Ras Emiru Health Center

Ras Emiru Health Center Ras Emiru Health Center is a Governmental institution that is found in Arada Subcity, Wereda 02 locally known as Gojam Berenda area.

It was established five years ago. It now serves approximately more than 29,344 people who reside in Wereda 02 and nearby Wereda's of Arada subcity and Addis Ketema subcity. It provide primary health care services including curative health services and also mainly on disease prevention and health promotion services.

ልዑል ራስ እምሩ ኃይለሥላሴ ኅዳር 15 ቀን 1885 ዓ/ም ተወለዱ።አባታቸው ደጃዝማች ኃይለሥላሴ ዓባይነህ ነበሩ።እናታቸው ወይዘሮ መዝለቂያ የራስ  መኰንን እህት የወይዘሮ እኅተ ማርያም ልጅ ...
03/01/2020

ልዑል ራስ እምሩ ኃይለሥላሴ ኅዳር 15 ቀን 1885 ዓ/ም ተወለዱ።አባታቸው ደጃዝማች ኃይለሥላሴ ዓባይነህ ነበሩ።እናታቸው ወይዘሮ መዝለቂያ የራስ መኰንን እህት የወይዘሮ እኅተ ማርያም ልጅ ስለነበሩ የአጼ ኃይለ ሥላሴ አብሮ አደግና የቅርብ ዘመድም ነበሩ።በሰገሌ ጦርነት ላይ ከሐረርጌ የጦር አበጋዞች አንዱ ሆነው ውጊያው ላይ ተሳትፈዋል።ከጠላት ወረራ በፊት የወሎ ቀጥሎም የሐረር እንደራሴ ሆነው አገልግለዋል።በጠላት ወረራ ጊዜ በሽሬ ግንባር የጦር አዛዥ ሆነው በጀግንነት ጠላትን ተከላክለዋል።በሰሜን ግንባር ጦሩ ሲፈታ ወደ ምዕራብ ኢትዮጵያ በመዞር ለአንድ ዓመት ያህል በአርበኝነት ቆዩ።ጎጀብ ላይ ከተማረኩ በኃላ ወደ ኢጣልያ ተወስደው እስከ 1935 ዓ/ም ድረስ በእስረኛነት ቆይተዋል።ወደ ሀገር ከተመለሱ በኃላ የሰሜንና የበጌምድር ጠቅላይ ገዢ ሆነው ለአጭር ጊዜ ከቆዩ በኋላ በተከታታይ በአሜሪካ እንዲሁም በህንድ አገር በአምባሳደርነት አገልግለዋል።ልዑል ራስ እምሩ በአስተዳዳሪነትና በጦር አዝማችነት እጅግ የተመሰገኑና የተከበሩ ነበሩ።በ1972 ዓ/ም አርፈው ስርዓተ ቀብራቸው አዲስ አበባ መንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ በክብር ተፈጽሟል።
ምስሉ ራስ እምሩ ከቤተሰቦቻቸው ጋር!

30/10/2019

Produced by Tommy T. Directed by Daniel Tamrat

"መላው ኢትዮጵያን ለማፅዳት በአንድነት እንነሳ" በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ በተጀመረው የፅዳት ንቅናቄ መሰረት በጤና ጣቢያችን የተካሄደው የፅዳት ዘመቻ እንደዚህ ነበር።
15/04/2019

"መላው ኢትዮጵያን ለማፅዳት በአንድነት እንነሳ" በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ በተጀመረው የፅዳት ንቅናቄ መሰረት በጤና ጣቢያችን የተካሄደው የፅዳት ዘመቻ እንደዚህ ነበር።

Cancer kills 65,000 people each year in Ethiopia. FMOH
05/02/2019

Cancer kills 65,000 people each year in Ethiopia. FMOH

Today is World Cancer Day!

Here are some ways to reduce your cancer risk

Celebrating National Flag Day @ our center with our staff. Tikimt 5, 2011 E.C
17/10/2018

Celebrating National Flag Day @ our center with our staff. Tikimt 5, 2011 E.C

02/09/2018
Good news  . . .
06/12/2017

Good news . . .

የመንግስት ሰራተኞች የወሊድ ፈቃድ ወደ አራት ወር ከፍ አለ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 26፣ 2010 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሻሻለውን የመንግስት ሰራተኞች ረቂቅ አዋጅ አጸደቀ።

ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ስብሰባ የተሻሻለውን የመንግስት ሰራተኞች አዋጅን ጨምሮ ሌሎች ሁለት አዋጆችንም አፅድቋል።

የተሻሻለው የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ ሀገሪቷ ከደረሰችበት የዕድገት ደረጃ ጋር የተጣጣመና የመንግስት ሰራተኛውን መብት የሚያስጠብቁ ድንጋጌዎችን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።

የሰው ኃብት ልማት እና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴዎች ረቂቅ አዋጁን በዝርዝር በማየት የውሳኔ ሀሳባቸውን ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

በዚህም ረቂቅ አዋጁ በዓለም አቀፍ ደረጃ የታዩ ምርጥ ተሞክሮዎችን መሰረት ያደረገና አገሪቷ እያስመዘገበች ያለውን ዕድገት ማስቀጠል የሚያስችል ፐብሊክ ሰርቪስ ለመገንባት የሚረዳ መሆኑን የቋሚ ኮሚቴዎቹ በውሳኔ ሀሳባቸው አብራርተዋል።

የመጀመሪያው የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ 515/1999 በትግበራ ወቅት ያጋጥሙትን ችግሮች የሚፈታ እና አዋጁ የነበሩበትን ክፍተቶች የሚሞላ መሆኑም ተብራርቷል።

የተሻሻለው አዋጅ ለሴት ሰራተኞች የአራት ወራት የወሊድ ፍቃድ ከመስጠቱም ባለፈ በመንግስት መስሪያ ቤቶች የህጻናት ማቆያ ቦታዎች እንዲዘጋጁ የሚያደርጉ ድንጋጌዎችን ይዟል።

በቀድሞው አዋጅ የወሊድ ፍቃድ 90 ቀናት ወይም 3 ወር የነበረ ሲሆን፥ በተሻሻለው አዋጅ ወደ 120 ቀናት ወይም 4 ወር ከፍ ብሏል።

የወሊድ ፈቃዱ ፅንስ የተቋረጠባቸው ሴቶችንም የሚያካትት መሆኑ ተገልጿል።

አንድ የመንግስት ሰራተኛ የዓመት ፍቃድ በገንዘብ ሲለወጥ የሰራተኛው የአንድ ቀን ደመወዝ የሚታሰበው ያልተጣራ የወር ደመወዙን በ30 ቀናት በማካፈል መሆኑንም አዋጁ ይደነግጋል።

በሌላ በኩል የህመም ፈቃድ የመጀመሪያዎቹ ሶስት ወራት ከሙሉ ደመወዝ ጋር፣ለተከታዮቹ ሶስት ወራት ደግሞ ከግማሽ ደመወዝ ጋር እንዲሁም ለሚቀጥሉት ሁለት ወራት ያለደመወዝ እንደሚሰጥ ነባሩ አዋጅ ይደነግጋል።

በአዲሱ አዋጅ ግን የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ከሙሉ ደመወዝ ጋር፣ ለተከታዮቹ ሁለት ወራት ደግሞ ከግማሽ ደመወዝ ጋር እንዲሰጣቸው በሚል ተሻሽሏል።

የምክር ቤቱ አባላት አዋጁ አገሪቷ አሁን ከደረሰችበት የዕድገት ደረጃ ጋር የሚጣጣምና የመንግስት ሰራተኞችን መብት የሚያስጠብቁ ድንጋጌዎችን ያካተተተ ነው በማለት በአንድ ድምፀ ተአቅቦና በአብላጫ ድምፅ አፅድቀውታል።

ምክር ቤቱ በዛሬው ውሎው የተፈጥሮ ኃብት ልማትና አካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የደን ልማት ጥበቃና ረቂቅ አዋጅን በተመለከተ ያቀረበወን የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ በአብላጫ ድምፅና በ13 ድምፀ ተአቅቦ አፅድቋል።

በኢትዮጵያ መንግስትና በአለምአቀፍ የልማት ማህበር መካከል ለፍትሃዊ የመሰረታዊ አገልግሎቶች ማስፋፊያ ፕሮግራም ማስፈጸሚያ የሚውል ተጨማሪ ብድር ለማግኘት የተደረገውን ስምምነት ለማፅደቅ የቀረበ ረቂቅ አዋጅንም በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ

10/11/2017

This is so hilarious!!!!

Address

Addis Ababa

Telephone

+251 111266718

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ras Emiru Health Center posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram