05/05/2026
አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀሙን በአዳማ ከተማ በጥልቅ ገመገመ
አዳማ፦ሚያዚያ 27/2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል) አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀሙን ከመላው ሰራተኞቹ ጋር በመሆን በአዳማ ከተማ በጥልቀት ገመገመ። በግምገማ መድረኩ ላይ "ወረቀት አልባ ተቋም እንገነባለን!" የሚለው የዲጂታላይዜሽን ጉዞ በዋና ትኩረትነት የተነሳ ሲሆን
የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ዋና ዓላማው "ምን ሰራን?" ብለን ራሳችንን ለመጠየቅ ብቻ ሳይሆን፣ "ለነገ ምን የተሻለ ነገር ይዘን እንቅረብ?" ብለን ለመመካከር ፥ ታካሚዎቻችን ከእኛ የሚያገኙት ህክምናና እንክብካቤ ይበልጥ እንዲሻሻል የጋራ ሃሳብ ለማመንጨት እንዲሁም ስራችንን በደህንነትና በቅልጥፍና ለመስራት የሚያስችሉንን ምቹ ሁኔታዎች ለመፍጠር የሚያስችል አቅም የምናጎልበት ነው ሲሉ የሆስፒታሉ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር አቶ ኢዳኦ ፈጆ ተናግረዋል። ዳይሬክተሩ አያይዘውም በአሁኑ ወቅት የንብረት አያያዝና አስተዳደር፣ የግዥ ስርዓት እንዲሁም የህክምና ምዝገባና መረጃ አያያዝ ሙሉ በሙሉ የኤሌክትሮኒክስ የአሰራር ስርዓት የተከተለ መሆኑን አብራርተዋል ። በቀጣይ ሁሉንም የሆስፒታሉን አገልግሎቶች ዲጂታላይዝድ በማድረግ ወረቀት አልባ ተቋም የመገንባቱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም በአፅንኦት አንስተዋል ።
በመድረኩ ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ጥራትና ፍትሃዊ ተደራሽነት ዙሪያ የተከናወኑ ተግባራት በቁልፍ የአፈፃፀም አመላካች መለኪያዎች ላይ ተመስርተው በሪፖርት ቀርበዋል። በዚህም በእያንዳንዱ ቁልፍ የአፈፃፀም መለኪያዎች ላይ የታዩ ጥንካሬዎች ይበልጥ ተጠናክረው የሚቀጥሉበት፣የታዩ ክፍተቶች ደግሞ በቀሪዎቹ ጊዜያት በልዩ ሁኔታ በእቅድ ተይዘው እንደሚተገበሩ ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በመጨረሻም በቀሪዎቹ 2 ወራት ውስጥ በክፍተት የታዩ ተግባራትን በልዩ ሁኔታ በማቀድና ርብርብ በማድረግ በላቀ ውጤት ለማጠናቀቅ አቅጣጫ ተቀምጧል።
Emmanuel Mental Specialized Hospital reviewed its 9-month plan implementation in Adama City
Adama: April 27/2018 (EMSH) Emmanuel Mental Specialized Hospital reviewed its 9-month plan implementation for the 2018 fiscal year in Adama City with all its staff. The digitalization journey, "We will build a paperless institution!", was the main focus of the review forum.
The main purpose of the plan implementation review forum is not only to ask ourselves "What have we done?" but also to discuss "What can we bring better for tomorrow?", to generate common ideas to further improve the treatment and care our patients receive from us, and to strengthen our capacity to create favorable conditions that allow us to do our work safely and efficiently, said the hospital's Chief Executive Director, Ato Edao Fejo. The Director explained that currently, asset management and administration, procurement system, and electronic medical record are fully electronic. The Director also emphasized that the work of building a paperless institution by digitizing all hospital services will continue to be strengthened.
The activities carried out in the context of universal health service quality and equitable access were presented in a report based on key performance indicators. In this way, it was discussed that the strengths seen in each key performance indicator will continue to be strengthened, and the gaps seen will be addressed in the remaining periods in a special way.
Finally, a direction has been set to complete the activities seen as a gap in the remaining 2 months with special planning and efforts.