Hawi agre

Hawi agre Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Hawi agre, AIDS Resource Center, Addis Ababa.

15/07/2024

በብዝሀነታችን ተደምረን በአብሮነታችን ደምቀን ፤ በህብረታችን ታሪካዊ አሻራ ማሳረፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን!

የኢትዮጵያውያን የከፍታ ሚስጢር ህብረታችን ነው።
አባት እናቶቻችን በህብረብሔራዊነት ደምቀው ዘመን ተሻጋሪ ታሪክ ሰርተዋል።

ኢትዮጵያ ታፍራና ተከብራ የኖረችው ዜጎቿ በውስጣቸው ያለውን ልዩነት ወደ ጎን በማለት ለአገር ክብር እና ለህዝብ ደህንነት ቅድሚያ በመስጠታቸው ነው።

በሁሉም ብሔር ብሔረሰብ ያሉን እንቁ ባህሎቻችን እና እሴቶቻችን ከትውልድ ትውልድ ሊሸጋገሩ የቻሉትም በየጊዜው የመጡ ወራሪ ሀይሎችን በጋራ መመከት በመቻላቸው ነው።

ኢትዮጵያውያን በተደመረ አቅም ለውጡን አምጥተዋል ፣ አፅንተዋል እንዲሁም አስቀጥለዋል።

ፓርቲያችን ህዝባችን ዕምቅ አቅሙን ተጠቅሞ ኑሮውን እንዲያሻሽል እና አገሩን እንዲያበለፅግ ከወሰዳቸው ቀዳሚ እርምጃዎች መካከል አገር በቀል የሆነውን የመደመር ፍልስፍና ተግባራዊ ማድረግ ነው፡፡

መደመር አቃፊ ነው። መደመር የሀሳብ ብዝሀነት እና ብዝሀ ማንነት የኢትዮጵያ ፀጋ መሆናቸውን በፅኑ ያምናል።

ፓርቲያች የተግባር ፓርቲ በመሆኑ አደርጋለሁ ባለበት ቅፅበት ዕቅዶቹን ይተገብራል። ለአብነትም አገራዊ ለውጡ ዕውን በሆነባት ዕለት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ ለአገረ መንግስት ግንባታው ከሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በትብብር በፉክክር እንደሚሰራ አመላክተው የነበረ ሲሆን ባለፉት የለውጥ ዓመታት የታየውም ይኸው ነው፡

ሁሉም ዜጋ ለአገሩ ታሪካዊ አሻራውን ማሳረፍ እንደሚገባው የማይዋዥቅ አቋም ያለው ፓርቲያችን ከሁሉም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በትብብርና በፉክክር መስራት ኢትዮጵያን ወደ ልዕልና እንደሚወስዳት ይገነዘባል።

ከለውጡ በኋላም ኢትዮጵያውያን በመሰባሰባችን የማይታለፉ የሚመስሉ ፈተናዎችን ተሻግረናል ፤ ብሄራዊነትን አንግበን የአገራችንን ልዕልና አስጠብቀናል።

በጋራ በመቆማችን ተግዳሮቶች ሳይበግሩን አንፀባራቂ ድሎችን አስመዝግበናል።

እየተገባደደ ያለው ታላቁ የህዳሴ ግድባችን ክንዳች አስተባብረን ለጋራ ነገአችን በመነሳታችን የተገኘ ስኬት ነው።

በአረንጓዴ አሻራ እየተጎናፀፍን ያለው ስኬት ሌሎች አገራት ላይም መንፈሳዊ ቅናት ፈጥሯል።

የገጠሩም የከተማውም አርሶ አደሩም አርብቶ አደሩም በህብር ባይነሳ በስንዴ ምርታማነት ላይ ያስመዘገብነው ድል አይታሰብም።

በጋራ በመቆማችን ተደማጭነታችን ጨምሯል ፤ በዚህም ብሪክስን የመሳሰሉ ዓለም አቀፍ ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብስቦች በራቸውን ከፍተውልናል።

የከተማችን ህዝብም አዲስ አበባን የሁላችንም ቤት በማለት ገፅታዋን ለመቀየር ቀን እና ሌት ከከተማ አስተዳደሩ ጎን ተሰልፎ በመትጋቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደ ስሟ ማበብ የጀመረች ከተማ ማየት ችሏል።

ታላቁ ትርክታችን የሆነውን ብሔራዊነትን አንግበን ፣በብዝሀነታችን ተደምረን በአብሮነታችን ደምቀን ፤ በህብረታችን ታሪካዊ አሻራ ማሳረፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን!

