Yekatit 12 Hospital Medical College

Yekatit 12 Hospital Medical College Yekatit 12 Hospital was founded in 1923 and one of the 1st modern hospitals in the country.

Yekatit 12 Hospital started providing medical education in 2011 and changed its name to Yekatit 12 Hospital Medical College.

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ሰራተኞች በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት ነፃ የህክምና አገልግሎት ሰጡ።የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮ...
06/08/2025

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ሰራተኞች በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት ነፃ የህክምና አገልግሎት ሰጡ።

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ሃምሌ 30/2017 ዓ.ም

እንደሚታወቀው የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በተቋሙ ከሚሰጣቸው የጤና አገልግሎቶች መካከል በተጨማሪ ህክምና የሚሹ የማህበረሰብ ክፍሎችን እዛው ባሉበት ሄዶ የጤና የህክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ ይታወቃል።

በተለይ የአዕምሮ ህሙማን ማዕከላት የአረጋውያንን ማቆያ ማዕከላት ወላጅ አልባ ህፃናት በጥቅሉ የተለያዩ መርጃ ማዕከላት ተቋሙ ለሚሰጣቸው የጤና አገልግሎቶች መዳረሻ ናቸው።

በመሆኑም በዛሬው እለት የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎትን አስመልክቶ በተቋሙ በCRC & MCC አስተባባሪነት 52 የሚደርሱ የጤና ባለሙያዎች በሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት የተለያዩ የጤና ህክምና አገልግሎት ሰጥተዋል።

በዛሬው ዕለተ በሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ለ352 ሰዎች የተደረገው የህክምና ድጋፍ ለታካሚዎቹ እጅግ እፎይታን የሰጠ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።

በተለይ በህክምና ሂደቱ ላይ የተሳተፉት ባለሙያዎች እንደገለፁት በዚህ ቦታ ተገኝቶ ይህንን ነፃ የህክምና አገልግሎት መስጠት ለነፍስ ደስታን ይሰጣል በማለት ተናግሯል። በተጨማሪም መሰል ኘሮግራሞች እንዲዘጋጅላቸውም የ CRC & MCC ክፍልን ጠይቀዋል ።

ተቋማችን የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ሰራተኞች ከዚህም በፊት በተለያዩ ግዚያት በሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በመገኘት ለወገኖቻችን የጤና አገልግሎት በመስጠት ለታማሚዎቹ እፎይታ መስጠታቸው ይታወሳል

በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የ2018 ዓ.ም የእቅድ ዝግጅት በጥናትና ምርምር ዘርፍ ቀረበ።የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ሃምሌ 30/2017 ዓ.ምተቋሙ የካቲት 12...
06/08/2025

በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የ2018 ዓ.ም የእቅድ ዝግጅት በጥናትና ምርምር ዘርፍ ቀረበ።

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ሃምሌ 30/2017 ዓ.ም

ተቋሙ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ እየሰጠ ከሚገኘው አገልግሎት ውስጥ አንዱ የሆነው የጥናትና ምርምር ዘርፍ ሲሆን በዚህ ጥናትና ምርምር ዘርፍ የ2018 ዓ.ም እቅድ ዝግጅትን አቅርቧል።

ዘርፉ በተለይ እንደሃገር ጥራቱን የጠበቀ የመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ system oriented medical education (SOME) የተሰኘውን የመማሪያ ስልት በመቅረፅ ተግባራዊ እያደረገ የሚገኝ ሲሆን በዚህም ጥሩ ውጤቶችን አያመጣም ይገኛል።

በዚህ የጥናትና ምርምር የ2018 ዓ.ም የእቅድ ዝግጅት ግምገማ እቅድ የቀረበ ሲሆን በቀረበው እቅድ ላይ የተቋሙ ሃላፊዎች በመገኘት እቅዱን በጥልቀት ገምግመዋል።

የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የጥናትና ምርምር ም/ኘሮቮስት ዶ/ር መረርቱ ተመስገን በእቅድ ዝግጅቱ ላይ በመገኘት እቅዱን የገመገሙ ሲሆን እቅዶቹ ስራ ላይ ውለው ተግባራዊ እንዲሆኑ ለተቋማችን የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ የሁላችንም ርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል።

ልሳን ዘየካቲትሐምሌ 29/2017 ዓ.ም"የእያንዳንዱ ደም ለጋሽ ሕይወት አዳኝ ነው!"የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ደም ባንክ ክፍል÷ ሰብዓዊ አገልግሎቱን ዛሬም ቀጥሏል!በተለያዩ የጤና...
05/08/2025

ልሳን ዘየካቲት
ሐምሌ 29/2017 ዓ.ም

"የእያንዳንዱ ደም ለጋሽ ሕይወት አዳኝ ነው!"

የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ደም ባንክ ክፍል÷ ሰብዓዊ አገልግሎቱን ዛሬም ቀጥሏል!
በተለያዩ የጤና ክህሎት የደም ማነስ ለሚያጋጥማቸው ሕመምተኞች፤
ከፍ ያለ ቀዶ ሕክምና ለሚያስፈልጋቸው፤
በተለያዩ አደጋዎች ሳቢያ ብዙ ደም ለሚፈሳቸው፤
በወሊድ ወቅት ብዙ ደም ለሚፈሳቸው እናቶች፤
በተለያዩ የጤና ችግሮች ሳቢያ እንደተወለዱ ደም ለሚያስፈልጋቸው ሕፃናት፤...በሚተካ ደም የማይተካ ሕይወት ለመታደግ÷
ደም መለገስ አንዳችም ጉዳት አያስከትልም!
ደም በመለገስ የወለዱ እናቶቻችንን እና በደም እጦት የሚሞቱ መገኖቻችንን ሕይወት እንታደግ÷ በማለት እንደከዚህ በፊቱ
በትላንትናውም ዕለት ከግቢ ውጪ እራሳቸውን አርአያ/ሞዴል/ ከማድረግ ባሻገር ማኅበረሰቡም እንዲሳተፍ በማስተባበር በአንድ ቀን 37 ዩኒት ደም ማሰባሰብ ተችሏል። ኮሚቴዎቹም ደም የለገሱትን ሠራተኞች እና ሕዝቡን በማመስገን÷ሠራተኛውም ለወደፊት ካቀድናቸው የደም ማሰባሰብ መርሐ ግብር እንዲሁም የወገን ማዳን ሥራ ላይ ርብርብ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

ሠናይ ቀን!

02/08/2025
26/07/2025
የአርትሮስኮፒ ቀዶ ህክምናበየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በአጥንት ህክምና ዓለም የደረሰበትን የመገጣጠሚያ ህክምና ቴክኖሎጂ በማካተት የአርትሮስኮፒ ቀዶ ህክምና እየተሰጠ ይገኛል።የአርት...
21/07/2025

የአርትሮስኮፒ ቀዶ ህክምና

በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በአጥንት ህክምና ዓለም የደረሰበትን የመገጣጠሚያ ህክምና ቴክኖሎጂ በማካተት የአርትሮስኮፒ ቀዶ ህክምና እየተሰጠ ይገኛል።

የአርትሮስኮፒ ህክምና እና የመገጣጠሚያ ቅየራ ሠብ ስፔሻሊስት የሆኑት ዶ/ር ሠኢድ መሐመድ እንዳሉት ይህ ዘዴ መገጣጠሚያ እምብዛም ሳይከፈት የሚካሄድ መሆኑን ገልፀው: ሂደቱ በትንንሽ ቀዳዳዎች ብቻ መገጣጠሚያ ውስጥ ያሉ ችግሮችን በካሜራ እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ከፍተኛ ቀዶ ህክምና የሚካሄድበት አማራጭ መሆኑን አስረድተዋል።

በተለይም እንደ ACL እና Meniscus ያሉ የጉልበት መገጣጠሚያ አካላት በስፖርት ወይም በሌሎች አደጋዎች፣ አልያም በተራዘመ ጫና ምክንያት ሲጎዱ፣ መገጣጠሚያን መክፈት ሳያስፈልግ በዚህ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አማራጭ የበርካቶችን ችግር መቅረፍ እንደተቻለ አብራርተዋል።

በቀጣይም ይህንን ቀዶ ህክምና በማስፋት ተጨማሪ የቀዶ ህክምና አይነቶችን ለመጀመር ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።

አበበች ጎበና እናቶችና ህፃናት ሆስፒታል ሰራተኞች የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎትን አስመልክቶ  በሙዳይ በጎ አድራጎት ማህበር በመሄድ የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌ...
15/07/2025

አበበች ጎበና እናቶችና ህፃናት ሆስፒታል ሰራተኞች የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎትን አስመልክቶ በሙዳይ በጎ አድራጎት ማህበር በመሄድ የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ሃምሌ 8/2017 ዓ.ም

ተቋሙ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ
በአበበች ጎበና እናቶችና ህፃናት ህክምና ማዕከል ለእናቶችና ህፃናት ህክምና ከፍተኛ የሚባለውን ህክምና እየሰጠ ይገባል።

የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎቱን የሰጠው ተቋሙ በተጨማሪም ሃያት አደባባይ ላይ ደም የማሰባሰብ መርሃግብር አካሂዷል በመርሃግብሩም በርካታ ሰዎች ተሳትፈዋል።

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ
በአበበች ጎበና እናቶችና ህፃናት ህክምና ማዕከል ሴንተር ዳይሬክተር ዶ/ር ዱረቲ ጀማል የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎቱን አስመልክተው ሲገልፁ በቀጣይ የምናከናውናቸው የክረምት በጎ ፍቃድ የጤና አገልግሎቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

በዛሬው እለት የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል  ኮሌጅ ሰራተኞች ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ላይ አሻራቸውን አሳረፉ። የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ሃምሌ 6/2017 ዓ.ም"በመ...
13/07/2025

በዛሬው እለት የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ሰራተኞች ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ላይ አሻራቸውን አሳረፉ።

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ሃምሌ 6/2017 ዓ.ም

"በመትከል" ማንሰራራት በሚል መሪ ቃል እየተከናወነ በሚገኘው ሃገር አቀፍ 7ተኛው ዙር የችግኝ ተከላ መርሃግብር በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ ሁለት ዩኒሳ አደባባይ ተከናውኗል። በመርሃግብሩ ላይ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ እና አበበች ጎበና ሰራተኞች በስፋት ተሳትፏል

በችግኝ ተከላ መርህ ግብሩ ላይ የሆስፒታሉ ሶስቱም ኘሮቮስቶች በመገኘት አሻራቸውን ያኖሩ ሲሆን ከተቋሙ አበበች ጎበና እናቶችና ህፃናት ህክምና ማዕከልን ጨምሮ ከሁሉም ዲፓርትመንቶች የተወጣጡ ባለሙያዎች አሻራቸውን አኑረው ተመልሰዋል።

ተቋሙ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ከችግኝ ተከላው ባሻገርም የተከላቸውን ችግኞች ሰራተኞቹን በማሰባሰብና እዛው የተከለበት ድረስ በመሄድ ችግኞቹን በመንከባከብ ለግብ እያደረሰ እንደሆነ ይታወቃል

ነፃ ህክምና በክበበ ፀሃይ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የክረምት በጎ ፍቃድን አገልግሎትን አስመልክቶ በክበበ ፀሐይ የሕፃናት ጊዜያዊ ማቆያና እንክብካቤ ማዕከል በመገኘት ነፃ ህክምና ...
11/07/2025

ነፃ ህክምና በክበበ ፀሃይ

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የክረምት በጎ ፍቃድን አገልግሎትን አስመልክቶ በክበበ ፀሐይ የሕፃናት ጊዜያዊ ማቆያና እንክብካቤ ማዕከል በመገኘት ነፃ ህክምና ሰጠ።

ካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል አዲስ አበባ ሃምሌ 4/2017 ዓ.ም

በህክምናው 30 የሚደርሱ የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የህፃናት ህክምና ስፔሻሊስት ሃኪምች የአይን ስፔሻሊስት ሃኪሞች ከአንገት በላይ ስፔሻሊስት ሃኪሞች ረዝደንት ሃኪሞች ጤና መኮንኖችና ነርሶች የበጎፍቃድ አገልጋዮችና ሌሎች ባለሙያዎች በመገኘት 250 ለሚደርሱ ህፃናት ነፃ ህክምና ሰጥተዋል።

በተቋሙ CRC/MCC አስተባባሪነት እየተከናወነ የሚገኘው የክረምት በጎ ፍቃድ ህክምና አገልግሎት በሌሎችም የመረጃ ማህከላት እንደሚቀጥል ተነግሯል።

ዶ/ር አበበ ታደሰ የህፃናት ስፔሻሊስት ሃኪምና ረ/ኘሮፌሰር እንዲሁም የተቋም የህክምና አሰጣጥ ም/ኘሮቮስት የህክምና አገልግሎቱን አስመልክቶ እንደገለፁት በክበበ ፀሃይ አገልግሎቱ ዛሬ ላይ ብቻ የሚቆም ሳይሆን በቀጣይም ተካታታይነት ያለው የጤና አገልግሎት እንሰጣለን ብለዋል።

1956 ዓ.ም የተመሰረተው በክበበ ፀሐይ የሕፃናት ጊዜያዊ ማቆያና እንክብካቤ ማዕከል በየጊዜው በርካታ ህፃናት ህይወት እየታደገ ይገኛል።

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የላብራቶሪ ዳይሬክቶሬት የ2017 ዓ.ም በጀት አመት እቅድ አፈፃፀምን ገመገመ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲሰ አበባ ሃምሌ 2/2017 ዓ.ም የተ...
09/07/2025

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የላብራቶሪ ዳይሬክቶሬት የ2017 ዓ.ም በጀት አመት እቅድ አፈፃፀምን ገመገመ

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲሰ አበባ ሃምሌ 2/2017 ዓ.ም

የተቋሙ የላብራቶሪ አገልግሎት ከጊዜ ወደ ጊዜ የአገልግሎት አድማሱን በማስፋት የተለያዩ ዘመኑን የዋጁ የላብራቶሪ መሳሪያዎችን በመጠቀም ቀልጣፋና ጥራቱነን የጠበቀ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

