደረገ መልኩ መመሪያ ማሻሻያ እንደሚደረግ #ከፌደራል #ስቪል #ሰርቨስ #ኮሚሽንና #ከጤና #ጥበቃ #ሚኒስትር እንጠብቃለን ።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Doc Book posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Doc Book:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Category