ጌጡ ተመስገን ውልደቱና እድገቱ አዲስ አበባ ነው። በጋዜጠኝነት ሙያው፤ ለአገር እና ለሕዝብ በሠራቸው አይረሴ ሥራዎቹ በርካታ ሽልማቶችን አግኝቷል። የፈረንሳይ ቴሌቪዥን ባሰባሰበው የተመልካቾች ምዘና መሠረት ‹‹ባለንሥሩ ጋዜጠኛ ~ A Journalist with an eagle eye›› የሚል ስያሜ አግኝቷል።
Getu Temesgen was born and raised in Addis Ababa. As a result of his unforgettable journalistic works/TV productions, he has won various recognitions. He was named “The Journalist with an eagle eye” in an audience poll conducted by French TV.
ሦስት ሥራዎቹም በፈረንሳይኛ ቋንቋ ተተርጉሞ ቀርበውለታል። በአዘጋጁቹ ግብዣ አውሮፓ ፤ ጀርመን፣ ጣልያን፣ ፈረንሳይና ቤልጅየም ተጉዞ፤ ትምህርታዊ ጉብኝት በማድረግ አገር ቤት ተመልሷል።
His three TV productions were also presented for European audience in French language and as a result was invited by the producers to visit France, Germany, Italy and Belgium.”
በ2002ዓ.ም. ለመጀመሪያ ጊዜ በተዘጋጀው የመገናኛ ብዙሃን ብሔራዊ የአረንጓዴ ሽልማት ‹‹በቴሌቪዥን ዘርፍ›› አንደኛ ደረጃ ተሸላሚና የላቀ ዘጋቢ የክብር ዋንጫ ከቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዚደንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ እጅ ተቀብሏል።
In 2010, Getu Temesgen was the winner of the National Championship of “National Green Award” .He received a trophy and a certificate from the hands of the late H.E Girma Wolde-Georgis (The President Federal Democratic Republic of Ethiopia for “the outstanding production ‘in TV Journalist Category’”.
የኮንሶ መልክዓ ምድር የኢትዮጵያ ዘጠነኛ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ ባደረገው ተከታታይ ሥራዎች በተለይ የጥበቃ ድንበር (Buffer zone) እንዲበጅላቸው ቀድሞ በቴሌቪዥን ዘገባው አገር እና ሕዝቡን በመቀስቀሱ ምክንያት ዩኔስኮ፣ የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣንና የኮንሶ ልዩ ወረዳ በጋራ ሸልመውታል።
As an effect of his influential journalistic/TV reporting, ‘Greening Konso’, recommending a buffer zone establishment for the Konso community landscape terracing enabled it to become a UNESCO Proscribed Heritage site. And he was honored as “Green Hero” by UNESCO and the Ethiopian National Heritage Research and Protection Authority.
በጣና አዋርድ እንዲሁም በኢትዮ ሶሻል ሚዲያ አዋርድ በፈጣን፣ ተአማኒ ወቅታዊ መረጃ ዘርፍ በተከታታይ ዓመታት አሸናፊ ሆኗል። የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲም በታሪክ ዘርፍ አሸናፊ ለሆነው ለሙሃዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት እና በፈጣን፣ ተአማኒ ወቅታዊ መረጃ ዘርፍ አሸናፊው ለጌጡ ተመስገን 70 ሺህ ብር የሚያወጣ ነጻ የትምህርት እድል በክብር ሰጥቷቸዋል፡፡
He is the winner of the 1 st and 2 nd TANA Social Media Award in the ‘Fast Reliable and Balanced Reporting category’. The Bahir Dar University also awarded his a scholarship for him.
ጌጡ ተመስገን ደህንነቱ የተጠበቀ ደም ለሁሉም ❤ Safe Blood for all- በሚል ዓለም አቀፍ መርህ፤ በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ የነፍስ አድን ስጦታ በማበርከት፤ ደም በመለገስ ይታወቃል፡፡
Getu works as a volunteer for the Ethiopian Blood Bank of the Ethiopian Red Cross Society and participates in its campaign “Safe Blood for all”.
https://youtu.be/pFeWKuf-_hk
የ - Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) - ፌስቡክ ገጽ ቤተሰቦች እንሆ ወቅታዊ ዜናዎችን፣ ታሪኮችንና ሃሳቦችን ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እንዲሁም ከዓለም ዙሪያ ታገኛላችሁ። በየቀኑ ወቅታዊ ክንውኖችን በሰዓቱ ለማግኘት ገጻችንን ጎብኙ፤ ሃሳባችሁንም አጋሩን። በተጨማሪም እንድናቀርበው የምትፈልጓቸው ታሪኮችም ካሉ ጠቁሙን።
GetuTemesgen365.com is your news and entertainment website. We provide you with the latest breaking news, stories, pictures and video films on Ethiopia and beyond. Please visit our page daily and send us information tips and story ideas that you may think is newsworthy.
ፌስቡክ ገጽ ቤተሰቦቻችንን - እጅ ነስተን እናመስግናለን!
We Thank You!