Amanuel mental specialized hospital

Amanuel mental specialized hospital Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Amanuel mental specialized hospital, Addis Ababa ethiopia Addis ketema subcity at the vicinity of Mesalemeya, Addis Ababa.

Emmanuel mental specialized hospital is apionner one which provides mental health care and treatment for about people who are from all corners of the nation and mental health rehabilitation services since it has been established in 1938

የማቋቋሚያ ደንብ ረቂቅ ሠነድ ላይ ውይይት ተካሄደአዲስ አበባ: መስከረም 10/2017 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል) ፤ አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በአዘጋጀው የማቋቋሚያ ደንብ ረ...
21/09/2025

የማቋቋሚያ ደንብ ረቂቅ ሠነድ ላይ ውይይት ተካሄደ
አዲስ አበባ: መስከረም 10/2017 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል) ፤ አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በአዘጋጀው የማቋቋሚያ ደንብ ረቂቅ ሠነድ ላይ ከጤና ሚ/ርና አቻ ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም ከፍትህ ሚ/ር የህግ ባለሙያዎችና የሆስፒታሉ የአመራር አካላት በተገኙበት ቀርቦ ጥልቅ ውይይት ተደረጓል።
ረቂቅ የማቋቋሚያ ደንብ ሠነዱን ማዘጋጀበት ያስፈለገበትን ዋነኛ አላማ አስመልክቶ የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር አቶ ኢዳኦ ፈጆ ሆስፒታሉ ከተመሠረተ 87 ዓመት ያስቆጠረ አንጋፋ የአእምሮ ህመምና የተሃድሶ ህክምና አገልግሎቶችን ሲሰጥ የቆየ እና በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን ሆስፒታሉ በተመሠረተበት ወቅት የነበረ የማቋቋሚያ ደንብ አሁን ከአለው የተገልጋይ ፍላጎት፣ ሃገራዊ የጤና ስርዓት ሪፎርምና ሆስፒታሉ ይዞት ከተነሳው ጥራቱን የጠበቀ የበሽታ መከላከል፤ ማከም እና የተሀድሶ ጤና አገልግሎትን በመስጠት በጥናትና በምርምር የታገዘ የአቅም ግንባታ ስራ በመስራት ከአዕምሮ ህመም የተነሳ የሚመጣ ጉዳት እና ሞትን የመቀነስ ተልዕኮና በኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት የሚሰጥ፤ በአዕምሮ ጤና ህክምና እንዲሁም በአእምሮ ጤና ምርምርና ስልጠና የልህቀት ማዕከል የመሆን ራዕዩን ተጨባጭ ወደ ሆነ ለውጥ የሚያመራ የማቋቋሚያ ደንብ መኖር እጅግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው ሲሉ በአፅንኦት አንስተዋል ።
በተጨማሪም ተገቢውን ተቋማዊ ስርአት በመዘርጋት ትኩረት በሚሹ የጤና ጉዳዮች ላይ ችግር ፈቺና ተግባራዊ ሊሆኑ የሚችሉ ምርምሮችን ማካሄድ ፤ የተቀናጀ ፤ጥራቱን የጠበቀ ተገልጋይ ተኮር እና ተደራሽነት ያለው የድንገተኛና መደበኛ የአካልና የአዕምሮ ህክምና አገልግሎቶችን እና የማህበረሠብ አገልግሎቶችን ለህብረተሠቡ ለመስጠት ያለመ መሆኑ ነው የተገለፀው ።
ረቂቅ የማቋቋሚያ ደንብ ሠነዱ በሆስፒታሉ የህግ አገልግሎት ስራ አስፈፃሚ በአቶ ደበበ ለገሠ በኩል የቀረበ ሲሆን በተሳታፊዎች ገንቢ አስተያየትና ግብዓት ተሠጥቶበታል። በመጨረሻም በቀጣይ ረቂቅ የማቋቋሚያ ደኖብ ሠነዱ ከጤናው ሴክተር ሪፎርምና ከህክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት አኳያ እንዲሁም ከሆስፒታሉ ነባራዊ ሁኔታና የወደፊት አላማ ላይ ተመርኩዞ መሟላት ያለባቸው ጉዳዮችን በማካተት ረቂቅ የማቋቋሚያ ደንብ ሰነዱ ለውሳኔ ለሚመለከተው የመንግስት አካል እንደሚቀርብ ተመላክቷል።