ክፍሉ ዘመኑ በደረሰበት የላቦራቶሪ መሳሪያ በመጠቀም የተገልጋዮችን እርካታ እየጨመረም ይገኛል።

በዛሬው ዕለት በተደረገው የ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ አበበች ጎበናን ጨምሮ ከ7 የኬዝ ቲም ሃላፊዎች እንዲሁም በየክፍሉ የተሻለ አፈፃፀም ላመጡ ባለሙያዎች የዕውቅና ሰርተፍኬት ተሸልመዋል።

ዳይሬክቶሬቱ በዛሬ እለት በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ላይ መልካም አፈፃፀም ላበረከቱ ሰራተኞች እውቅና ሲሰጥ የካቲት 12 ሆስፒል ሜዲካል ኮሌጅ ኘሮቮስት ዶ/ር አንተነህ ምትኩ እና የህክምና አሰጣጥ ም/ኘሮቮስት ዶ/ር አበበ ታደሰ በመገኘት የእውቅና ሰርተፍኬቱን ሸልመዋል።

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የክረምት ነፃ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት  ተጠናክሮ እንደቀጠለ ይገኛል የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ሃምሌ 2/2017 ዓ.ም ተቋሙ የካቲት...
09/07/2025

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የክረምት ነፃ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተጠናክሮ እንደቀጠለ ይገኛል

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ሃምሌ 2/2017 ዓ.ም

ተቋሙ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ለማህበረሰቡ በክረምት ወራት የሚሰጣቸውን የበጎ አድራጎት ስራዎች በከፍተኛ ሁኔታ እያካሄደ እንዳለ ይታወቃል።

እያከናወናቸው ካሉ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎቶች መካከል ወረፋ ለሚጠባበቁ የቀዶ ህክምና አገልግሎት መስጠት የቅድመ የማህፀን በር ካንሰር ምርመራ ማድረግ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ልየታ ማድረግ በተለያዩ በታዎች በመሄድ የጤና ትምህርት መስጠት ለባለሙያዎች የሙያ ስነምግባር ስልጠናዎችን መስጠት እነዚህ ለአብነት የሚጠቀሱ ሲሆን ሌሎች በርካታ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል።

በቀጣይም መሰል ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተነግሯል።

የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ጥምረት ለጥረት አራተኛው ሳይክል ኢቢሲ ምዘና ተካሄደየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ሐምሌ 1/2017 ዓ.ምየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በሀገር ...
08/07/2025

የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ጥምረት ለጥረት አራተኛው ሳይክል ኢቢሲ ምዘና ተካሄደ

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ሐምሌ 1/2017 ዓ.ም

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው ውድድር አዲስ አበባን ወክለው ከሚወዳደሩ አራት እጩ ሆስፒታል ለመሆን የሚያስችለውን የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ጥምረት ለጥረት አራተኛው ሳይክል ኢቢሲ ምዘና (Ethiopian Hospital Alliance For Quality(EHAQ) 4th cycle - Evidence Based Audit tool) በዛሬው ዕለት ተካሄዷል።

መመዘኛው ከሦስት መቶ በላይ መስፈርቶችን ያካተተ ሲሆን በተከታታይ ለሦስት ጊዜ የተካሄደ ሲሆን የዛሬው አራተኛው እና የመጨረሻው ነው። ውጤቱም በቅርቡ ይታወቃል።

በዚህ ምዘና ጥሩ ውጤት ያመጣ ተቋም አዲስ አበባ ከተማን ወክሎ ለሀገር አቀፉ ውድድር እጩ ይሆናል ለዚህም ስኬት መላው የሆስፒታላችን ሰራተኞች ትልቅ ርብርብ ያደረጉ ሲሆን፤ ይህም የሆስፒታላችንን የቡድን ስራና ቤተሰባዊ ግንኙነት ያሳየ ነው ያሉ ሲሆን ውጤቱም አዎንታዊና ሥራችንን ያማካለ እንደሚሆን ባለሙሉ ተስፋ እንደሆኑ የሆስፒታሉ አመራሮች ገልጸዋል።

የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ዋና ፕሮቮስት ዶክተር አንተነህ ምትኩ "ለየዲፓርትመንት ሀላፊዎች ፣ ኬዝ ቲም አስተባባሪዎች እና ለመላው ሰራተኞች ተቋማችን የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በዛሬው ዕለት በነበረው የአገር አቀፍ የሆስፒታሎች የ Evidence based Care (EBC) የዕውቅና ምዘና ላይ ለነበራቹ ተነሳሽነት ፣ ትጋትና ብርታት በተቋሙ ስም ከልብ አመሰግናለሁ።" በማለት ለመላው ሰራተኞች ያላቸውን አድናቆትን ክብር ገልጸዋል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yekatit 12 Hospital Medical College posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Yekatit 12 Hospital Medical College:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram