Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C

Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C Fit Corner Sport & ConsultancyPLC sport training , consultancy company based in Ethiopia Addis Ababa.

Weekends are for dreamers, but also for doers. Saturday grind mode 💪Thanks Hugre!!!
30/08/2025

Weekends are for dreamers, but also for doers. Saturday grind mode 💪
Thanks Hugre!!!

26/08/2025

በ መሀል ፒያሳ ፊት ኮርነር

ዛሬ ማለዳ ደማቅ የማሕበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በአድዋ ድል ሙዚዬም ተካሄደ፡፡ነሃሴ 11/2017 ዓ.ም፡ አዲስ አበባ******=****ዛሬ ከማለዳው ጀምሮ የፊት ኮርነር ስፖርት ...
17/08/2025

ዛሬ ማለዳ ደማቅ የማሕበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በአድዋ ድል ሙዚዬም ተካሄደ፡፡
ነሃሴ 11/2017 ዓ.ም፡ አዲስ አበባ
******=****
ዛሬ ከማለዳው ጀምሮ የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ጂም አባላት፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የአካባቢው ማሕበረሰብ በተገኝበት ለዩ የማስ-ስፖርት እንቅስቃሴ አድዋ ድል መታሰቢያ ውስጥ በሚገኝው የሁለገብ ጂም ውስጥ ተከናውኗል፡፡ ይህም በዋናነት ማህበረሰቡ ነቁ የአኗኗር ዘይቤ ባህል እንዲያደርግ የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑን ኢንስትራክተር ነጻነት ካሣ ገልጸዋል፡፡
ተምሣሣይ ማሕበረሰቡን የሚያሳትፉ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች በፊት ኮርነር ስፖርት አማካኝነት በቋሚነት እየተከናወኑ መሆኑ ይታወቃል፡፡
======//=====

የሕይወት ዘመን መምህር; ምርጥ ሞደል ;የማይረሳ አባት: ቅን የዋህ መካሪ ወንድም ቤዛብህ ነብስህ በስላም ትረፍ::
16/08/2025

የሕይወት ዘመን መምህር; ምርጥ ሞደል ;የማይረሳ አባት: ቅን የዋህ መካሪ ወንድም ቤዛብህ ነብስህ በስላም ትረፍ::

📌 ላልተዘመረለት ጀግና የኢ/አ/ፌ ሀዉልት አቆመለት!!

| ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ ሃታኡ (ዶ/ር)፤ ከሐምሌ 23/1952 – ነሃሴ 19/2014 ዓ.ም

👉 ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ በቀድሞው ባሌ ክፍለ ሀገር ልዩ ስሙ ጊኒር በሚባል አካባቢ ሐምሌ 23/1952 ዓ.ም ተወለዱ፡፡

የእስፖርት ሳይንሱ አባት ዶ/ር በዛብህ ወልዴ ሰብእናው፥ ሙያው እና ሕይወቱ በአንድ ቃል ይገለጽ ቢባል ያ ቃል "ፈውስ" ነው።
እጁ የአካል ሰብራትን ሲጠግን ንግግሩ መንፈስን ከድቀት ይታደጋል።

ሁሉንም ሰው እንደየመልኩና እንደየ አመሉ በፍቅርና ከልብ በመነጨ ፈገግታ መቀበሉ፤ ለኹሉም የሚዳረስ የጊዜ በረከት የታደለ መሆኑ ወዳጆቹን ዘወትር እንዳስደነቀ ይኖራል።

ረጅም ቁመናው ብዙዎችን ለማስጠለል ለሚችለው ጠባዩ ጥሩ ምሳሌ ይሆናል።

ዕድልና አጋጣሚ አግኝተን ባወቅነው ፤በቀረብነው ፥ ባወጋነው ዘንድ የማይረሳ የሰው አብነት ነው።
ቸሩ እግዚአብሔር ነፍሱን ከደጋጎች ጎራ እንዲያሳርፍ እንጸልያለን።

በትምህርቱ ዘርፍ የነበራቸው አበርክቶ
***
➡️ ትምህርታቸውን በጅማ መምህራን ማሰልጠኛ ተቋም፣ በኮተቤ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ ፤በቡልጋሪያ አገር በሶፊያ ሰውነት ማጎልመሻ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፤በፖላንድ አገር በሚገኘው ዋርሶ የሰውነት ማጎልመሻ ማእከል ተከታትለው በከፍተኛ ማዕረግ ተመርቀዋል ።

➡️ በኮተቤ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት፣ በምርምር ስራዎችና በማህበረሰብ አገልግሎት የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል፤

