Amanuel mental specialized hospital

Amanuel mental specialized hospital Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Amanuel mental specialized hospital, Addis Ababa ethiopia Addis ketema subcity at the vicinity of Mesalemeya, Addis Ababa.

Emmanuel mental specialized hospital is apionner one which provides mental health care and treatment for about people who are from all corners of the nation and mental health rehabilitation services since it has been established in 1938

07/05/2026
አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀሙን በአዳማ ከተማ በጥልቅ ገመገመ​አዳማ፦ሚያዚያ 27/2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል) አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆ...
05/05/2026

አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀሙን በአዳማ ከተማ በጥልቅ ገመገመ
​አዳማ፦ሚያዚያ 27/2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል) አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀሙን ከመላው ሰራተኞቹ ጋር በመሆን በአዳማ ከተማ በጥልቀት ገመገመ። በግምገማ መድረኩ ላይ "ወረቀት አልባ ተቋም እንገነባለን!" የሚለው የዲጂታላይዜሽን ጉዞ በዋና ትኩረትነት የተነሳ ሲሆን
የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ዋና ዓላማው "ምን ሰራን?" ብለን ራሳችንን ለመጠየቅ ብቻ ሳይሆን፣ "ለነገ ምን የተሻለ ነገር ይዘን እንቅረብ?" ብለን ለመመካከር ፥ ታካሚዎቻችን ከእኛ የሚያገኙት ህክምናና እንክብካቤ ይበልጥ እንዲሻሻል የጋራ ሃሳብ ለማመንጨት እንዲሁም ስራችንን በደህንነትና በቅልጥፍና ለመስራት የሚያስችሉንን ምቹ ሁኔታዎች ለመፍጠር የሚያስችል አቅም የምናጎልበት ነው ሲሉ የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር አቶ ኢዳኦ ፈጆ ተናግረዋል። ዳይሬክተሩ አያይዘውም በአሁኑ ወቅት የንብረት አያያዝና አስተዳደር፣ የግዥ ስርዓት እንዲሁም የህክምና ምዝገባና መረጃ አያያዝ ሙሉ በሙሉ የኤሌክትሮኒክስ የአሰራር ስርዓት የተከተለ መሆኑን አብራርተዋል ። በቀጣይ ሁሉንም የሆስፒታሉን አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ በማድረግ ወረቀት አልባ ተቋም የመገንባቱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም በአፅንኦት አንስተዋል ።
በመድረኩ ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ጥራትና ፍትሃዊ ተደራሽነት ዙሪያ የተከናወኑ ተግባራት በቁልፍ የአፈፃፀም አመላካች መለኪያዎች ላይ ተመስርተው በሪፖርት ቀርበዋል። በዚህም በእያንዳንዱ ቁልፍ የአፈፃፀም መለኪያዎች ላይ የታዩ ጥንካሬዎች ይበልጥ ተጠናክረው የሚቀጥሉበት፣የታዩ ክፍተቶች ደግሞ በቀሪዎቹ ጊዜያት በልዩ ሁኔታ በእቅድ ተይዘው እንደሚተገበሩ ውይይት ተደርጎባቸዋል።
​ በመጨረሻም በቀሪዎቹ 2 ወራት ውስጥ በክፍተት የታዩ ተግባራትን በልዩ ሁኔታ በማቀድና ርብርብ በማድረግ በላቀ ውጤት ለማጠናቀቅ አቅጣጫ ተቀምጧል።
Emmanuel Mental Specialized Hospital reviewed its 9-month plan implementation in Adama City
​Adama: April 27/2018 (EMSH) Emmanuel Mental Specialized Hospital reviewed its 9-month plan implementation for the 2018 fiscal year in Adama City with all its staff. The digitalization journey, "We will build a paperless institution!", was the main focus of the review forum.
The main purpose of the plan implementation review forum is not only to ask ourselves "What have we done?" but also to discuss "What can we bring better for tomorrow?", to generate common ideas to further improve the treatment and care our patients receive from us, and to strengthen our capacity to create favorable conditions that allow us to do our work safely and efficiently, said the hospital's Chief Executive Director, Ato Edao Fejo. The Director explained that currently, asset management and administration, procurement system, and electronic medical record are fully electronic. The Director also emphasized that the work of building a paperless institution by digitizing all hospital services will continue to be strengthened.
The activities carried out in the context of universal health service quality and equitable access were presented in a report based on key performance indicators. In this way, it was discussed that the strengths seen in each key performance indicator will continue to be strengthened, and the gaps seen will be addressed in the remaining periods in a special way.
​ Finally, a direction has been set to complete the activities seen as a gap in the remaining 2 months with special planning and efforts.

