Medical Information

Medical Information በዚህ ገጽ ጤናን የተመለከቱ የሥራ ማስታወቂያዎች፤ ሕይወታዊ ቁም-ነገሮችና አጠቃላይ መረጃዎችን እንለዋወጥበታለን! Medical Media

23/12/2025

ሼር፣ ኢንቫይት አድርጉና 200K አስገቡን። ለሥራ ተፈልጎ ነው!

CBC machine slightly usedReal buyer call 0944065701Price negotiable
22/12/2025

CBC machine slightly used
Real buyer call 0944065701
Price negotiable

ናይጄሪያ እና አሜሪካ ለአምስት አመት የሚቆይ የ5.1 ቢሊየን ዶላር የጤና ዘርፍ ስምምነት ፈፀሙ።አሜሪካ የክርስትና እምነት ላይ መሰረት ያደረጉ የጤና አገልግሎት ሰጪዎችን በደንብ ያበረታታል ...
22/12/2025

ናይጄሪያ እና አሜሪካ ለአምስት አመት የሚቆይ የ5.1 ቢሊየን ዶላር የጤና ዘርፍ ስምምነት ፈፀሙ።

አሜሪካ የክርስትና እምነት ላይ መሰረት ያደረጉ የጤና አገልግሎት ሰጪዎችን በደንብ ያበረታታል ያለችውን የጤና ስምምነት ከናይጄሪያ ጋር መፈራረሟን ገልፃለች።

አሜሪካ በስምምነቱ መሰረት እንደ ኤችአይቪ፣ ቲቢ፣ ወባ እና ፖሊዮ ያሉ በሽታዎችን ህክምና ለመደገፍ 2.1 ቢሊየን ዶላር ስትሰጥ ናይጄሪያ የጤና ዘርፍ በጀቷን በ3 ቢሊየን ዶላር ትጨምራለች።

አሜሪካ ስምምነቱ ክርስትያኖችን ከጥቃት መጠበቅን ቅድሚያ ይሰጣል ሰትል በልዩነት ድጋፉ የክርስቲያን ጤና ተቋማትን ይመለከታል ብላለች።

አሜሪካ 900 የሚሆኑ የእምነት መሰረት ያላቸው ክሊኒኮችና ሆስፒታሎች ከ30 በመቶ በላይ የሚሆነውን የናይጄሪያ ህዝብ እያገለገሉ ነው ስትል እነዚህን መደገፍ አስፈላጊ ነው ብላለች።

አሜሪካ ስምምነቶቹን በፈለገችው ጊዜ ማቋረጥ እንደምትችል ገልፃ ናይጄሪያ ክርስቲያኖችን ኢላማ ያደረገ የኃይማኖት ጥቃትን በመዋጋት ለውጥ ማምጣት ይኖርባታል ብላለች።

አሜሪካ ተመሳሳይ የጤና ዘርፍ ስምምነቶችን ከዚህ በፊት ከኬንያ ጋር ተፈራርማ ፍርድ ቤት ማገዱ ሲታወስ ከሩዋንዳ እና ኡጋንዳ ጋር ተመሳሳይ ስምምነቶችን ፈፅማለች።

አሜሪካን ቀዳሚ ያደረገውን የጤና ስምምነት በቀጣይ ሳምንትም ከብዙ ሃገራት ጋር እንደሚፈፀም አሜሪካ አስታውቃለች።

22/12/2025

ተራዝሟል !

የ2018 ዓ/ም አጋማሽ ዓመት የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና የምዝገባ ጊዜ ተራዝሟል።

የምዝገባ ጊዜው ከተቋማት በቀረበ ጥያቄ እና ሌሎች ሁኔታዎችን ከግምት በማስገባት እስከ አርብ ታህሳስ 17/2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ስዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

ሁሉም የመንግሥት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተፈታኞች እንዲሁም የግል ተፈታኞች ምዝገባቸውን በተራዘመው ጊዜ እንዲያጠናቅቁ ተብሏል።

" እግዚአብሔር ረድቶን ይህን ልጅ ለማትረፍ ስላበቃን፣ ስላስተማረን ፤ አስተማሪዎቻችንም ይህንን ሞያ ስላስተማሩን ከልብ አመሰግናለሁ " - ዶ/ር ራሄል አበባየሁ🩺" ብዙ ሒደቶችን አልፈን ህክ...
21/12/2025

" እግዚአብሔር ረድቶን ይህን ልጅ ለማትረፍ ስላበቃን፣ ስላስተማረን ፤ አስተማሪዎቻችንም ይህንን ሞያ ስላስተማሩን ከልብ አመሰግናለሁ " - ዶ/ር ራሄል አበባየሁ

🩺" ብዙ ሒደቶችን አልፈን ህክምናውን በስኬት በማጠናቀቃችን ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶኛል " - ዶ/ር ቢኒያም ተሾመ

በሳምሪታን ቀዶ ህክምና ማዕከል (Samaritan Surgical Centre) ለመጀመሪያ ጊዜ በማሽን የተቆረጠ እጅን በተሳካ ሁኔታ መቀጠል መቻሉን የአጥንት ቀዶ ህክምና የከፍተኛ አደጋዎች እና መገጣጠሚያ ቅየራ ሰብ-ስፔሻሊስት ዶ/ር ቢኒያም ተሾመ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ይህንን የተቆረጠ እጅ ወደነበረበት ለመመለስ፦
- የጽዳት ሰራተኞች፣
- የሰመመን ባለሞያዎች፣
- ነርሶች፣
- አናስቴዚዮሎጂስት፣
- የአጥንት ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት፣
- የቫስኩላር ሰርጀሪ ባለሙያ፣
- የፕላስቲክ ሰርጀሪ ባለሙያዎች እና ሌሎችም በርካታ የህክምና ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል ብለዋል።

ዶክተር ቢኒያም ተሾመ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?

" ባለኝ መረጃ መሰረት በሀገራችን የተቆረጠ እጅን ለመቀጠል የተደረጉ የቀዶ ህክምናዎች የሉም። እጁን የቀጠልነት ልጅ ጉዳት የደረሰበት ስጋ ቤት ላይ ማሽን ለማስተካከል በሚሞክርበት ወቅተ ነው።

እጁን ሙሉ በሙሉ ቆርጦትም አልቆመም፣ ደረቱን ቀዶታል፣ ወደ ውስጥ አለመግባቱ ነው እንጂ የደረቱ ጉዳት ከፍተኛ ነበር የሚሆነው።

የልጁ እጅ ከክርኑ በላይ ሙሉ በሙሉ ነው የተቆረጠው፣ ልጁ በአስቸኳይ ወደ ጤና ተቋም መሔድ ችሏል፣ ይህ ትልቅ ነገር ነው፣ የሄደበት ተቋም ጥሩ በመሆኑ ይፈስ የነበረውን ደም በማስቆም የተቆረጠውን እጁን በበረዶ ለብቻው አስቀምጠውታል። ይህም ዳግም ለመቀጠል በጣም ወሳኝ ነው።

በሰአቱ የአጥንት ቀዶ ህክምና ቡድኑ በሳምሪታን ቀዶ ህክምና ማዕከል ሌላ ቀዶ ህክምና እየሰራን ነበረ። ጉዳዩ ተነገረን፣ ፕላስቲክ ሰርጀሪውም በአቅራቢያችን ነበር። ጉዳት የደረሰበት ልጅ በአስቸኳይ እንዲመጣ አደረግን፣ ልጁ እና እጁ እየብቻ ነው የመጣው።

የህክምና ቡድኑ እጁ ቢቀጠል ውጤታማ የመሆን እድል እንዳለው ከሳይንሱ ጋር በመገመት በድፍረት ለመስራት ወስነን መስራት ችለናል።

በደቂቃዎች በእጁ ውስጥ ብረት በማስገባት ለደም ስር ከቀዶ ህክምና ባለሞያዋ በፍጥነት ሰርተን አጠናቀቅን። ከዛም በኋላ vascular surgical ባለሙያዋ ዶክተር ራሔል የደም ስሮቹን የማያያዝ ስራ በሰአቱ ሰርታ ማጠናቀቅ በመቻሏ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጋለች።

አሁን ላይ የሚቀሩ ቀዶ ህክምናዎች አሉ፣ ምክንያቱም የእጅ እንቅስቃሴዎቹን ጋር በተያያዘ መሰራት ያለባቸው ጉዳዮች አሉ። እጁን ማትረፍ ችለናል፣ አንድ ቆዶ ህክምና ይቀረናል። ይህ የእጁን እነቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ባይሆንም እንኳ በበቂ ሁኔታ መመለስ የሚያስችል ነው።

ዋናው ነገር እጁን ማትረፍ ነበር ተሳክቷል፣ የእጅ ስራው ብዙ ነው፣ እግር እና እጅ የሚለያየው መሰረታዊ ነገር ይህ ነው፣ እግር ሲቆረጥ ለመቀጠል ብዙ አያለፋም፣ እጅ ደግሞ ስራው ውስብስብ ነው፣ በወራት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ከእጁ ማግኘት ያለበትን አገልግሎት ያገኛል።

ይህ ቀዶ ህክምና ለተሰራለት ሰው በጣም ትልቅ ነገር ነው፣ እንደ ቀዶ ህክምና ሀኪምም ስራውን በቡድን በስኬት መስራት በመቻላችን ደስ ብሎናል፣ ብዙ ሒደቶችን አልፈን ህክምናውን በስኬት በማጠናቀቃችን ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶኛል።

የመጀመሪያም እንደመሆናችን መጠን ሌላም ጊዜ እንድንሰራ ያደፋፍረናል፣ ማህበረሰቡም ግንዛቤ ይኖረዋል፣ ሌሎች ባለሙያዎችም መስራት እንደሚችሉ እና እጅ ሲቆረጥ መቀጠል እንደሚችሉ ይማሩበታል " ብለዋል።

የደም ሥር ቀዶ ህክምና ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ራሄል አበባየሁ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?

" ቀዶ ህክምናውን ለማከናወን 6 ስአት ወስዶብናል፣ የ20 አመት ወጣት ልጅ ነው። ልጁ በጣም እድለኛ ነው፣ የተቆረጠን እጅ እና እግር ይዞ የመምጣት ባህልም ሆነ ልምድ እንደ ሀገር የለንም። የዚህን ልጅ የተቆረጠ እጁን በበረዶ ያስቀመጡለት የህክምና ባለሙያዎች በጣም ጎበዞች ናቸው። ያለ ኦክስጅን ረጅም ጊዜ መቆየት እንዲችል አድርገውለታል።

የብዙ ሰው እርብርብ ነው ስኬታማ ያደረገው። ከዚህም በሗላ ክትትል እና rehabilitation ያስፈልገዋል። ጥገና ስንሰራ የደም ሁኔታው በጣም እየዋዠቀ ሲያስቸግር ነበር። የደም ዝውውሩን መድሀኒት እየተጠቀምን ነው ያስተካከልነው። ስለሆነም የነርቭ ጥገናው ረፈድ ባለ ጊዜ መሰራት ስለሚችል ቅድሚያ እጁን ለማዳን ባደረግነው ጥረት አሳክተነዋል። በቅርብ ቀን የነርቭ ጥገና እናደርግለታለን።

ጉዳት የደረሰበትን ልጅ እጅህን እንቀጥልልህ የመዳን እድሉ ግን 50/ 50 ነው፣ እንሞክርልህ ብለን ስንጠይቀው እሱም አስታማሚዎቹም ፍቃደኛ ሆነው በጥሩ ሁኔታ ተሰርቶለት ተሳክቶልናል። ይህ ማለት ግን ሁሌም ይሳካል ማለት አይደለም።

እግዚአብሔር ረድቶን ይህን ልጅ ለማትረፍ ስላበቃን፣ ስላስተማረን፣ አስተማሪዎቻችንም ይህንን ሞያ ስላስተማሩን ከልብ አመሰግናለሁ።

እስካሁን ባለው ሂደት በጣም ደስተኛ ነኝ፣ ከዚህም በኋላ ክትትል እና rehabilitation አድርጎ ልጅየው በደንብ Functional ሆኖ እግዚአብሔር ተጨምሮበት እንደምናየው ተስፋ አደርጋለሁ።

የህክምና ቡድኑ መደነቅ አለባቸው፣ እኛ የምንሰራው እግዚአብሔር የፈቀደልንን ብቻ ነው። ሰርተንም ላይሳካልን ይችላል፣ አሁን ላይ ግን ስለተሳካልን ከዚህም በኋላ ገፋፍተን በደንብ መስራት እንደምንችል በማሳየታችን ደስ ብሎኛል " ሲሉ ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደዘገበው!

21/12/2025

“ከኪራይ ቤት ለመውጣት አስበዋል!?”

አያስቡ፣ ተሥማምተው ይቀመጡ!

የደብረ ብርሃን ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተለያዩ የሙያ መስኮች  ያሠለጠናቸውን 161 ተማሪዎች አስመረቀ!
21/12/2025

የደብረ ብርሃን ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተለያዩ የሙያ መስኮች ያሠለጠናቸውን 161 ተማሪዎች አስመረቀ!

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የጤና ሠራተኞች የትርፍ ሰዓት የሚፈቀድበት ሁኔታ እና ክፍያ ለመወሠን የወጣው መመሪያ በፍትህ ሚኒስቴር መመዝገቡን ገልጿል። "የመንግሥት ጤና ተቋማት ሠራተኞች...
20/12/2025

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የጤና ሠራተኞች የትርፍ ሰዓት የሚፈቀድበት ሁኔታ እና ክፍያ ለመወሠን የወጣው መመሪያ በፍትህ ሚኒስቴር መመዝገቡን ገልጿል።

"የመንግሥት ጤና ተቋማት ሠራተኞች የትርፍ ሰዓት የሚፈቀድበት ሁኔታ እና ክፍያ ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 1119/2018" በሚል የተመዘገበው መመሪያ በሚመለከታቸው ተቋማት ተግባራዊ እንዲሆን የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ታህሳስ 7/2018 ዓም በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል።

ረቂቅ መመሪያው የተዘጋጀው በጤና ሚኒስቴር ሲሆን ረቂቁ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከታየ እና ከተገመገመ በኋላ በፍትህ ሚኒስትር መመዝገቡን ደብዳቤው ያትታል።

ቲክቫህ መመሪያው ትክክለኛ ስለመሆኑ እና ተግባራዊ እንዲሆን ስለመላኩ ከሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አረጋግጧል።

(በዝርዝር መመሪያውን ከተያያዘው ፋይል ይመልከቱ)


Medical Information

ብራዚል ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፍን ኤችአይቪ በመግታቷ ከአለም ጤና ድርጅት እውቅና ተሰጥቷታል። World Health Organization (WHO) ብራዚል ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፍን ኤች...
20/12/2025

ብራዚል ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፍን ኤችአይቪ በመግታቷ ከአለም ጤና ድርጅት እውቅና ተሰጥቷታል። World Health Organization (WHO)

ብራዚል ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፍን ኤችአይቪ የገታች በሁለቱ የአሜሪካ አህጉራት ብዙ ህዝብ ያላት ሃገርም ሆናለች።

የአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሃኖም(ዶ/ር) ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፍን ኤችአይቪ መግታት መቻል ለየትኛውም ሃገር ትልቅ ስኬት ነው ያሉ ሲሆን በተለይም እንደ ብራዚል ትልቅና ውስብስብ ለሆነ ሃገር ትልቅ የህብረተሰብ የጤና ስኬት ነው ብለዋል።

ብራዚል በፖለቲካ ቁርጠኝነትና የጤና አገልግሎትን በማስፋፋት ማሳካት እንደሚቻል አሳይታለች ያሉት ዳይሬክተሩ ሁሉም ህፃን ያለ ኤችአይቪ እንዲወለድ ሁሉም ሃገር ማድረግ ይችላል ብለዋል።

ኩባ ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፍን ኤችአይቪ በ2015 በመግታት ቀዳሚዋ ሃገር ስትሆን ከብራዚል ጋር 19 ሃገራት እስካሁን ይህንን ስኬት ማሳካት ችለዋል።

ከእነዚህ ሃገራት 12ቱ በካሪቢያን የሚገኙ ሲሆን የተቀሩት በአውሮፓ እና እስያ ይገኛሉ።

 #ጥቆማቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም በኅብረተሰብ ጤና ትምህርት የፒኤችዲ ፕሮግራም (PhD in Public Health) ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡የምዝገባ...
19/12/2025

#ጥቆማ

ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም በኅብረተሰብ ጤና ትምህርት የፒኤችዲ ፕሮግራም (PhD in Public Health) ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡

የምዝገባ ጊዜ፦
ከታህሳስ 09-25/2018 ዓ.ም

የፈተና/Synopsis ማቅረቢያ ቀናት፦
ጥር 07 እና 08/2018 ዓ.ም

ለመመዝገብ ተከታዩን ሊንክ ይጠቀሙ 👇
https://portal.sphmmc.edu.et/Web/Announcement

(ዝርዝር መስፈርቶችን ለማግኘት የኮሌጁን ድረ-ገፅ https://sphmmc.edu.et/ ይጎብኙ፡፡)

19/12/2025

እንኳን ደስ አላችሁ፣ ዲቪ ታግዷል 😅

በግዙፉ   ዶ/ር Abrham Amare ከፍተኛ ልምድ ያካበተ የአጥንትና መገጣጠሚያ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ሃኪም  ሲሆኑ ዘወትር ከሰኞ እስከ እሁድ ባሉት ቀናት በአገው ምድር ጠቅላላ ሆስፒታል...
19/12/2025

በግዙፉ
ዶ/ር Abrham Amare ከፍተኛ ልምድ ያካበተ የአጥንትና መገጣጠሚያ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ሃኪም ሲሆኑ ዘወትር ከሰኞ እስከ እሁድ ባሉት ቀናት በአገው ምድር ጠቅላላ ሆስፒታል ማግኘት ይችላሉ፡፡

@አገው ምድር ጠቅላላ ሆስፒታል/Agew Midir General Hospital
አድራሻችን፡- እንጅባራ ከተማ ቻግኒ መውጫ ላይ ያገኙናል፡፡

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Medical Information posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Medical Information:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Our Story

Feed Health Information