Gandhi Memorial Hospital ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል

Gandhi Memorial Hospital                  ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል Gandhi Memorial Hospital is a pioneer Maternal and Neonatal Health Hospital located in Addis Ababa E

" ዜሮ... " ይሁንልን!!!!ከሠዉ ቤት እንጀራ አልጫ መረቁየእናት እጅ ይጥማል ዘንጋዳዉ ደረቁእናት ለምን ትሙት ትሂድ አጎንብሳየምታሳድግ ናት በችግር ተጠብሳ...           (ይቀጥላል...
03/02/2026

" ዜሮ... " ይሁንልን!!!!

ከሠዉ ቤት እንጀራ አልጫ መረቁ
የእናት እጅ ይጥማል ዘንጋዳዉ ደረቁ
እናት ለምን ትሙት ትሂድ አጎንብሳ
የምታሳድግ ናት በችግር ተጠብሳ...

(ይቀጥላል)

ከላይ ያለዉን ስንኝ የወሰድኩት አንጋፋዉ ድምጻዊ አለማየሁ እሸቴ በ1962 ዓ.ም ከተጫወተዉ ግሩም ዜማ ላይ ነዉ።

በምድር ላይ ከእናት ሞት በላይ መራር ሀዘን የለም ! ሞት የማይቀር የተፈጥሮ ግዴታ ቢሆንም ድምጻዊዉ እንዳለዉ
እናት ዝንተ-ዓለም አብራን ብትኖር የሁላችንም ምኞት ነዉ!

አይሆንም እንጂ ሎሬት ፀጋዬ " ሞትም ይሙት ፤ የት አባቱ" ያለዉ ቢሆን ሠርግና ምላሽ ነበር። የባለቅኔዉ ሀሳብ እንደተጠበቀ ሆኖ... የእናት ሞትን ማዳን እየተቻለ ህይወት ሲያልፍ ....ልብ ይሰብራል...! ቅስም ያደቃል ...! በተለይ ልትወልድ ሄዳ እናት ስትሞት...!!! አስባችሁታል ....

የመንደርደሪያዉ ሀሳብ ወደ ቀኝ ወደ ግራ ሳይል የሚያርፈዉ በሆስፒታላችን በዛሬዉ ዕለት በድምቀት የተከበረዉን የጤናማ እናትነት ወርን ይመለከታል።

" ፈጠራ እና ዘላቂ ፋይናንስ ለጤናማ እናትነት " በሚል መሪ ቃል በተሰናዳዉ መርሃ-ግብር ላይ ዋና ስራ አስኪያጁ ዶ/ር ታሪኩ ደሬሳ ካደረጉት ንግግር ዉስጥ የሚከተለዉን አጽንኦት እሰጣለሁ!

" በሀገር አቀፍም ይሁን በከተማ ደረጃ በርካታ እናቶችን በማዋለድ ቅድሚያዉን እንይዛለን። በዓመት 10,000 ገደማ እናቶች እኛ ጋር ወልደዉ ይስማሉ። "

( ስራ እስኪያጁ ቀጥለዋል...)

"እንደ ጋንዲ አንድ መፈክር አለን ...እሱም የእናት እና ህጻናት የሞት ቁጥርን መቀነስ ሳይሆን ዜሮ ማድረግ ነዉ! አንድ እናት እኛ ጋር ስትሞት ቁጥሩ ለኛ 1 ብቻ ነዉ ፣ ለቤተሰቦቿ ግን 100% ጥልቅ ሀዘን ነዉ...በዚህ መነሻነት ግባችንን ለማሳካት የአገልግሎት ጥራትን በተመለከተ ቀን ከ ሌት እየሠራን እንገኛለን ...ዉጥናችን እንደሚሳካም እርግጠኛ ነኝ..." ብለዋል።

ወ/ሮ አንጋቱ መሀመድ የከተማችንን ጤና ቢሮ በምክትልነት ይመራሉ። " አናቶች ያለ ምንም ችግር በሰላም ተገላግለዉ እንዲያዩ በሙያቸዉ እያገለገሉ ላሉ የጤና ባለሙያዎች ምስጋና አቀርባለሁ ። ....እንደ ሀገር የእናቶች እና ህፃናትን ሞት ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መቀነሳችንን የአለም ጤና ድርጅት ሳይቀር እዉቅና ሰጥቶናል። ...እኛ ግን አላማችን በወሊድ ምክንያት የሚመጣን የእናቶች እና ህጻናትን ሞት ከነጭራሹ ማስቀረት ነዉ" ብለዉናል።

በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ደ.ኤ.ታ አማካሪዉ አቶ ዬናስ ዙላ
ከተናገሩት መሀከል " በሀገራችን የእናቶች እና ህጻናት የሞት ምጣኔ መቀነሱ ለጉዳዩ ትኩረት እንደተሠጠ ማሳያ ነዉ " ያሉትን አስምሬበታለሁ።

በመቀጠልም ከተለያዩ ተቋማት በመጡ ባለሙያዎች የፓናል ዉይይት ተደርጎ ፣ የእናቶች ጤና ላይ ያተኮረ አዉደ-ርዕይ በታዳሚዎቹ ተጎብኝቶ የመርሃ-ግብሩ ማሳረጊያ የነበረዉ ክብርት ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ሆስፒታሉን በጎበኙበት ወቅት " ቢሆን ጥሩ ነዉ ...." ብለዉ የሰጡትን አስተያየት ተከትሎ የተሠሩ የማሻሻያ ስራዎች ተጎብኝተዉ ይሁንታን አግኝተዋል። ጎን ለጎንም በህክምና ላይ ለማገኙ እናቶች የተለያዩ ስጦታዎች ተበርክቶላቸዉ እንግዶቹ ተሸኝተዋል።

26/05/2018

"ተዉ ልመድ ገላዬ..." ....በ "ወርቃማ ሰኞ" ተገናኘን ...ቀልደኛ ናቸዉ። ሳቅ ጨዋታ ይወዳሉ ! ደማቅ ፈገግታ መሸለም አይሰለቻቸዉም። ከሊቅ እስከ ደቂቅ ባሉ ሙያተኞች ይወዳሉ! ይከበራ...
02/02/2026

"ተዉ ልመድ ገላዬ..." ....

በ "ወርቃማ ሰኞ" ተገናኘን ...

ቀልደኛ ናቸዉ። ሳቅ ጨዋታ ይወዳሉ ! ደማቅ ፈገግታ መሸለም አይሰለቻቸዉም። ከሊቅ እስከ ደቂቅ ባሉ ሙያተኞች ይወዳሉ! ይከበራሉ ። ሲበዛ ግልጽ ናቸዉ ! የተመለከቱትን ጥሩ ነገር ያደንቃሉ! ጎደለ የሚሉትንም ያርማሉ ! ይመክራሉ ይዘክራሉ! የከፋ ከሆነ ደግሞ ቆፍጠን ብለዉ ይገስፃሉ! በአጭሩ ተራማጅ ናቸዉ።

እኚህ ሠዉ ማን ናቸዉ ? ካሉ.....ጉምቱዋ ሀኪም!... የጽንሰ እና የማህጸን ስፔሻሊስት እንዲሁም የስነ-ተዋልዶ ሰብ-ስፔሻሊስቷ ዶ/ር ማህሌት ይገረሙ የዛሬ ባለ ተራ ናቸዉ።

ቀጥለናል....

ዶ/ር ማህሌት ተወልደዉ ያደጉት ፣ እስከ ዶክትሬት ድረስ የተማሩት!... ተኩለዉ ...ተድረዉ ...ወልደዉ.. የከበዱት እዚሁ አዲስ አበባ ነዉ።

ለ 21 ዓመታት በጥቁር አንበሳ በህክምና እና በመምህርነት ሙያዊ ግዴታቸዉን ተወጥተዋል። ተማሪዎቻቸዉ "እናት የሆነች ሠዉ!" በማለት ያሞካሿቸዋል። የሙያ አጋሮቻቸዉ በስራ ላይ ደከመኝ ሠለቸኝ እማያዉቁ ጠንካራ ሀኪም ስለመሆናቸዉ ይመሰክራሉ።

ዘለግ ላሉ ዓመታት ካገለገሉበት ጥቁር አንበሳን በመልቀቅ ከሰኔ 2017 ዓ.ም ጀምሮ ጋንዲ መታሰቢያን የተቀላቀሉት ወደዉ እና ፈቅደዉ መሆኑን ነግረዉናል።

" ለጋንዲ ያለኝ ፍቅር አሁን የመጣ አይደለም! ከተማሪነት ግዜ ጀምሮ የከረመ ፍቅር ነዉ...." ሲሉ የልባቸዉን ገልጸዋል።

ዶ/ር ቀጥለዋል ....

"ጋንዲ ከመጣሁበት ግዜ ጀምሮ በተመለከትኩት ነገር ተደስቻለሁ። በተለይ ነርሶቹ ....ለስራቸዉ ሟች ናቸዉ!..ታካሚዎችን ጠብ እርግፍ ብለዉ ያስተናግዳሉ ! እንዲህ አይነት የአገልግሎት አሰጣጥ የትም አላየሁም " በማለት የሆስፒታሉን ባለሙያዎች በየፈርጁ አመስግነዋል።

ሌላም ነገር አለ ! ይላሉ ሀኪሟ....." ጋንዲ ሆስፒታል ዉስጥ ያለዉ መንፈስ ቤተሰባዊ ነዉ። ሁሉም ይከባበራል! ሁሉም ይሸፋፈናል! ሁለም በግልጽ ሀሳቡን ይናገራል!!!." ሌላዉ አሉ ዶ/ር ማህሌት "የሆስፒታሉ ማኔጅመንት ለሙያተኛዉ ቅርብ
ነዉ! ቢሮክራሲ የሚባል ነገር የለም..." በማለት በገባቸዉ እና በተረዱት ልክ መስክረዋል።

የሶስት ልጆች እናት የሆኑት ሀኪም ከስራ በኋላ በትርፍ ግዜያቸዉ ሙዚቃ የማድመጥ ዝንባሌ አላቸዉ። በተለይ የማህሙድ አህመድ አድናቂ ነኝ ይላሉ!!! የድምጻዊዉ
"ተዉ ልመድ ገላዬ ..." የሚለዉን ዜማ በልዩነት እንደሚወዱት
አክለዉም "ሙዚቃ ሳዳምጥ ግጥሙ ላይ ትኩረት አደርጋለሁ!!! በዚህ ምክንያት አሁን ላይ የሚወጡ የሙዚቃ ስራዎችን አላደምጥም...ግጥማቸዉ ስለማይሰማ "ብለዋል።

"ከቅርብ ጊዜ ድምጻዊያን የፀደኒያ ገ/ማርቆስ እና በሞት የተለየን የእዬብ መኮንን ዜማዎች ይጥሙኛል። ... አቤት ...የእዬብ ግጥሞች ልዩ ናቸዉ።" ....(በአድናቆት)

ዶ/ር ማህሌት እረፍት ሲያሻቸዉ ፊልም ማየት እና መጽሀፍት ማንበብ እንደሚወዱ አጫዉተዉናል።

ተወዳጇን ዶ/ር ማህሌት ይገረሙን ፈጣሪ ረጅም እድሜ ከጤና ጋር ያድልዎ ብለን መርቀናል!!!

25/05/2018

በይነ-መረብን መሠረት ያደረጉ በእጅጉ የረቀቁ ወንጀሎች ከግዜ ወደ ግዜ መልካቸዉን በመቀየር የዓለም ስጋት ሆነዋል። በዚህም መነሻነት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) ከጋን...
28/01/2026

በይነ-መረብን መሠረት ያደረጉ በእጅጉ የረቀቁ ወንጀሎች ከግዜ ወደ ግዜ መልካቸዉን በመቀየር የዓለም ስጋት ሆነዋል።

በዚህም መነሻነት የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) ከጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ጋር በመተባበር ያሰዱት በሳይበር ደህንነት ላይ ያተኮረ ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በዛሬዉ ዕለት በሆስፒታሉ የስልጠና ማዕከል ተካሂዷል።

የሆስፒታሉ ሚዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ኃይለገብርኤል ኪዳኔ ርዕሰ-ጉዳዩ ከዕለት ተዕለት ተግባራት እና አስራር ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለዉ በመሆኑ መድረኩ አስፈላጊ ብሎም ዘመኑን የዋጀ ነዉ ብለዋል።

ከደህንነት አስተዳደሩ በመጡ ባለሙያ የተመራዉ መድረክ የሳይበር ምንነት፣ የሳይበር ጥቃት ለምን ? እና እንዴት? የዲጂታል ዓለም ተጽእኖ እንዲሁም የሳይበር ጥቃት ከመድረሱ በፊት ቅድመ ጥንቃቄ በማድረግ እንዴት መከላከል ይቻላል? በሚሉ ዝርዝር ጉዳዬች ላይ ነባራዊ ሁኔታን ባገናዘበ መንገድ ማብራሪያ እና ትንታኔ ቀርቧል።

በስልጠና ማዕከሉ እየተከናወኑ ያሉ የአቅም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረዉ መቀጠላቸዉ ይበል የሚያሰኝ ሆኖ አግኝተነዋል!!!

20/5/2018

በ"ወርቃማ ሰኞ" እነሆ ተገናኘን .....የዛሬዋ ባለተራ ሲስተር ሰብለ ተፈራ ነበረች። ሲስተር ተወልዳ ያደገችዉ አ/አ ልዩ ስሙ 3 ቁጥር ማዞሪያ ተብሎ የሚጠራዉ ቦታ መሆኑን ነግራናለች። የነ...
26/01/2026

በ"ወርቃማ ሰኞ" እነሆ ተገናኘን .....

የዛሬዋ ባለተራ ሲስተር ሰብለ ተፈራ ነበረች። ሲስተር ተወልዳ ያደገችዉ አ/አ ልዩ ስሙ 3 ቁጥር ማዞሪያ ተብሎ የሚጠራዉ ቦታ መሆኑን ነግራናለች። የነርሲንግ ትምህርቷን ሜድኮ ባዬ ሜዲካል ኮሎጅ እንደተማረችም አዉግታናለች።

ሲስተር ትምህርቷን አጠናቃ ወደ ስራዉ አለም የዘለቀችዉ ኬንያ ጠረፍ የሚገኘዉ "አማሮ" ልዩ ወረዳ በማቅናት እንደነበረ በትዝታ መለስ አርጋናለች። በስፍራዉ የገጠሟትንም ከባቢያዊ ፈተናዎች በዝርዝር ተናግራለች።

በወቅቱ ትላለች ሲስተር ሰብለ.... በየዕለቱ የ19 ኪሎ ሜትር ርቀት በእግር የመጓዝ ግዴታ ዉስጥ መግባቷን እንዲሁም በስፍራዉ ምንም አይነት የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዳልነበረ ሁኔታዉም ከተማ ተወልዶ ላደገ ሠዉ በእጅጉ ፈታኝ እንደነበረ አስታዉሳለች።

ወጉ እንደቀጠለ ነዉ....

ሌላዉ ከባዱ ፈተና በወረዳዉ በተደጋጋሚ በተለያዩ ጉሳዎች መሀከል ይከሰቱ የነበሩ ግጭቶች ለህይወት ስጋትን የጋረጡ በመሆናቸዉ ከሁለት ዓመታት ቆይታ በኋላ "ጨርቄን ማቄን " ሳትል ስፍራዉን ለቃ ወደ አዲስ አበባ እንደተመለሰች ገልጻለች።

ሲስተር ሰብለ የንባብ ልምድ እንዳላት በተለይ መጽሃፍ ቅዱስን ማንበብ ፣ መዝሙር ማዳመጥ እንዲሁም ወደ ቤተ-ዕምነት መመላለስ ሠርክ የምትከዉናቸዉ ተግባራት መሆናቸዉን ነግራናለች።

ባለ ተራዋ አቅራቢ ከ 2011 ዓ.ም ጀምሮ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታልን በመቀላቀል በተለያዩ መደቦች ላይ የሠራች ሲሆን አሁን ላይ የአንቡላንስ ቡድን መሪ ሆና በማገልገል ላይ ትገኛለች።

18/05/2018

22/01/2026

እነሆ ብለናል ...! የምስራች ....በአክብሮት ተጋብዘዋል!!!
ስትጠብቁት የነበረዉ ተጀምሯል!!! ኑ እንጂ!!!
14/05/2018
👉 Follow us on tiktok
https://www.tiktok.com/?_r=1&_t=ZM-91G3us8dOF2

የአዕምሮ ህመም ምንነቶች እና መንስኤዎቻቸዉ እንዲሁም መፍትሄዎቻቸዉ በሚል ርዕሰ ጉዳይ የማህበረሰብ ተኮር ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ በሆስፒታሉ የስልጠና ማዕከል በዛሬዉ ዕለት ተካሂዷል።ከጤና ...
21/01/2026

የአዕምሮ ህመም ምንነቶች እና መንስኤዎቻቸዉ እንዲሁም መፍትሄዎቻቸዉ በሚል ርዕሰ ጉዳይ የማህበረሰብ ተኮር ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ በሆስፒታሉ የስልጠና ማዕከል በዛሬዉ ዕለት ተካሂዷል።

ከጤና ሚኒስቴር በመጡ የዘርፉ ባለሙያዎች የተመራዉ መድረክ ስለ አዕምሮ ህመም የተዛባ አመለካከት ላይ ያተኮረ ነበር። ህመሙ ተገቢዉ የህክምና ክትትል ከተደረገ መዳን እንደሚቻል የተገለጸ ሲሆን በሀገራችን ግን ወደ ህክምና ቦታ የሚሄዱት በጣም ጥቂቶች መሆናቸዉ ታዉቋል።

በዚህ ጉዳይ ላይ የአመለካከት ለዉጥ ለማምጣት የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በጥምረት መስራት እንዳለባቸዉ ተመላክቷል።

13/02/2018

ዛሬ ማለዳ በጃንሜዳ ተገኝተን ለጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት መታሰቢያ በዓል እንኳን አደረሳችሁ ብለናል።ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ከሀጥያት ሞት በፍቅር፣  በምህረቱና በርህራሄው...
19/01/2026

ዛሬ ማለዳ በጃንሜዳ ተገኝተን ለጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት መታሰቢያ በዓል እንኳን አደረሳችሁ ብለናል።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ከሀጥያት ሞት በፍቅር፣ በምህረቱና በርህራሄው ሊያድን ሰውን መስሎ ከድንግል ማሪያም በቤተልሔም ተወልዶ፣ በዮርዳኖስ ተጠምቆ ለዓለም እንደተገለጠው ሁሉ፤ እኛም የጥምቀቱን ዓላማ ተረድተን በእለት እለት ህይወታችን ልንኖረው ይገባል።

ይህም ከቂምና ከጥላቻ ተላቀን፤ ከቂም ይልቅ ይቅርታን፣ ከልዩነት ይልቅ አንድነታችንን በማስቀደም በሀገራዊ ጉዳዮቻችን ላይ በመምከር የጥል እና የጥላቻ ግድግዳዎችን እናፍርስ ።

በምትኩም የፍቅር፣ የሰላም፣ የይቅርታ እና የአንድነት ድልድዮችን መገንባት ይጠበቅብናል።
የጥምቀት በዓል የእምነት መግለጫ ብቻ ሳይሆን፤ የአንድነታችን፣ የመፈቃቀራችን የሰላማችንና የኢትዮጵያዊ ጨዋነት መገለጫ የጋራ ውበታችን ነጸብራቅም ነው።

መልካም በዓል በድጋሚ!
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

19/01/2026
18/01/2026

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!!

በክርስቲያኖች ዘንድ ጥምቀት የመገለጥ፣ የእርቅና ዳግም የመወለድ ምልክት ነው። ከሀገራችን ደማቅ የአደባባይ በዓላት አንዱ የሆነው የጥምቀት በዓል ድንቅ ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ እሴቶች ጎልተው የሚታዩበት ከመሆኑ ባሻገር፤ በዓለም የማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበ በርካታ የውጭ ሃገር ቱሪስቶች የሚታደሙበት፣ የሃገራችንን መልካም ገጽታ ለዓለም የሚያስተዋውቅ ደማቅ በዓል ነው።
ይህንን ውብና ደማቅ በዓል ከሀይማኖታዊ ልዩ ሥርዓቶቹ በተጨማሪ ባህላችንን፣ ቋንቋችንን፣ ዜማችንን፣ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በአደባባይ የምናሳይበት በመሆኑ በኢትዮጵያዊ ጨዋነትና እንግዳ ተቀባይነት ባህል፣ ሃይማኖታዊ ስረዓቱንና እሴቶቹን ጠብቆ በማክበር የበለጠ ሀገራችንን ለዓለም እናስተዋቅበታለን።

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የአብሮነት እንዲሆን እመኛለሁ።

መልካም በዓል!

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ !

Baga ayyaana cuuphaa gooftaa Iayyasuus Kiristoosiin isin gahe nu gahe!

Kisristaanota biratti Cuuphaan, mul'istuu ifatti bahuu, araaraa fi irra deebiin dhalachuuti. Ayyaanota addabaabaayii biyya keenyaa bifa miidhagaan kabajaman keessaa tokko kan ta'e ayyanni Cuuphaa duudhaaleen ajaa'ibaa amantaa fi aadaa guddatanii kan itti mul'atan ta'uun alatti, hambaa hin tuqamamne addunyaatti kan galmaa'e, turistoonni biyya alaa hedduun kan irratti hirmaatan, fuula gaarii biyya keenyaa addunyaaf ayyaana beeksisuudha.
Ayyana miidhagaa fi hoo'aa kana sirnoota addaa amantaa dabalatee aadaa keenya, afaanota keenya, faaruulee keenya, tokkummaa sab-daneessummaa keenyaa, addabaabaayitti kan itti mul'isnu waan ta'eef aadaa gaarummaa fi keessummaa simachuu Itoophiyummaatiin duudhaafii sirna amantaasaa eeguun kabajuun caalaatti biyya keenya addunyaaf ittiin ni beeksifna.

Ayyaanichi kan nagaa, kan jaalalaa fi waloomaa akka ta'un hawwa.

Ayyaana Gaarii!

Waaqni Itoophiyaa fi Uummata Ishee Haa Eebbisu!

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!!በክርስቲያኖች ዘንድ ጥምቀት አንድም የመገለጥ፣ ሁለትም የእርቅና ዳግም የመወለድ ምልክት ነው፡፡ በቀደመው ዘመን አዳምና ሔዋ...
18/01/2026

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!!

በክርስቲያኖች ዘንድ ጥምቀት አንድም የመገለጥ፣ ሁለትም የእርቅና ዳግም የመወለድ ምልክት ነው፡፡ በቀደመው ዘመን አዳምና ሔዋን በፈጸሙት ሐጥያት የሰው ልጅ ከአምላኩ ተቀያይሞ የፍዳ ዘመናትን አሳልፏል፡፡ ዳሩ ግን ሰው በሐጥያቱ ልጅነቱን ቢነጠቅም እስከወዲያኛው ጠፍቶ አልቀረም፤ አባቱን ያስከፋ ሥህተት ቢሰራም እስከመጨረሻው ተረግሞ አልኖረም፡፡ አጥቶ የነበረውን የልጅነት ጸጋ በክርስቶስ ዳግም ተቀብሏልና፡፡ ክርስቶስ በፈለገ ዮርዳኖስ የተገኘው እሱ ራሱ ሐጥያት ኖሮበት አይደለም፤ ይልቁንም በሐጥያት እድፍ ለቆሸሸው የሰው ልጅ የእርቅ መንገድ ለመሆን እንጂ፡፡

ሥርዓተ-ጥምቀቱን ስናከብር የጥፋት መፍትሔው ይቅርታ፣ የጸብ መድሃኒቱ እርቅ እንደሆነ እያሰብን መሆን አለበት፡፡ ጸብ አይቀሬ ተፈጥሯዊ ሁነት ነው፡፡ በአባትና በልጅ፣ በፈጣሪና በፍጡር፣ በሕዝብና በሕዝብ መካከል ጸብ ይኖራል፡፡ ነገር ግን ይቅርታና እርቅም አይቀሬ የተፈጥሮ ሁነቶች ናቸው፡፡ ጸብ በአንድ አጋጣሚ የሚከሰት ድንገቴ ክስተት እንደሆነ ሁሉ፥ እርቅ ደግሞ ልዩ ልዩ ሁነቶችን ያቀፈ ጊዜ ወሳጅ ሂደት ነው፡፡ በፈጣሪና በሰው ልጅ መካከል የተፈጠረው የጸብ ግድግዳ መፍረስ የጀመረው በቃል ነው፡፡ አምላክ “ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ” ብሎ ሲናገር የእርቅ ሂደቱም ያኔ ጀምሯል፡፡ የተቋጨው ግን ክርስቶስ በቤተልሄም ተወልዶ፣ በዮርዳኖስ ተጠምቆ፣ መስቀሉን ተሸክሞ ከተሰቀለ በኋላ ነው፡፡

በአምላክና በሰው ልጅ መካከል የተፈጠረው ጸብ በክርስቶስ ፍጻሜውን እንዳገኘ ሁሉ፤ እንደ ሀገር ያሉብንን አለመግባባቶች በጠረጴዛ ዙሪያ ልንፈታቸው፣ የዘመናት የልዩነት እዳዎቻችን ፍጻሜ ሊያገኙ ከጫፍ ደርሰናል፡፡ የሀገራዊ ምክክር ኮምሽኑ ከተቋቋመ ወዲህ ባለፉት ሦስት ዓመታት ሰፊ ቁጥር ያላቸው ዜጎቻችን የተካፈሉበት፣ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፉ እና የልዩነት አጀንዳዎችን ያሰባሰቡ ሰፋፊ መድረኮች ተዘጋጅተዋል፡፡ ተቃርኖዎቻችን በዘላቂነት መፍትሔ የሚያገኙት በምክክራችን ፍጻሜ ነውና እንደሂደቱ ሁሉ ለፍጻሜው ርብርብ እንድናደርግ በዚሁ አጋጣሚ አደራ እላለሁ፡፡

ሥርዓተ-ጥምቀቱ የመገለጥም ምልክት ነው፡፡ ከጥምቀቱ እለት በፊት ክርስቶስ የሚታወቀው በጥቂቶች ብቻ ነበር። በልደቱ የተገለጠውን ብርሃን ለማዳፈን የሞከሩ ሄሮድስን የመሰሉ አካላትም የተሳካላቸው መስሏቸው ነበር። ከሠላሳ ዓመታት በፊት በቤተልሔም የታየው የሰው ልጅ ተስፋ መልሶ የጠፋ መስሎም ነበር። ታይቶ እንደሚጠፋ ኮከብ፤ መጥቶ እንደሚሄድ ዘመን፣ ተከሥቶ እንደሚሠወር መብረቅ የቆጠሩትም ነበሩ።

በጥምቀት ዕለት ግን እውነት ለዓለም ሁሉ ተገለጠች። ከሰማይ እና ከምድር ምስክር መጣ። እንደ ቤተልሔም በጥቂቶች ፊት ብቻ ሳይሆን፣ በዐደባባይ በብዙዎች ፊት ተገለጠ። “እርሱን ስሙት” የሚለው ቃልም ከሰማይ መጣ። ከዚህ በፊት ለእረኞች ብቻ ነበር የተነገረው። ዛሬ ግን ጆሮ ላላቸው ሁሉ ተነገረ። ያኔ በበረት ውስጥ ነበር፤ አሁን ግን በሄኖም ሸለቆ፣ በዮርዳኖስ ወንዝ፣ በዓለም ፊት ሆነ።

ጊዜው ደርሶ የተገለጠ ነገር በዓላማው ፈጻሚዎች እና በዜናው ሰሚዎች መካከል የተለያየ አካሄድ አለው። የዓላማው ፈጻሚዎች ከየት፣ ለምን፣ እንዴት እንደመጣ ያውቃሉ። ወዴት፣ እንዴት እንደሚሄድ ይረዳሉ። ለምን ዓይነት ግብ እንደመጣ ይገነዘባሉ። ስለዚህም ምንም ዓይነት መሥዋዕትነት ለመክፈል ይዘጋጃሉ። አንድ ሆኖ የበራው ሻማ፣ ቀስ እያለ እልፎችን ሲያቀጣጥል ይታያቸዋል። በደመናት ውስጥ የፈነጠቀው ፀሐይ፣ ቀስ እያለ ደመናውን ሲገላልጥ ይታያቸዋል። ከአንድ እንጨት የተለኮሰው እሳት፣ ቀስ እያለ ሲንቦገቦግ ይታያቸዋል።

ዜናውን የሚሰሙት ግን እንደዚያ አይደሉም። ሂደቱን የሚገመግሙት ባገኙት መረጃ መሠረት ብቻ ነው። ዜናው የቀዘቀዘ ሲመስላቸው ጠፍቷል ብለው ያምናሉ። ዜናው የሞቀ መስሎ ሲሰማቸው ደግሞ አለ ብለው ይገምታሉ። የነገሩን መነሻ፣ ሂደትና ግብ በቅርበት አያውቁም። በቤተልሔም የሉም፤ በዮርዳኖስ አልቆሙም። አየን ያሉ ይነግሯቸዋል፤ ሰማን ያሉ ያወሯቸዋል። በዚህም የተነሣ ውሳኔያቸውና ብያኔያቸው በዕለት ክሥተት ላይ የተመሠረተ ነው። ክርስቶስ በሚያስተምርበት ወራት በየተአምራቱ፣ በየክሥተቱና በየኩነቱ ይገኙ እንደነበሩ ሰዎች ዓይነት። በጥብርያዶስ ዳር ሲመግባቸው “እናንግሥህ” ይላሉ፤ በጲላጦስ ዐደባባይ ሲቆም “ስቀለው” ብለው ይፈርዳሉ።

ዛሬ በዚህ የበዓሉ መንፈስ ውስጥ ሆነን የኢትዮጵያን የመገለጥ ጉዞ እንድንመረምር እጋብዛለሁ።

የኢትዮጵያ ዕሴቶች፣ የኢትዮጵያ ሀብቶች፣ የኢትዮጵያ ዐቅሞች፣ የኢትዮጵያ ክንዶች፣ የኢትዮጵያ ውበቶች፣ የኢትዮጵያ ክብሮች፣ የኢትዮጵያ ከፍታዎች - እየተገለጡ ናቸው።

ለውጡ ከመጣ ጀምሮ ላለፉት ጥቂት ዓመታት መሠረቱን ስንሠራ ነበር። የብሉዩን ዘመን ስናድስ፣ የሐዲሱን ዘመን ስንረስስ ነበር። የኦሪቱን ዕዳ ስንደመስስ፣ የሐዲሱን ምንዳ ስናስስ ነበር። የያዘንን ትብታብ ስንበጥስ፣ የለያየንን ግንብ ስናፈርስ ነበር። የፈነጠቀው እስኪፈካ፣ የተወጠነው እስኪሳካ ጠብቀን ነበር። ያልገባቸው እስኪረዱ፣ የገባቸው እስኪራመዱ ዕድል ሰጥተን ነበር።

አሁን ያ ሁሉ አልፎ የኢትዮጵያ የመገለጥ ዘመን መጥቷል። የግብርና ዐቅሟ ተገልጦ ሕዝቦቿን ይመግባል። የማዕድን ዐቅሟ ተገልጦ ዕድገቷን ያፋጥናል። የቱሪዝም ዐቅሟ ተገልጦ ዓለምን ያስደምማል። የቴክኖሎጂ ዐቅሟ ተገልጦ ልማቷን ያቀላጥፋል። የዲፕሎማሲ ዐቅሟ ተገልጦ ተጽዕኖ ፈጣሪነቷን ያጸናል። የአምራችነት ዐቅሟ ተገልጦ የዓለምን ገበያ ይሻማል።

አሁን የኢትዮጵያ ምስክሮች ከላይም ከታችም እየተሰሙ ናቸው። በቤተልሔም ለጥቂቶች ተገልጦ የነበረው የኢትዮጵያ ታላቅነት፣ ዛሬ በዮርዳኖስ ለዓለም ሁሉ እየታየ ነው። ከእንግዲህ የተገለጠችውን ኢትዮጵያን መስማት የግድ ነው። በዮርዳኖስ ስንገለጥ እያዩ በምኩራብ የቀሩት አካላት ብዙ ቢናገሩ አይገርመንም። እኛ የሐዲስ ሰዎች ነን። ብዙ ነገሮችን ቀይረናል፤ አድሰናል። እነርሱ የኦሪት ሰዎች ናቸው። ባልታደሱ ጎዳናዎቻቸው፣ ባረጁ ከተሞቻቸው፣ በደከሙ ቅጥሮቻቸው ውስጥ ይኖራሉ።

ኢትዮጵያ እንደሆነች ከቤተልሔም ወደ ዮርዳኖስ፤ ከዮርዳኖስ ወደ ቆሮንጦስ - ከቆሮንጦስ ወደ ደብረ ታቦር - ከደብረ ታቦር ወደ ቀራንዮ - ከቀራንዮ ወደ ደብረ ዘይት እያለች መጓዟን ትቀጥላለች። ከእንግዲህ እያረገች ትሄዳለች እንጂ ወደ አሮጌ መንደሮቿ አትመለስም። የፈርዖን አስማተኞች የሚፈጥሩት አስማትና መተት ከእንግዲህ አያስፈራትም። ባሕር እንዴት እንደሚከፈል በዮርዳኖስ አይታለችና።

ይህ ዘመን ያለ ጥርጥር የኢትዮጵያ ዘመን ነው። ከኢትዮጵያ እውነት ጋር የሚራመዱ ሁሉ ከኃይል ወደ ኃይል ይራመዳሉ። ይሄን የተረዱ ብዙዎች ከውጭም፣ ከጫካም ወደ ኢትዮጵያ እየመጡ ነው። ኢትዮጵያም እየተቀበለቻቸው ነው። የቀሩት ብዙዎች ደግሞ የጊዜ ጉዳይ እንጂ እንደሚመጡ እናምናለን። ከጥፋት ልጅ በቀር ማንም ከኢትዮጵያ እውነት አይቀርም።

እምነታችን፣ ሥርዓታችን፣ ባህላችን፣ ቋንቋችን፣ ዜማችን፣ በአጠቃላይ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችን በዐደባባይ ለሚገለጥበት የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ።

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ጥር 10 ቀን 2018 ዓ.ም

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Address

Addis Ababa
782

Telephone

+251115514981

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gandhi Memorial Hospital ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Gandhi Memorial Hospital ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Category