30/04/2026

በጤናው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች



Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

እንኳን ለዓለም አቀፍ የላብ አደሮች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!​አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የላቀ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ሌት ከቀን ለምትተጉ የጤና ባለሙያዎችና የእንክብካቤ ሠራተኞ...
30/04/2026

እንኳን ለዓለም አቀፍ የላብ አደሮች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!
​አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የላቀ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ሌት ከቀን ለምትተጉ የጤና ባለሙያዎችና የእንክብካቤ ሠራተኞች በሙሉ እንኳን ለላብ አደሮች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!
​የአእምሮ ጤና አገልግሎት ትዕግስትን፣ ርኅራኄንና ቁርጠኝነትን የሚጠይቅ እንደመሆኑ መጠን ለታካሚዎቻችን እንክብካቤና ደህንነትን ለምታጎናፅፉ ሆስፒታሉ እጅግ የላቀ ክብርና ምስጋና ያቀርብላችኋል።
​"ሥራ ለሰው ልጅ ክብር ነው!"
​መልካም የላብ አደሮች ቀን!
የአማኑኤል አእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ

የአእምሮ ህመም ከታከመ በኋላ ለምን ያገረሻል?አንድ የአእምሮ ሕመምተኛ በሕክምና ታግዞ ካገገመ በኋላ በሽታው ተመልሶ የሚመጣባቸው (የሚያገረሽባቸው) በርካታ ሳይንሳዊና ማህበራዊ ምክንያቶች አ...
29/04/2026

የአእምሮ ህመም ከታከመ በኋላ ለምን ያገረሻል?
አንድ የአእምሮ ሕመምተኛ በሕክምና ታግዞ ካገገመ በኋላ በሽታው ተመልሶ የሚመጣባቸው (የሚያገረሽባቸው) በርካታ ሳይንሳዊና ማህበራዊ ምክንያቶች አሉ። ዋና ዋናዎቹ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፦
​1. መድኃኒትን በአግባቡና እስከመጨረሻው አለመውሰድ
​ይህ በጣም የተለመደው ምክንያት ነው። ታካሚው የተወሰነ መሻሻል ሲሰማው "ድኛለሁ" ብሎ በማሰብ ወይም በመድኃኒቶቹ የጎንዮሽ ጉዳት (Side effects) በመሰላቸት ሕክምናውን ያቋርጣል። የአእምሮ መድኃኒቶች በድንገት ሲቋረጡ በጭንቅላት ውስጥ ያሉ የኬሚካል መዛባቶች ተመልሰው ስለሚመጡ በሽታው በከፋ ሁኔታ ሊያገረሽ ይችላል።
​2. ማህበራዊ ጫና እና መገለል (Stigma)
​ታካሚው ወደ ማህበረሰቡ ሲቀላቀል የሚገጥመው መድልዎ፣ መገለል ወይም "አብዷል" የሚል ስያሜ ለከፍተኛ ስነ-ልቦናዊ ውጥረት ይዳርገዋል። ይህ ሁኔታ ታካሚው በራሱ ላይ ያለውን እምነት እንዲያጣና ወደ ድብርት ወይም ወደ ቀድሞው የጭንቀት ሁኔታ እንዲመለስ ያደርገዋል።
​3. የድጋፍ ስርዓት ማነስ
​ከሕክምና ተቋም የወጣ ሰው የቤተሰብ እና የቅርብ ሰዎች ፍቅር፣ እንክብካቤና ክትትል ያስፈልገዋል። ታካሚው ብቻውን ሲሆን፣ የሚሰማውን ስሜት የሚያካፍለው ሲያጣ ወይም በቤተሰብ ውስጥ ግጭቶች ሲበዙ ለበሽታው የመጋለጥ እድሉ ከፍተኛ ይሆናል።
​4. ሱስ የሚያስይዙ ነገሮችን መጠቀም
​አልኮል፣ ጫት፣ ሲጋራና ሌሎች አደንዛዥ እጾች የአእምሮን ኬሚካላዊ ሚዛን ያዛባሉ። ከሕመም ያገገመ ሰው እነዚህን ነገሮች መጠቀም ሲጀምር መድኃኒቶቹ ከእጾቹ ጋር ይጋጩና ስራቸውን በአግባቡ እንዳይሰሩ ያደርጋቸዋል፤ ይህም ለፈጣን ማገርሸት መንስኤ ይሆናል።
​5. ከፍተኛ የአእምሮ ውጥረት (Stress)
​ከባድ የህይወት ውጣ ውረዶች—ለምሳሌ የስራ ማጣት፣ የቅርብ ሰው ሞት፣ የኢኮኖሚ ችግር ወይም የፍቅር ግንኙነት መቋረጥ አእምሮ ላይ ጫና ይፈጥራሉ። እነዚህ ክስተቶች በሽታውን የሚቀሰቅሱ (Triggers) በመሆን ያገለግላሉ።
​6. የበሽታው ባህሪ (Chronic Nature)
​አንዳንድ የአእምሮ ሕመሞች ልክ እንደ ደም ግፊት ወይም ስኳር ስር የሰደደ (Chronic) ባህሪ አላቸው። ይህም ማለት ሕመሙ ሙሉ በሙሉ ከመጥፋት ይልቅ በክትትል ቁጥጥር ስር የሚውል በመሆኑ ጥንቃቄ ሲጎድል የማገርሸት ተፈጥሮአዊ ባህሪ ሊኖረው ይችላል።
​ምን መደረግ አለበት?
• ​የመድኃኒት ክትትልን በሀኪም ትዕዛዝ ብቻ ማስተካከል።
• ​ለታካሚው ምቹና ሰላማዊ አካባቢ መፍጠር።
• ​የማገርሸት ቅድመ ምልክቶችን (ለምሳሌ እንቅልፍ ማጣት፣ መለፍለፍ፣ ራስን ማግለል) ቀድሞ መረዳትና ወደ ሕክምና መውሰድ።
​ታካሚው ወደ ቀድሞው ስራውና ማህበራዊ ህይወቱ እንዲመለስ የሚያደርጉ አበረታች ተግባራት ማገርሸትን ለመከላከል ትልቅ ሚና አላቸው።
ያለ አእምሮ ጤና ጤና የለም!
የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ

በሶስት የፌዴራል ሆስፒታሎች ረቂቅ የማቋቋሚያ አዋጅ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሄደ​አዳማ ፦ ሚያዚያ 17/2018 ዓ.ም በጤና ሚኒስቴር ስር ተጠሪ የሆኑት አማኑኤል የአእ...
25/04/2026

በሶስት የፌዴራል ሆስፒታሎች ረቂቅ የማቋቋሚያ አዋጅ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በአዳማ ከተማ ተካሄደ
​አዳማ ፦ ሚያዚያ 17/2018 ዓ.ም
በጤና ሚኒስቴር ስር ተጠሪ የሆኑት አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፣ የአለርት ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን በሕግ ለማቋቋም በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይ የሆስፒታሎቹ የጤና ሚ/ር የህግ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚና ባለሙያዎች ከሆስፒታሎቹ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን በአዳማ ከተማ ጥልቅ ውይይት አካሂደዋል።
​በአዳማ ከተማ በተካሄደው በዚህ የውይይት መድረክ ላይ የተቋማቱ የስራ ኃላፊዎች በረቂቅ ሰነዱ ይዘት፣ በሆስፒታሎቹ ስልጣንና ተግባር እንዲሁም ወደፊት በሚኖራቸው አደረጃጀት ላይ ሰፊ ምክክር አድርገዋል።
​በውይይቱ ወቅት ተሳታፊዎቹ ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መካከል ሆስፒታሎቹ በአሁኑ ወቅት ከሚሰጡት የሕክምና አገልግሎት ስፋትና እያከናወኑት ካለው የስልጠናና የምርምር ስራ አኳያ የማስተማሪያ ኮሌጅ መሆን ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተነስቷል።
​የማስተማሪያ ኮሌጅነት መነሻ ሀሳብም ሆስፒታሎቹ ካላቸው ከፍተኛ የሕክምና አገልግሎት ስፋትና ለወደፊት ካቀዱት የማስፋፊያ ስራዎች አንጻር እና አሁን ላይ በተግባር እያከናወኑት የሚገኘውን ከፍተኛ የክሊኒካል ስልጠና እና የምርምር ስራዎችን መሠረት ያደረገ ነው። በመሆኑም
ሆስፒታሎቹ በሕግ "የማስተማሪያ ኮሌጅ" እንዲሆኑ የሚፈቅድ አንቀጽ በአዋጁ ውስጥ እንዲካተት በአፅንኦት ጠይቀዋል።
​ይህ የማቋቋሚያ አዋጅ መጽደቅ ሆስፒታሎቹ የራሳቸው የሆነ ሕጋዊ ሰውነት ኖሯቸው አገልግሎታቸውን በላቀ ሁኔታ ለማሳለጥ፣ ምርምርና ስልጠናን በስፋት ለማከናወን እንዲሁም ተገቢውን በጀትና የሰው ኃይል ለማስተዳደር ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረውም በውይይቱ ላይ በአፅንኦት ተገልጿል። በመጨረሻም
​በመድረኩ ማጠቃለያ ላይም ከአመራሮቹ የተሰበሰቡ ግብዓቶች ታክለውበት ረቂቅ አዋጁ ለሚመለከተው የመንግስት አካል እንዲቀርብ ተጠይቋል።

ሆስፒታሉ የ9 ወራት ዕቅድ አፈጻጸሙን ገመገመ​አዲስ አበባ | ሚያዝያ 16/2018 ዓ.ም​አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት የሥራ አፈጻጸሙን ከከፍተኛና...
24/04/2026

ሆስፒታሉ የ9 ወራት ዕቅድ አፈጻጸሙን ገመገመ
​አዲስ አበባ | ሚያዝያ 16/2018 ዓ.ም
​አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት የሥራ አፈጻጸሙን ከከፍተኛና ከመካከለኛ የሆስፒታሉ አመራሮች ጋር በሰሜን ሆቴል በጥልቀት ገመገመ።
በመድረኩ ላይ በዘጠኝ ወራት ውስጥ የታቀዱ ዋና ዋና ተግባራት፣ የተመዘገቡ ስኬቶች እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ላይ ዝርዝር ውይይት ተደርጓል። በተለይም ለታካሚዎች በሚሰጠው የተሃድሶና የህክምና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነትን በማስጠበቅ ረገድ እንዲሁም የሆስፒታሉን አገልግሎት ለማዘመን የተከናወኑ የዲጅታላይዝድ ጤና ሪፎርም ሥራዎች ተቋማዊ ለውጥን ከማጠናከርና ከማስቀጠል ረገድ የነበረው የትግበራ ሂደት እንዲሁም የሆስፒታል አመራሮች በተመደቡበት የስራ ሃላፊነት በአግባቡ ሚናቸውን የመወጣት፥የክትትልና የቁጥጥር ስርዓት አተገባበር ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል። በመጨረሻም ሆስፒታሉ የአእምሮ ጤና አገልግሎትን ይበልጥ ተደራሽ እና ጥራቱን የጠበቀ ለማድረግ ተሳታፊዎቹ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡ ሲሆን
በቀሪዎቹ ሦስት ወራት ውስጥ ትኩረት የሚሹ ተግባራትና የትኩረት መስኮች ተለይተው እንዲከናወኑ አቅጣጫ ተሰጥቶበቶ መግባባት ላይ ተደርሷል።
​The hospital evaluates the 9-month plan performance.
​Addis Ababa | April 16, 2018 E.C.
Emmanuel Mental Specialized Hospital's senior and middle management met at the Simen Hotel to discuss the hospital's 9-month 2018 fiscal year performance.
The forum included a detailed discussion of the main activities planned for the next nine months, as well as the achievements and challenges encountered. In particular, the digitalized health reform implementation outcome was carried out to modernize hospital services, strengthen and sustain institutional change, and implement the monitoring and control system to ensure that hospital managers properly fulfill their assigned responsibilities. Finally, the participants reaffirmed their commitment to improving access and quality of mental health services at the hospital, and they agreed to identify and prioritize activities and areas of focus for the next three months.

24/04/2026
በሆስፒታል ቅጥር ግቢ ውበትና ፅዳት ባለሙያዎች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫና የተግባር ስልጠና ተሰጠ​አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 14/2018 ዓ.ም ( አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)​አማኑኤል የአእምሮ ስ...
22/04/2026

በሆስፒታል ቅጥር ግቢ ውበትና ፅዳት ባለሙያዎች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫና የተግባር ስልጠና ተሰጠ
​አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 14/2018 ዓ.ም ( አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)
​አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በግቢ ውበትና ፅዳት መጠበቅ ላይ ለተሰማሩ ባለሙያዎች በበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫና የተግባር ስልጠና ተሰጠ። ስልጠናው በዋናነት የሆስፒታል ኢንፌክሽንን ለመከላከል፥የታካሚንና የባለሙያዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ያለመ ነው።
በስልጠናው ላይ በሆስፒታል ውስጥ የሚከሰቱ ኢንፌክሽኖች (Hospital-Acquired Infections) እንዴት እንደሚተላለፉና እነዚህን ለመከላከል የፅዳት ባለሙያዎች መከተልና መተግበር ያለባቸው እርምጃዎች ተመላክተዋል።
በተጨማሪም የደህንነት ቁሳቁስ ማለትም የጓንት፣ የጭንብል (Mask) እና የሌሎች የግል መከላከያ ቁሳቁሶችን (PPE) ትክክለኛ አጠቃቀምና አወጋገድ ላይ የተግባር ልምምድ ተደርጓል እንዲሁም የፅዳት ኬሚካሎችንና ቁሳቁሶችን በምን መልኩ በጥንቃቄ መጠቀም እንደሚገባና ለጤና ጠንቅ የሆኑ ቆሻሻዎችን (Medical Waste) እንዴት መለየትና ማስወገድ እንደሚቻል በስልጠናው የተብራራ ሲሆን የሆስፒታሉን ምድረ-ግቢ ውበት መጠበቅ ለታካሚዎች የስነ-ልቦና እረፍት ከመስጠቱም ባለፈ ፅዳቱ የተጠበቀ ግቢ ለበሽታ አምጪ ተህዋሲያን መራቢያ እንዳይሆን ማድረግ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫው ስልጠና ሌላው የትኩረት ነጥብ ተደርጎ ተሰጥቷል።
​በመጨረሻም ስልጠናው የሆስፒታሉን የአገልግሎት ጥራት ለማሻሻልና ለታካሚዎችም ሆነ ለሰራተኞች ምቹና ደህንነቱ የተጠበቀ የሕክምና አካባቢ ለመፍጠር ከፍተኛ ፋይዳ ያለው መሆኑ በሁሉም ሰልጣኞች ዘንድ ግንዛቤ ተጨብጦበታል።

21/04/2026

Address

Addis Ababa Ethiopia Addis Ketema Subcity At The Vicinity Of Mesalemeya
Addis Ababa

Telephone

251944199174

Website

http://WWW.amsh.gov.et/

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amanuel mental specialized hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share