አለም አቀፍ የህሙማን ደህንነት ቀን በውይይት ተከብሮ ዋለ አዲስ አበባ መስከረም 7/2018 ዓ.ም ( አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል) በየአመቱ እ. ኤ. አ መስከረም 17 ቀን የሚከበረው አለም አቀፍ የ...
17/09/2025

አለም አቀፍ የህሙማን ደህንነት ቀን በውይይት ተከብሮ ዋለ
አዲስ አበባ መስከረም 7/2018 ዓ.ም ( አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል) በየአመቱ እ. ኤ. አ መስከረም 17 ቀን የሚከበረው አለም አቀፍ የህሙማን የደህንነት ቀን ደህንነቱን የጠበቀ ክብካቤ ለሁሉም ህፃናትና ጨቅላ ህፃናት " የህሙማን ደህንነት ከውልደት" በሚል መሪ ቃል የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የጤና ባለሙያዎችና የክብካቤ ሰራተኞች በተገኙበት በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ በፓናል ውይይት ተከብሮ ውሏል
ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የሆስፒታሉ የድንገተኛ ህክምና ዳይሬክተር ዶ/ር ሉሉ በቃና የቀኑ መከበር ዋና አላማ የአእምሮ ጤናን ከታካሚ ደህንነት ጋር በማቀናጀት የሰዎች ደህንነት ከእርግዝና ጀምሮ አካላዊ፣ ስሜታዊ እና አእምሮአዊ ጤና መጠበቅ እንዳለበት አንስተው ለህፃናት አእምሯዊ እድገት የእናትዮዋ በእርግዝና ወቅት መውሰድ ያለባት የተመጣጠነ ምግብና ከድባቴና ጭንቀት ከመሳሰሉ የአእምሮ እክሎች መጠበቅ ወሳኝ የሆነ ሚና እንደሚጫዎቱ በአፅንዖት አንስተዋል ።

ለፓናል ውይይቱ የህሙማን ደህንነትና የአእምሮ ጤና በሚል ርዕሰ ጉዳይ የውይይት መነሻ ፅሁፍ ያቀረቡት የሆስፒታሉ የህክምና ጥራትና ቁጥጥር የስራ ክፍል ሃላፊ ሲ/ር ቀለሟ ሃይሌ ከ6-17 አመት ከሆናቸው 5 ህጻናት ውስጥ አንዱ የአእምሮ ጤና መታወክ እንደሚያጋጥመው አንስተው የሕፃናትን እና የጨቅላ ሕፃናትን ደህንነት ለማሻሻል የአእምሮ ጤናን ወደ ታካሚ ደህንነት ክብካቤ ተደራሽነት ማቀናጀት እንደሚገባና -የጤና እንክብካቤ አቅራቢዎች፣ ቤተሰብ እና ማህበረሰብ በጋራ በመስራት የአእምሮ ጤናን እና አጠቃላይ እድገትን የሚያጎለብቱ ደጋፊ አካባቢዎችን መፍጠር የሚቻል መሆኑን ገልፀዋል።
የአእምሮ ጤና ስጋቶችን አስቀድሞ መፍታት የተሻለ አእምሯዊና አካላዊ ውጤት ያስገኛል ለአብነትሞ ወቅታዊ ድጋፍ የሚያገኙ ልጆች በት/ቤት ስኬታማ የመሆን እድላቸው ሰፊ ነው እንዲሁም ጤናማ ግንኙነት የመፍጠር እድላቸውም ሰፊ ነው በማለት በፅሁፋቸው አትተዋል።
አክለውም በአእምሮ ጤና ላይ የሚደርስ መገለል ብዙውን ጊዜ የታካሚ ቤተሰብ እርዳታ እንዳይፈልግ ያደርገዋል ብለዋል።
በመጨረሻም የታካሚዎች ደህንነት የሚረጋገጠው ከመጀመሪያው በእርግዝና ወቅት ጀምሮ የእናቶችን የአእምሮ ጤና መጠበቅ፤ የቤተሰብ ድጋፍ እና የማህበረሰብ ግንዛቤን ማጎልበት፥ ለህጻናት ተስማሚ የሆኑ አገልግሎቶችን መፍጠር፡ የአዕምሮ ህክምናና ክብካቤ ጥራትና ተደራሽነት ማስፋፋት የሁሉም ዜጋ ሃላፊነት ሊሆን እንደሚገባ በውይይቱ ላይ የቀረበ ሲሆን ከመጀመሪያው የህይወት መሠረት ከሆነው ፅንሰት ጀምሮ ደህንነቱ የተጠበቀ እንክብካቤን ማረጋገጥ ደህንነቱ የተጠበቀ ፣ ጤናማ ፣ ውጤታማ ትውልድን ለመፍጠር የሚያስችልም መሆኑም ነው የተገለፀው ።

