Gandhi Memorial Hospital ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል

Gandhi Memorial Hospital                  ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል Gandhi Memorial Hospital is a pioneer Maternal and Neonatal Health Hospital located in Addis Ababa E

26/02/2026
24/02/2026

ድንቅ ነዉ!

በህክምና አገልግሎት ጥራት ላይ ያጠነጠነ ስልጠና በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል የስልጠና ማዕከል በዛሬዉ ዕለት ተጀምሯል።ለተመረጡ የጤና ባለሙያዎች የተሰናዳዉ ስልጠና ቀጥተኛ በሆነ መንገድ ከዕለ...
23/02/2026

በህክምና አገልግሎት ጥራት ላይ ያጠነጠነ ስልጠና በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል የስልጠና ማዕከል በዛሬዉ ዕለት ተጀምሯል።

ለተመረጡ የጤና ባለሙያዎች የተሰናዳዉ ስልጠና ቀጥተኛ በሆነ መንገድ ከዕለት - ተዕለት ተግባራት ጋር ተዛምዶ ያለዉ በመሆኑ በተቋም ደረጃ ትኩረት የተሰጠዉ ጉዳይ መሆኑ ተገልጿል።

👉የስልጠናዉ ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸዉ

in healtcare
of Improvement
change
of improvement ,spread and scale-up
identification

የጤና ባለሙያዎቹ ያሉበትን ቁመና ለማየት የፅሁፍ ፈተና የወሰዱ ሲሆን በስልጠናዉ ማጠናቀቂያ ላይም ተመሳሳይ ምዘና እንደሚኖር ለማወቅ ችለናል።
16/06/2018

" ...በኢትዮጽያ የህንድ አምባሳደር እንዲሁም በአፍሪካ ህብረት የሀገርዎ ቋሚ ተወካይ! ...ክቡር አምባሳደር አኒል ኩማር ራይ! ከእርስዎ ጎን ሆኖ መስራት ሁልግዜም አስደሳች ነዉ !........
21/02/2026

" ...በኢትዮጽያ የህንድ አምባሳደር እንዲሁም በአፍሪካ ህብረት የሀገርዎ ቋሚ ተወካይ! ...ክቡር አምባሳደር አኒል ኩማር ራይ! ከእርስዎ ጎን ሆኖ መስራት ሁልግዜም አስደሳች ነዉ !..... አመሰግናለሁ! "
ዶ/ር ታሪኩ ደሬሳ
የጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ

" Thank you...! H.E. Ambassador Anil Kumar Rai, Ambassador of India to Ethiopia and permanent representative to the African Union. It is always a pleasure working alongside you...!"
Dr Tariku Deressa
CEO of GMH

18/02/2026

የላቀ አገልግሎት ...በጥራት!

ኢንፌክሽንን መቆጣጠር እና ማስወገድ(IPC) ላይ ያተኮረ ስልጠና በጋንዲ መታሰቢያ የስልጠና ማዕከል በዛሬዉ ዕለት ተጀምሯል። ለተመረጡ የሆስፒታሉ የጤና ባለሙያዎች የተሰናዳዉ ስልጠና ከጤና ቢ...
16/02/2026

ኢንፌክሽንን መቆጣጠር እና ማስወገድ(IPC) ላይ ያተኮረ ስልጠና በጋንዲ መታሰቢያ የስልጠና ማዕከል በዛሬዉ ዕለት ተጀምሯል።

ለተመረጡ የሆስፒታሉ የጤና ባለሙያዎች የተሰናዳዉ ስልጠና ከጤና ቢሮ በመጡ ባለሙያ የሚመራ ሲሆን ርዕሰ-ጉዳዩ በስራ ላይ የሚያጋጥም በመሆኑ ስልጠናዉ ነባራዊ ሁኔታን ያገናዘበ መሆኑ ተመላክቷል።

በስልጠናዉ ከሚነሱ አንኳር ነጥቦች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦

and transmission based precaution
protective equipments
and infection safety
care waste management
and reprocessing of medical devices

