09/11/2025
በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ለኬዝ ቲም ሃላፊዎች የኢንፌክሽን ቅድመ መከላከል ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጫ ስልጠና ተሰጠ።
በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ጥቅምት 30/2018 ዓ.ም
የግንዛቤ ማስጨበጫውን የሰጡት የ infection prevention ኬዝ ቲም ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ደስታ አእምሮ ሲሆኑ ስለ ስልጠናው ጠቃሚነት አጠንክረው ተናግረዋል።
በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ለኬዝ ቲም ሃላፊዎች የኢንፌክሽን ቅድመ መከላከል ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጫ ስልጠና መሰጠቱ ተቋሙ ለሚሰጠው ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት እጅግ ጠቃሚ ነው ተብሏል።
ስልጠናው በዋናነት infection prevention ሲሆን በተለይ የህክምና መሳሪያዎች አጥቦ መልሶ መጠቀም ( instrumental processing) ላይ እንዲሁም አጠቃላይ የህክምና መሳሪያዎች እንዴት መጠቀም እንደሚገባ እንዲሁም አጠቃላይ በየ ክፍሉ ያሉ የአገልግሎት መስጫ ስፈራዎች ንፅህናቸው የተጠበቀ መሆኑ ላይ አጠንጥኗል።
በስልጠናው ላይ የተሳተፉት የየክፍሉ የኬዝ ቲም ሃላፊዎች እንዳሉት አጠቃላይ የህክምና መሳሪያ አጠቃቀምና / አጥቦ መልሶ መጠቀ እና የህክምና ስፍራዎች ንፅህናቸው የጠበቁ እንዲሆኑ ስልጠናው ጠቃሚ ነው ብለዋል።
📌 Follow Us on Social Media
👉 Facebook:
https://www.facebook.com/profile.php?id=100063650457050
👉 Telegram: Join Our Channel https://t.me/Y12HMCC
👉 Follow us on tiktok
https://vm.tiktok.com/ZMHWJyPGKQmQp-dftjE/
🔖