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት


15/07/2024
15/07/2024
14/07/2024

የሀገረ መንግስት ግንባታ የትውልድ ቅብብሎሽ ውጤት ነው።

ሀገር የትውልዶች ትስስር ውጤት ናት። የትውልድ ቅብብሎሽ ሲባል፣ በትውልዶች መካከል በሚኖር ጠንካራ ተግባቦት የሚፈጠር፣ የጠንካራ እሴት መወራረስ ነው።

በዚህ አይነት መንገድ መልካም ያልሆኑ እሴቶች እየታረሙ፣ ጠንካራ ሀገራዊ እሴቶች ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገሩ፣ ዘመኑን እየዋጁ ሲሄዱ፣ ሀገር እየተጠናከረ ይመጣል።

ትውልዶች የሚያልፉበት ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ የተለያየ ከመሆኑ የተነሳ፣ በትውልዶች መካከል የሚኖር ልዩነት አይቀሬ ነው።

አልፎ አልፎም ልዩነቱ ወደ ተቃርኖና የለየለት ጠላትነት ሊለወጥ ይችላል። በትውልዶች መካከል ያለውን ልዩነት ተረድቶ ለማስማማትና ለማቻቻል አለመሞከር በትውልዶች መካከል የትስስር ክፍተት ይፈጥራል።

ይህ የትውልድ ትስስር ክፍተት እየሰፋ ሲሄድ በሀገር ጥንካሬ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል። በቀደመውና በተተኪው ትውልድ መካከል ያለው የዕሴትና የባህሪ ልዩነት እጅግ የሰፋ ሲሄድ በማህበረሰብ መካከል የጥቅም ግጭት በመፍጠር አፍራሽ ሀገራዊ ሁኔታ ይፈጥራል።

አንዱ የአንዱን ሁኔታ የሚገነዘብ ሳይሆን፣ ተተኪው የቀደመውን አምርሮ የሚጠላ፣ የቀደመው ተተኪውን የሚያብጠለጥል በመሆኑ፣ ባለው ላይ የመገንባት ሳይሆን የማፍረስ ባህል እንዲፈጠር ያደርጋል።

ትውልድ አብሮ የተገመደና የተቋጠረ ብቻ ሳይሆን እንደ ወንዝ ሳያቋርጥ የሚፈስስ የዘመንና የክሥተት ውጤት ነው። ሊሸከሙትና ሊያሻግሩት የማይችሉትን የምልከታ መነጽሮቹን አውልቆና የአተያይ አድማሱን አስፍቶ ፤ የራሱን ፈተና በማሸነፍ ለሚቀጥለው ትውልድ የተሻለ ሀገርን ማስረከብ ፤ የዚህ ትውልድ ጊዜ የማይሰጥ የቤት ስራ ነው።


11/07/2024

ከፍ ብለን አስበን በጥራትና ፍጥነት ተግተን እየሰራን ልዕልናችንን እናበስራለን!

ዘመንን በዋጀ ተደማሪ ዕሳቤ የሚተጋ ትውልድ ሩቅ አስቦ ዝቅ ብሎ በመስራት አቧራን አራግፎ ምንዳ የሚሆን አሻራን ያሳርፋል። ለዚህ ነው ፓርቲያችን በከፍታ አስቦ ሁለንተናዊ ልዕልናን ለማረጋገጥ እየተጋ የሚገኘው። በብልጽግና ራዕይና ትጋት ተጨባጭና የሚታይ እምርታዎችን እያስመዘገበ ቃልን በተግባር በማጽናት ወደ ብርሃናማ ጉዞ እየተሻገርን ነው።

ብልፅግና የሀሳብ ልዕልና ያለው በተግባራ የተፈተነ ውጤታማ ፓርቲ ነው። ፓርቲያችን እሩቅ ያልማል፣ አስቦ ያቅዳል፣ ያቀደውን በመፈፀም ስኬት ያስመዘግባል።

ፓርቲያችን የዘመነ አሰራርና ስርዓት ዘርግቶ የህዝባችንን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ በሚያደርጋቸው ጥረቶች አጠቃላይ ህዝባችንም የልማት ተነሳሽነት ከፍ ብሏል። በተጨባጭም በርካታ ሰው ተኮርና የበጎ ፈቃድ ተግባራት በህዝባችን የገንዘብ የጉልበትና የእውቀት ተሳትፎ በርካታ ዕምርታዎች ተመዝግበዋል።

በመዲናችን አዲስ አበባ በአስተደማሚ ጥራትና ፍጥነት እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የከተማዋን ከፍታ በማብሰር የተሞክሮ ማዕከል አድርጓታል። ሳይታክቱ በሚታትትሩ የብልጽግና እጆች አዲስ አበባ እውነትም አዲስና አበባ ሆናለች። እናቅዳለን፤ ያሰብነውን አሳክተን አስደማሚ ድሎችን እያስመዘገብን ልዕልናችንን በመመለስ ቀና ብለን ቀና ብሎ የሚራመድ ምንዳ ያለው ትውልድና ሀገር እንገነባለን። ከፍ ብለን አስበን፤ በህብር ደመቀን በትጋት እየሰራን ብልጽግናዊ ተምሳሌትነታችንን እናበስራለን።

በብልጽግና የመደመር ከፍታ ጉዞ በየተሰማራንበት የስራ መስክ ተልዕኳችንን እየተወጣን፣ በስኬት ፈፅመን ውጤት እናስመዘግባለን፤ የህዝባችንን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጥን በድምር የከተማችንን የብልፅግና ተምሳሌት እናፀናለን!

Abiy Ahmed Ali



Adanech Abiebie- አዳነች አቤቤ
Moges Balcha Gebremedhin

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hawi agre posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram