Nurse to other's

Nurse to other's To help people's

19/06/2022

The Other-Self
ሌላው እኔ
ኡስታዝ በድሩ ሁሴን እንደፃፈው

የሰው ልጅ የክብር ጉዞ የኔና ያንተ ክብር ነው፤ የሰው ልጅ የውርደት እሽቁልቁሊት የኔና ያንተ ውርደት ነው። ከመኪና እያወረዱ የረሸኑን እኔና አንተን ነው፤ ረሻኞችም እኛው ነን።
በወለጋ የተጨፈጨፍነው እኔና አንተ ነን፤ ጨፍጫፊዎቹም እኛው ነን።

የትም ቦታ የሚደርስ ኢሰብአዊነት ከሰውነት ተርታ የሚያስወጣን እኛኑ ነው። ከሰውነት ክብር መውረድ ማለት ወደ እንስሳነት ደረጃ ዝቅ ማለት ነው። እንስሳነት ሲያይል በንፁሃን ደም የሚፎክርና ነውሩ ክብሩ የሆነ ሰው በማህበረሰብ ውስጥ ይበቅላል።

ወንድሜ፣
"ማን ተገደለ?" ብለህ አትጠይቅ፤ የሞትነው እኔና አንተ ነን። "ማን ገደለ?" ብለህም አትጠይቅ፤ የጨፈጨፍነው እኔና አንተ ነን። "ማን ያስቁመው?" ካልከኝ ራሱን "ሰው" ብሎ የሚጠራ ማንኛውም ሰው ሁሉ እልሃለሁ። ፖለቲከኞች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ተፅእኖ ፈጣሪ ግለሰቦች...

አላህ ሆይ! በቃ በለን! የእውነት "ሰው" እንሆን ዘንድ እርዳን።

Address

Haile Gebre Sillase Road
Addis Ababa

Telephone

+251960412319

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nurse to other's posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Nurse to other's:

Share