ከስልጠናዉ በፊት ሰልጣኞቹ ያለባቸዉን ክፍተት ለመለየት ይረዳ ዘንድ የጽሁፍ ፈተና ወስደዋል።

8/06/2018

" 24/7..." በሉት!በ "ወርቃማዉ ሰኞ " ተገልጠናል....ለመሳቅ ትንሽ ነገር ይበቃዋል። አይን አፋር ቢጤ ቢመስልም ቀረብ ካሉት ግን ....ተግባቢ እና ጨዋታ ወዳድ ነዉ !   ክርክር ....
16/02/2026

" 24/7..." በሉት!

በ "ወርቃማዉ ሰኞ " ተገልጠናል....

ለመሳቅ ትንሽ ነገር ይበቃዋል። አይን አፋር ቢጤ ቢመስልም ቀረብ ካሉት ግን ....ተግባቢ እና ጨዋታ ወዳድ ነዉ ! ክርክር ...ጭቅጭቅ... ብሎ ነገር እሱ ጋር የለም! ...ይልቁን ከፉክክር በተሻለ ትብብርን ይመርጣል ። ሰርቶ ያሰራል። ቤተ-ሙከራዉን የቤቱ ያህል ይወዳል......ከሱ ዘንድ ሁሌ ሩጫ ነዉ! ...ከሱ ዘንድ...ሁሌ ጥድፊያ ነዉ ከ ጊዜ ጋር!!!
የላቦራቶሪ ዳይሬክተሩ ገመቺስ ሌንጫሞ!

ገሜ ተወልዶ ያደገዉ ባቱ ከተማ መሆኑን ይናገራል። ሀረማያ ዩኒቨሪሲቲ ገብቶ...ዲግሪዉን ተቀብሎ ስራን "ሀ"ብሎ የጀመረዉ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን እንደነበረ አዉግቶናል።
"ቡሌ ቦራ" ጤና ጣቢያ 1 ዓመት ከመንፈቅ በነበረዉ ቆይታ በርካታ ፈተናዎችን መጋፈጡን አስታዉሷል።

ገሜ ይቀጥላል...

" .....በአካባቢዉ የኤሌክትሪክ ሃይል ባለመኖሩ ቤተ-ሙከራ ያሉ መሳሪያዎችን ለመጠቀም አልቻልንም ነበር....በዚህ የተነሳ ለምርመራ የመጡ ከታካሚ የተወሰዱ ናሙናዎችን ለማየት አጉሊ-መነጽር መጠቀም የግድ ስለነበር ባትሪ ዲንጋይን ተጠቅሜ በግል ፈጠራ ...መጠነኛ ኤሌክትሪክ መብራት ለመግኘነት በመቻላችን ...ግዜያዊ መፍትሄ ለመስጠት ችያለሁ... " በማለት እጅ መስጠት እንደማይወድ ገልጿል።

ገመቺስ ለጥቆ ያቀናዉ ወደ ሀገረማርያም ሆስፒታል ነበር። እዚያም በኃላፊነት አገልግሏል። እዚህ ቤት ያገጠመዉ ፈተና ደግሞ " የደም ባንክ ... አለመኖር..." ነዉ ብሎናል። ...

"አንድ ግዜ" አለ... ገሜ ሳቅ ብሎ "... አንድ ጊዜ አንዲት እናት በወሊድ ምክንያት ብዙ ደም ፈሰሳት እና በሞት እና በህይወት መሀከል ወደቀች...! ......ቤተሠቦቿ ደም ለመለገስ ፈቃደኛ አልነበሩምና ተጨነቅኩ !..... ...አይኔ እያየ መሞት የለባትም በማለት እኔዉ እራሴ ደም ለመለገስ ቆረጥኩ። ከዚያም.....ጓደኞቼን ከእኔ ላይ ደም እንዲቀዱ ብነግራቸዉ አሻፈረኝ አሉ!!!... ከዚያ እራሴዉ ከራሴ ላይ ደም በመዉሰድ የእናቲቱን ህይወት ለመታደግ ችያለሁ.....!" ሲል የሠራዉን ጀብድ በኩራት አስታዉሷል።

ገመቺስ ወደ ጋንዲ መታሠቢያ ሆስፒታል በዝዉዉር ከመጣ በኋላ በላቦራቶሪ ክፍል በዳይሬክተርነት እያገለገለ ይገኛል።
በቅርቡም በተደረገ ምዘና የሆስፒታሉ ቤተ-ሙከራ በላቀ ዉጤት ባለ 5 ኮኮብ ጀረጃ መያዙን ልብ በሉ!

ቀጥለናል.....

በመድረኩ ላይ የታደሙት የሠዉ ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተሯ ወ/ሮ የትናየት ዘዉዴ ".... ገሜ ....በሰራተኛ አያያዝ ፣ ክፍተትን በመሸፈን ፣ ተግባብቶ በመስራት በምሳሌነት የሚጠቀስ ምስጉን ሀላፊ ነዉ...." የሚል ምስክርነት አሰምተዋል።

ሜዲካል ዳይሬክተሩም በበኩላቸዉ " ...ገመቺስ ስራን ጠንቅቆ የሚያዉቅ ...ባለዉ የስራ ከባቢ ዉጤት ማምጣት የቻለ ምስጉን እና የምንተማመንበት ባልደረባችን ነዉ...." ሲሉ ተደምጠዋል።

ሌሎችም የሙያ አጋሮቹ ገመቺስ ያለዉን ግዜ... እዉቀት... ጉልበት... የማይሰስት ወሎ አዳሩ ...እንዲሁም ተግባሩ ...ለ24 ሰዓታት...! በሳምንቱ 7 ቀናት...! በስራ ላይ መሆኑን ያልሰማችሁ ስሙ ብለዋል።

ገሜ ለመዝናናት ኳስ ጨዋታ ይመለከታ.... ማንቺስተር ዩናይትድን ይደግፋል....! ወንድማችን አሁን ላይ ማስትሬት ዲግሪዉን አጠናቋል!....

በርታ ተበራታ ...የልብህ ይሙላ! ብለን መርቀናል!!!!

8/ 06/2018

13/02/2026

ይታከሙ ...ይፈወሱ!!!

12/02/2026

የቤተሰብ ምጣኔ ...ለምን?

ትናንትናዉ ዕለት የጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል የጤና ባለሙያዎች በቂርቆስ ክፍለ  ከተማ ወረዳ 3  ለሚኖሩ 70 የሚሆኑ አቅመ ደካማ  ሴቶችን  ወረዳው ድረስ  በመሄድ  የጤና  ትምህርት በመስጠ...
12/02/2026

ትናንትናዉ ዕለት የጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል የጤና ባለሙያዎች በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ለሚኖሩ 70 የሚሆኑ አቅመ ደካማ ሴቶችን ወረዳው ድረስ በመሄድ የጤና ትምህርት በመስጠት እንዲሁም ነፃ የስኳር እና የደም ግፊት ምርመራ እንዲያደርጉ አግዘዋል ። ከመደበኛው በላይ የደም ግፊታቸዉ ከፍ ያለባቸዉን እና የደም ዉስጥ ስኳር መጠን የጨመረባቸዉን እናቶች ወደ ጤና ተቋም በመሄድ ክትትል እንዲያደርጉ ምክር የተሰጣቸዉ ሲሆን በተጨማሪም
በወረዳዉ ላሉ ሴቶች የንፅህና መጠበቂያ እንዲያገኙ ሆኗል።
በተመሳሳይ የተባበሩት ትምህርት ቤት በመሄድ አፍላ ወጣት ሴቶችን ከእድሜያቸዉ ጋር በተያያዘ ሊገጥሟቸዉ በሚችሉ ጉዳዬች ላይ የምክር አገልግሎት በመስጠት ልዩ ልዩ የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች ተበርክቶላቸዋል።

Address

Addis Ababa
782

Telephone

+251115514981

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gandhi Memorial Hospital ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Gandhi Memorial Hospital ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram

Category