➡️ ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ሶስተኛ ዲግሪ መርሀ-ግብሮች በመምህርነት አገልግለዋል፤

➡️ በአገር ውስጥና ከአገር ውጪ በሚገኙ የተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተጋበዥ መምህርነት፣ ተማሪዎችን በማማከርና የምርምር ስራዎችን በማቅረብ አገልግለዋል፤

በስፖርቱ ዘርፍ ነበራቸው አበርክቶ
***
በኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ ‹‹የአትሌቲክስ አባት›› ተብለው ከሚታወቁ የዘርፉ ምሁራንና ባለሙያዎች መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠሩ አንጋፋና ባለውለታ ነበሩ፡፡

ከ20 አመት በላይ በአትሌቲክሱ ላይ እጅግ ደማቅ አሻራቸውን ያሳረፉ ሲሆን ከብዙው በጥቂቱ ለመጥቀስ:-

➡️ በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በዋና ፀኃፊነት፣

➡️ በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በዋና ፀኃፊነት፣ በሥራ አስፈጻሚ ኮ/አባልነት፣ በአቃቢ ነዋይነት አገልግለዋል።

➡️ በአትላንታና በሲድኒ ኦሎምፒክ በዝግጅትና በአመራር፤

➡️ በኤድመንተን ዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአመራርነት፤

➡️ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በፕሬዚዳንትነት፣

➡️ በአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
በፕሬዜዳንትነት እንዲሁም

➡️ በቴክኒክና በህክምና ኮሚቴ ሰብሳቢነት ፣በአቃቤ ነዋይነት እስከ ህልፈተ ህይወታቸው ድረስ ደከመኝ፣ ሰለቸኝ ሳይሉ አትሌቲክሱን ያገለገሉ የኢትዮጵያ ባለውለታ በመሆናቸው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሙሉ ወጪዉን በመሸፈን የመታሰቢያ ሐውልት በስማቸው አሰርቶላቸዋል።

ሐዉልቱም የፊታችን ጳጉሜ 2 በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ⛪ ቤተክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቹ ፣የሙያ አጋሮቹ እንዲሁም የቀድሞ ተማሪዎቹ በተገኙበት የሚመረቅ ይሆናል።

ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ ለኢትዮጵያ እስፖርት ላደረከዉ አስተዋፅኦ ሁሌም እናመሰግንሀለን ።🙏🙏🙏🙏🙏

ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ ሃታኡ ነሃሴ 19/2014 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡

በተስፋዬ አብዲሳ (ቻይና አብዲ)

በቀን 7 ሺህ እርምጃዎችን መራመድ የአዕምሮ ጉልበትን ለመጨመር እና ከተለያዩ በሽታዎች ለመከላከል በቂ ሊሆን እንደሚችል አንድ ጥናት አመለከተ።ከ10 ሺህ እርምጃዎች በላይ መራመድ የበለጠ ጠቃ...
11/08/2025

በቀን 7 ሺህ እርምጃዎችን መራመድ የአዕምሮ ጉልበትን ለመጨመር እና ከተለያዩ በሽታዎች ለመከላከል በቂ ሊሆን እንደሚችል አንድ ጥናት አመለከተ።

ከ10 ሺህ እርምጃዎች በላይ መራመድ የበለጠ ጠቃሚ ሊሆን አንደሚችል ያመለከተው ጥህ ጥናት ይህም ብዙ ጊዜ እንደ ግብ ሊታይ እንደሚችል ገልጿል።

https://bbc.in/40ZoZZP

Between glass towers and cobblestone alleys, Frankfurt whispered stories of the past and dreams of tomorrow.  # German  ...
04/08/2025

Between glass towers and cobblestone alleys, Frankfurt whispered stories of the past and dreams of tomorrow.
# German
# Frankfurt

02/08/2025
Disneyland Paris, A place full of wonder and magic where both kids and adults can feel like they’re part of a story.It’s...
31/07/2025

Disneyland Paris,
A place full of wonder and magic where both kids and adults can feel like they’re part of a story.
It’s a place where imagination become a reality.

In Paris, even the silence feels like a story.Some of unforgettable moments at Eiffel Tower.
29/07/2025

In Paris, even the silence feels like a story.
Some of unforgettable moments at Eiffel Tower.

After some hectic weeks, I’m off to Europe for a little break. Any friends in France 🇫🇷 or Germany 🇩🇪 — raise your hand!...
28/07/2025

After some hectic weeks, I’m off to Europe for a little break. Any friends in France 🇫🇷 or Germany 🇩🇪 — raise your hand! 👋
Goodbye, Addis!”

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Fit Corner sport Training & Consultancy P.L.C:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram