09/05/2026
በ2018 ዓ.ም ለሬዚደንሲ ስልጠና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ሐኪሞች የምዝገባ ጊዜ ግንቦት 06 እና 07/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦
➫ የብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ሰርተፊኬት፣
➫ የስፖንሰርሺፕ ደብዳቤ (በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስፖንሰር ለተደረጋችሁ)፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስከሪፐት ዋናውና ኮፒው እንዲሁም የ8፣ 10 እና 12ኛ ከፍል ሰርተፊኬቶች፣
➫ ስትሰሩበት ከነበረ መስሪያ ቤት የመልቀቂያ ደብዳቤ፣
➫ ሁለት ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ
አስቀድማችሁ ለወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሳላይዝድ ሆስፒታል ፖ.ሳ.ቁ. አድራሻ 200 የመጀመሪያ ዲግሪ ኦፊሻል ትራንስክሪፕት ማስላክ እንዳለባችሁ ተገልጿል፡፡