መስከረም 01 ቀን 2018 ዓ.ም የአማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አመራር አባላት አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ ከታካሚዎችና ተንከባካቢዎች እንዲሁም በበዓል ቀን ተረኛ ከነበሩ የ...
11/09/2025

መስከረም 01 ቀን 2018 ዓ.ም የአማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አመራር አባላት አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ ከታካሚዎችና ተንከባካቢዎች እንዲሁም በበዓል ቀን ተረኛ ከነበሩ የጤና ባለሙያዎችና የክብካቤ ሰራተኞች ጋር የምሳ ፕሮግራም አዘጋጅተው በዓሉን በደማቅ ሁኔታ አሳልፈዋል ።

የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የማዕድ ማጋራት ኘሮግራም አካሄደጳጉሜ 5/2017 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታ...
10/09/2025

የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የማዕድ ማጋራት ኘሮግራም አካሄደ
ጳጉሜ 5/2017 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሆስፒታሉ ውስጥ የስራ ባልደረባ ለሆኑ እና በሆስፒታሉ አካባቢ ለሚኖሩ 20 ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው አቅመ ደካማ ግለሠቦች 2018 ዓዲስ ዓመትን በዓልን ተደስተው እንዲያሳልፉ በማሠብ ለእያንዳንዳዳቸው 5ሊትር ዘይት፥ ዶሮና እንቁላል እንዲሁም ለእያንዳንዳቸው በጥሬ ገንዘብ 650ብር ድጋፍ በማድረግ ማዕድ አጋርቷል።
በዚህም ሆስፒታሉ አብሮነትን ፥መተሳሰብን ፥መደጋገፍን፥ ወንድማማችነትና አህትማማችን በማጠናከር መልካም ባህላዊ እሴቶቻችንን መገንባትና ለቀጣይ ትውልድም ማሻገር ይገባል በማለት መልካም ምኞቱን አስተላልፏል።
አዲሱ ዓመት የመተሳሰብ የፍቅር የአንድነትና የብልፅግና ይሁንልን

መልካም አዲስ ዓመት
10/09/2025

መልካም አዲስ ዓመት

09/09/2025

ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የምረቃ ቀን እንኳን አደረሳችሁ

07/09/2025
የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህብር ቀንን በማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር አከበረአዲስ አበባ ፡ጳጉሜን 2/2017 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)፡ ብሄራዊ የህብር ቀን አብሮነት ለሃገ...
07/09/2025

የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህብር ቀንን በማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር አከበረ
አዲስ አበባ ፡ጳጉሜን 2/2017 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)፡ ብሄራዊ የህብር ቀን አብሮነት ለሃገራዊ አንድነት በሚል መሪ ቃል በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ፤ የጤናና ባህልና ስፖርት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክብርት ወ/ሮ ወርቅ ሰሙ ማሞ፤ ክብርት ወ/ሮ ሳህረላ አብዱላሂ የጤና ሚኒስቴር ሚ/ር ዴኤታ፤ ክብርት ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ፤ ክብርት ወ/ሮ ነፊሳ አልማሃዲ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ፤ ክብርት ወ/ሮ ፈሪያ መሃመድ የባህልና ስፖርት ሚ/ር የሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ ፤ የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቦርድ አመራር አባላት፤ የጤና ሚ/ር የስራ አስፈፃሚዎች፤ የባህልና ስፖርት ሚ/ር የስራ አስፈፃሚዎች፤ የሆስፒታሉ የስራ አመራር አባላትና ሰራተኞች፤ ታካሚዎችና የታካሚ ቤተሰቦች እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በታደሙበት በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ ማዕድ በማጋራት እና የቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ በደማቅ መርሃ ግብር ተከብሮ ውሏል፡፡
መርሃ ግብሩን በእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት የከፈቱት የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር አቶ ኢዳኦ ፈጆ የብሄራዊ የህብር ቀንን በአብሮነት ስናከብር ዋነኛ አላማው በሃገራችን ህዝቦች መካከል መተባበርንና ወንድማማችነትን በማጉላት ህብረብሄራዊ አንድነትና ሃገረ መንግስት ግንባታን ለማጠናከር ብሎም መተሳሰብን፤ መደጋገፍን፤ ማህበራዊ ትስስርና አብሮነትን ለማጠናከር የሚያግዝ በመሆኑ ነው በማለት ሲገልፁ አክለውም ሃገራችን ለጀመረችው የብልፅግና ጉዞ መረጋገጥ መሰረት የሆኑትን የአብሮነት፤ የመደጋገፍ፤ የመተባበር፤ የወንድማማችነት፤ የትስስር ማህበራዊ እሴቶቻችንን ባህላችንን አድርገን ለሃገራዊ አንድነት ግንባታ በማዋል እና እነኝህን የባህል እሴቶች ተሻጋሪ በማድረግ ረገድ በዘርፉ የተሰማሩ ምሁራን፤ የሲቪልና የሃይማኖት ተቋማት፤ አጠቃላይ ማህበረሰቡና የሚድያ ተቋማትን ጨምሮ የአንበሳውን ድርሻ ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
ክብርት ወ/ሮ ኒፊሳ አልማሃዲ የባህልና ስፖርት ሚ/ር ዴኤታ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በብዝሃ-ባህል ፀጋዎች የታደለች ሲትሆን የመተባበርና የመደጋገፍ ባህልን በማዳበር ለዘመናት የቆዬ የጋራ መስተጋብርና የአብሮነት መንፈስ ከዜጎቿ ደም ጋር ተሰናስሎ የኖረ እና በቀላሉ የማይደበዝዝ ማህበራዊ ትሩፋቶችን የተገናፀፈች አገር መሆኗ ገልፀው
በዚህ የማህበረሰብ አስተሳሰብ ለውጥና የትብብር መንፈስ ግንባታ ሁላችንም ተረባርበን ልንሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ሚኒስቴር መስሪያቤታቸው የወንድማማችነትና እህታማማችነት አስተሳሰብን በማጉላት የመተሳሰብና የአብሮነት ባህል እንዲጠናከር የተለያዩ ድጋፎችን ለማድረግ ዝግጁ መሆናችውንም በአፅንኦት አንስተዋል ፡፡
በመቀጠልም ክብርት ወ/ሮ ሳሃረላ አብዱላሂ የህብር ቀንንና የታላቁ ህዳሴ ግድብ የምረቃ ቀንን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በ2018 ዓ.ም ከተስፋ ወደ ሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበትና ኢትዮጵያ የምታንሰራራበት ጊዜ ነው በማለት ገልፀዋል፡፡
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ፤ የጤናና ባህልና ስፖርት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት ክብርት ወ/ሮ ወርቅ ሰሙ ማሞ በበኩላቸው የህዳሴ ግድባችን የአንድነታችን፤ የአብሮነታችን፤ የማህበራዊ ትስስራችን፤ የጀግንነታችንና የአይበገሬነታችን ብሎም የብዙሃነታችን መገለጫ ነው፡፡ አንድ ስንሆን ፤ስንተባበር ፤ ስንደጋገፍ ታምር እንሰራለን ሰርተናልም ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በመጨረሻም ሁሉም የክብር እንግዶች ተኝተው በሆስፒታሉ ውስጥ ከሚታከሙ ታካሚዎች፤ የታካሚ ቤተሰቦችና ከሆስፒታሉ ሰራተኞች ጋራ በጋራ በመሆን የማዕድ ማጋራት ስነ-ስርዓት አከናውነዋል፡፡ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በብዝኃነቷ እያጌጠች፤ በብዝኃነቷ ዐቅም እያደገች፤ ዐዲሲቷ የተስፋ ዓድማስ ትኾናለች፡፡ የማንሰራራት ዘመኗም በብዝኃነቷ ያጌጣል፡፡

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1500ኛው የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ አደረሠን ። በዓሉ የሠላም የአንድነት የመተሳብ እና የፍቅር ይሆንላችሁ ዘንድ የአማኑኤል አእምሮ ስፔ...
04/09/2025

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1500ኛው የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ አደረሠን ። በዓሉ የሠላም የአንድነት የመተሳብ እና የፍቅር ይሆንላችሁ ዘንድ የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መልካም ምኞቱን ያስተላልፋል

በህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ማነቆዎች ላይ መሠረት ያደረገ የለውጥ አፈፃፀም  ግምገማ ተካሄደ አዲስ አበባ: ነሐሴ 16/2017 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል) የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆ...
23/08/2025

በህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ማነቆዎች ላይ መሠረት ያደረገ የለውጥ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ

አዲስ አበባ: ነሐሴ 16/2017 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል) የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2017 በጀት አመት የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ማነቆዎች ላይ መሠረት ያደረገ የለውጥ አፈፃፀም ግምገማ ከ16/12/2017_17/12/2017 ዓ.ም ድረስ በአዳማ ከተማ አካሄደ
ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የሆስፒታሉ የፅ/ቤት ሃላፊ አቶ መኮንን አሰፋው በኢትዮጵያ ሆስፒታሎች የአሰራር ሥርዓት ማነቆዎች ሪፎርም ላይ ማተኮር በጤና አጠባበቅ አሰጣጥ ላይ ለውጥ ለማምጣት ያስችላል ብለዋል ። አያየዘዉም የአቅም ውስንነት፣ ከፍተኛ የታካሚ ፍሰት፣ የመሠረተ ልማት ክፍተቶች እና የሰራተኞች እጥረት ችግሮችን ከመፍታት አንፃር የጎላ ጠቀሜታ እንዳለው እና ማነቆዎችን በመፍታት ላይ ያተኮሩ ማሻሻያዎች የአጠቃላይ የሆስፒታል የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓቱን አፈፃፀም በእጅጉ እንደሚያሳድግ ገልፀዋል። በግምገማው ላይ የአገልግሎት አሰጣጥ ማነቆ መሠረት ያደረገ ሪፍርም ትግበራ (SBFR)፥ የተመላላሽ ህክምና ፥ የአስተኝቶና የነርሲንግ አገልግሎት የአፈፃፀም ኦዲት በዝርዝር ቀርቦ ጥልቅ ውይይት ተደርጎበታል።

በኢትዮጵያ ሆስፒታሎች የስርዓት ማነቆ ላይ ያተኮረ ማሻሻያ ዋና ዓላማዎች የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት አፈጻጸምን የሚገድቡ እንቅፋቶች ላይ በማነጣጠር አጠቃላይ የጤና አጠባበቅን ውጤታማነት፣ ቅልጥፍና እና ፍትሃዊነትን ማሻሻል ላይ ያተኮረ ሲሆን የአሰራር ስርዓት ማነቆ-ተኮር ማሻሻያ በሆስፒታል ደረጃ የታካሚ እንክብካቤን ጥራት እና ወቅታዊነት ለማሳደግ ፥የሀብት አጠቃቀምን እና ውጤታማነትን ማሻሻል ፥የታካሚዎችን መጨናነቅ እና የጥበቃ ጊዜን ለመቀነስ ፥የጤና ስርዓት ውህደት እና ቅንጅትን ማጠናከር ፥የጤና ባለሙያዎችና ክብካቤ ሰራተኞችን ምርታማነት እና ተነሳሽነት ለማሻሻል፥ወሳኝ የጤና አገልግሎቶችን ፍትሃዊ ተደራሽነት ከማረጋገጥ በተጨማሪም በማስረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔን ለማስተዋወቅ ፥ የተጠያቂነት እና የአፈፃፀም ክትትልን ለማጠናከር እና ዘላቂ የስርዓት ማሻሻያዎችን ለማመቻቸት ያለመ ነው።
በመጨረሻም የ2017 በጀት አመት የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ማነቆዎች ላይ መሠረት ያደረገ የለውጥ አፈፃፀም ላይ የነበሩ ጥንካሬዎችና ክፍተቶች ቀርበው ጥልቅ ውይይት ከተደረገባቸው በኋላ ለ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ በግብዓትነት ተወስደዋል።

የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተከታታይ ሙያ ማሻሻያ ማዕከል ሁሉንም የብሄራዊ መመዘኛ ደረጃዎችን በማሟላት 2018 ዓ.ም የማሰልጠኛ ማዕከል ሆኖ እንዲቀጥል በድጋሜ እውቅና አግኝቷ...
13/08/2025

የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተከታታይ ሙያ ማሻሻያ ማዕከል ሁሉንም የብሄራዊ መመዘኛ ደረጃዎችን በማሟላት 2018 ዓ.ም የማሰልጠኛ ማዕከል ሆኖ እንዲቀጥል በድጋሜ እውቅና አግኝቷል። ለሙያ ፍቃድ እድሳትዎና ጥራት ላለው አገልግሎት ተደራሽነት ዛሬውኑ ይመዝገቡ፣ ይሰልጥኑ፣ ሙያዎን ከጊዜው ጋር ያሻሽሉ

12/08/2025

Address

Addis Ababa Ethiopia Addis Ketema Subcity At The Vicinity Of Mesalemeya
Addis Ababa

Telephone

251944199174

Website

http://WWW.amsh.gov.et/

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amanuel mental specialized hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram