Medical Information

Medical Information በዚህ ገጽ ጤናን የተመለከቱ የሥራ ማስታወቂያዎች፤ ሕይወታዊ ቁም-ነገሮችና አጠቃላይ መረጃዎችን እንለዋወጥበታለን! Medical Media

09/05/2026



በ2018 ዓ.ም ለሬዚደንሲ ስልጠና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ሐኪሞች የምዝገባ ጊዜ ግንቦት 06 እና 07/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦
➫ የብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ሰርተፊኬት፣
➫ የስፖንሰርሺፕ ደብዳቤ (በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስፖንሰር ለተደረጋችሁ)፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስከሪፐት ዋናውና ኮፒው እንዲሁም የ8፣ 10 እና 12ኛ ከፍል ሰርተፊኬቶች፣
➫ ስትሰሩበት ከነበረ መስሪያ ቤት የመልቀቂያ ደብዳቤ፣
➫ ሁለት ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ

አስቀድማችሁ ለወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሳላይዝድ ሆስፒታል ፖ.ሳ.ቁ. አድራሻ 200 የመጀመሪያ ዲግሪ ኦፊሻል ትራንስክሪፕት ማስላክ እንዳለባችሁ ተገልጿል፡፡

09/05/2026
🎇 Only 2 DAYS TO GO!We’re excited for the National Data and Digital Health Week 2026, organized by MoH and CDHI!Get read...
09/05/2026

🎇 Only 2 DAYS TO GO!
We’re excited for the National Data and Digital Health Week 2026, organized by MoH and CDHI!

Get ready for impactful discussions, innovations, and collaborations driving Ethiopia’s digital health future.

💥

ዝውውር 💥
09/05/2026

ዝውውር 💥

 "ተጥለህ ነው ያገኘንህ"በዶክተር ኃይለልዑል መኮንን (የአዕምሮ ሕክምና ስፔሻሊስት)በአብዛኞች የልጅነት ጊዜ የማይጠፋ ጨዋታ መሳይ ቀልድ አለ። " ተጥለህ እኮ ነው ያገኘንህ፤ ከጓሮ አግኝተን...
08/05/2026



"ተጥለህ ነው ያገኘንህ"

በዶክተር ኃይለልዑል መኮንን (የአዕምሮ ሕክምና ስፔሻሊስት)

በአብዛኞች የልጅነት ጊዜ የማይጠፋ ጨዋታ መሳይ ቀልድ አለ። " ተጥለህ እኮ ነው ያገኘንህ፤ ከጓሮ አግኝተንህ ነው እንጂ አንተ የኛ ልጅ አይደለህም። "

ሰሞኑን አንዲት ታካሚዬ የልጅነት ትውስታዋን ስታጋራኝ፣ ይህ ንግግር ለዓመታት በውስጧ የፈጠረውን ባዶነትና የባዕድነት ስሜት ገልፃልኛለች። ምንም እንኳን በጨወታ መሀል ወላጆች ይህን ቀልድ ቢያነሱም ለልጆች ግን የማንነት ጥያቄ የሚያስነሳ የጭንቀት ምንጭ ሊሆን ይችላል።

ህጻናት ዓለምን የሚያዩት በወላጆቻቸው አይን ነው። ወላጅ " የኛ አይደለህም " ሲል ልጁ የሚሰማው የመተው ፍርሃት እንዲሁም " እነዚህ ሰዎች ካልወለዱኝ ነገ ሌላ ሰው መጥቶ ቢወስደኝስ ? ወይም እነሱ መልሰው ቢጥሉኝስ ? " የሚል ጭንቀት በውስጡ ሊፈጠር ይችላል።

ልጅነት " እኔ ማን ነኝ ? " የሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚያገኝበት ወሳኝ ወቅት እንደመሆኑ ከጓሮ ተገኘህ የሚለው ቃል ልጁን ከማንነቱ በመነጠል ራሱን ሲያይ በቤተሰቡ መሃል እንደ እንግዳ እንዲሰማው ያደርገዋል። በእያንዳንዱ ግጭት ወይም ቅጣት ወቅት፣ ልጁ ያንን የጓሮ ታሪክ ያስታውሳል። " የእነርሱ ስላልሆንኩኝ ነው የሚቆጡኝ " ብሎ እንዲያስብና የራሱን ማንነት እንዳይቀበል እንዲሁም ሁልጊዜ ተቀባይነት ፍለጋ እና " እኔ እዚህ ቦታ አይገባኝም " የሚል የበታችነት ስሜት ሊያሳድርበት ይችላል።

" ተጥዬ የተገኘሁ ስለሆንኩ ዋጋ እንዲኖረኝና እንዳይጥሉኝ ሁልጊዜ ሰዎችን ማስደሰት አለብኝ " የሚል የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ ሊደርስ ይችላል። ይህም የራሱን ፍላጎትና ስሜት ደብቆ ለሌሎች ይሁንታ ብቻ የሚኖር ስብዕና እንዲላበስ ሊያደርገዉ ይችላል። ወደፊትም የፍቅር ሆነ የጓደኝነት ግንኙነት ሲመሰርት ሰዎችን ለማመን ይቸገራል። ሰዎች አንድ ቀን ጥለውኝ ይሄዳሉ የሚል ስጋት ስላለዉ ወይ ራሱን ቀድሞ ያገላል ካልሆነ ከመጠን በላይ ሰዎች ላይ ሊጣበቅ ይችላል። ታካሚዬ ላይ ያየሁትም ይሄንኑ ነበር።

ይህ ቀልድ መሳይ ጨዋታ በልጆች እያደገ ባለ ስነልቦና ላይ ከባድ አሻራ ይጥላልና መቅረት ያለበት ልማድ ነዉ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ



Notice from University of Gondar
08/05/2026

Notice from University of Gondar

NOTICE
08/05/2026

NOTICE

Hantavirus: A silent, climate-sensitive threat that demands better early warning systemsHantavirus pulmonary syndrome (H...
08/05/2026

Hantavirus: A silent, climate-sensitive threat that demands better early warning systems
Hantavirus pulmonary syndrome (HPS) has a high case fatality rate, yet it often remains under the radar - until an outbreak happens.

Rodent populations surge with rainfall, temperature shifts, and land use changes. That means hantavirus outbreaks are predictable, if we integrate climate, environmental, and surveillance data.
Yet, in many regions, early warning capabilities remain weak.
Key takeaways from recent global health work (e.g., Exemplars in Global Health):
Advance warning requires cross-sector data (climate, ecology, human cases)
One Health platforms enable faster detection and response
Sustainable financing for surveillance saves lives
Hantavirus won't wait for us to be ready. Let's build systems that see it coming.

🔼  የብቃት ምዘና ፈተና መረጃ በማረጋገጥ ላይ የምትገኙ የጤና ሙያ ተመራቂዎች የመረጃ ማረጋገጫ ቀነ ገደቡ እስከ ግንቦት 07/2018 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡በግንቦ...
08/05/2026

🔼

የብቃት ምዘና ፈተና መረጃ በማረጋገጥ ላይ የምትገኙ የጤና ሙያ ተመራቂዎች የመረጃ ማረጋገጫ ቀነ ገደቡ እስከ ግንቦት 07/2018 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

በግንቦት ወር የሚሰጠውን የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ የምትገኙ የጤና ሙያ ተመራቂዎች የብቃት ምዘና ፈተና መለያ ቁጥራችሁን (Registration Number) ከብሔራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥራችሁ (16 Digit FAN) ጋር የማረጋገጥ ሥራ እስከ ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም ድረስ https://hple.moh.gov.et/ ሊንክን በመጫን እንድታከናውኑ መባሉ ይታወቃል፡፡

የመረጃ ማረጋገጫ ቀነ ገደቡ እስከ ግንቦት 07/2018 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን ሚኒስቴሩ አስገንዝቧል፡፡

08/05/2026
🏆 Call for Nominations: University of Gondar Annual Health Award 2025/26Do you know an individual, team, or institution ...
07/05/2026

🏆 Call for Nominations: University of Gondar Annual Health Award 2025/26

Do you know an individual, team, or institution making a lasting impact on Ethiopia's health sector? Now is the time to celebrate them.

The University of Gondar is proud to announce the Annual Health Award 2025/26 - honoring excellence across four categories:

① Lifetime Achievement in Health Service
② Community Health Champion
③ Health Research Excellence
④ Health Educator/Mentor Excellence

Who can be nominated?
● Ethiopian and international individuals, teams, and institutions whose work has demonstrably improved health outcomes in Ethiopia - whether through research, service delivery, education, leadership, or community engagement.

Why nominate?
● Winners will be formally recognized during the University of Gondar Graduation Ceremony and will become part of the UoG Health Impact Network, a platform for continued collaboration and influence.

Submit your nomination today!

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Medical Information posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Medical Information:

Share