ጤና ይስጠን-Tena Yisten

ጤና ይስጠን-Tena Yisten ጤና ነክ መረጃዎች የሚተላለፉበት እና ትምህርታዊ ጽሁፎች የሚለጠፉበት መድረክ ነው።

ጤና ይስጠን: ጤና ይስጣችሁ።
Tena-Yisten Medical Information. add a member...

16/11/2025

#ሰበር — የጂንካ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ከስራ ተባረሩ !

መርበርግ የተባለ አደገኛ ቫይረስ የ6 ሰዎችን ህይወት በቀጠፈ ማግስት የሆስፒታሉ ሜዲካል የዳይሬክሩ መባረር አነጋጋሪ ሆኗል።

ሜዲካል ዳይሬክተሩ የተባረሩትም አለማቀፉ ሚድያ በቫይረሱ የሞቱ ዜጎች መኖራቸውን በማረጋገጣቸው እንደሆነም የውስጥ ምንጮች ነግረውናል።

ከሰሞኑ ምንነቱ ባልታወቀ በሽታ የ 6 ሰዎች ህልፈትን ተከትሎ የማህበራዊ ሚድያዎች ትኩረት በጂንካ ሆስፒታል ላይ አነጣጥሯል።

ቫይራል ሄሞሬጅክ ፌቨር የተሰኘው አደገኛ የቫይረሶች ቡድን ተከተሰተ መባሉን ተከትሎ በተደረገ የሟቾች የደም ናሙና ምርመራ ውጤት ማርበርግ የተሰኘ አደገኛ ወረርሽኝ መከሰቱ ተሰምቷል።

የሟቾቹ የናሙና ምርመራ ውጤትን መነሻ በማድረግ በፌደራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና በኢትዮጽያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት በኩል የወረርሽኙን ክስተት ያረጋገጡ መግለጫዎችም በማህበራዊ ሚድያ ገጾቻቸው ያሰራጩ ሲሆን አለም ዓቀፉ የጤና ድርጅትም አፋጣኝ የገንዘብ፣ የሙያተኛና የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉም ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።

ይህንን ተከትሎ ከጀርመን ድምጽ ራድዮ ጣቢያ ዶቼቬሌ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የጂንካ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ቢኒያም አስራት የወረርሽኙ ክስተት ሞት ማስከተሉን ያረጋገጡበትን ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ 4 ታካሚዎችና የህክምና እርዳታ ያደረጉላቸው 2 ሀኪሞች፤ 1 ዶክተርና 1 ነርስ ህይወት ማለፍን ያረጋገጡት ሜዲካል ዳይሬክተሩ የሟቾችን ቁጥር መግለጻቸው ተከትሎም ሜዲካል ዳይሬክተሩ ከስራቸው መባረራቸው ተሰምቷል።

የቀረበው ውንጀላም ለአለማቀፉ የሚድያ ተቋም DW የተከሰተውን ሃቅ ያረጋገጠ መረጃ ሰጥተሃል በሚል ውንጀላ መሆኑንም ከሆስፒታሉ የመረጃ ምንጮች ለማረጋገጥ ችለናል።

የፌደራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት በሰጡት በመግለጫ በሆስፒታሉ በቫይረሱ የተጠረጠሩ ሰዎችን እንጂ የሞቱ ሰዎች መኖራቸውን ያልገለጹ ቢሆንም ዳይሬክተሩ ይህንኑ ይፉ ማድረጋቸውን ተከተሎ ከስራ መታገዳቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ደርሷቸዋል።

የተከሰተው ቫይረስ እጅግ አደገኛና ገዳይ መሆኑ እየተገለጸ የሟቾችን ቁጥር መደበቅ ለምን እንደተፈለገ የታወቀ ነገር ባይኖርም ሃቁን ባለመደበቃቸው የተወነጀሉት ሜዲካል ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቢኒያም አስራት አደገኛ ዛቻና የእስር ማስፈራሪያ እየደረሱባቸው መሆኑንም ለማረጋገጥ ችለናል።

ከስራ የተባረሩበት ደብዳቤ የደረሳቸው ሜዲካል ዳይሬክተሩን ለማነጋገር ተደጋጋሚ ጥረት ብናደርግም በዚህ ጉዳይ ምንም አስተያዬት ለማንም መስጠት እንደማይፈልጉ በመግለጽ ስልካቸውን ዘግተዋል።

ሆኖም ግን የእገዳ ደብዳቤው በክልሉ የጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ ጫና አድራጊነት የተጻፈባቸው መሆኑን ከሆስፒታሉ የውስጥ ምንጮች ለማረጋገጥ ችለናል።

በስራው ታታሪና ትጉህ የሆነው የጂንካው ተወላጅ ዶ/ር ቢኒያም ሆስፒታሉን ለማሻሻል እየተጋ ቢሆንም በተደጋጋሚ ጫና ውስጥ መቆየቱን ጠቁመው እውነተኛ መረጃ መስጠት ኃላፊነቱን በመወጣቱ ሊመሰገን ሲገባው ከስራ መታገዱ ተገቢ አይደለም ብለዋል።

በአለማቀፉ የጤና ተቋም ተረጋግጦ በመንግስት መግለጫ በተሰጠበት ጉዳይ መረጃ ምንም አይነት ክልከላ በሌለበት፤ ዶ/ሩ መባረር እውነታን ለመደበቅ የሚፈልግ አካል ሴራ ሊሆን ይችላል የሚሉት ምንጮቹ ሃቀኛ መረጃ እንዲሸፈን የተፈለገበት ምክንያት ግን ምን ሊሆን እንደሚችል አናቅም ብለዋል።

አስደንጋጭ እልቂት ያስከትላል የሚለው የቫይረሱ ስጋት ባጠላበት ጂንካ ሆስፒታል ከሟቾች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው በርካታ ዜጎች በተጠርጣሪነት ተለይተው በሚገኙበት በዚህ ወቅት

በከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ የሚገኘው ነዋሪ ከመንግስት የሚሰጡ መመሪያዎችና የጥንቃቄ መልዕክት እየተጠባበቀ ቢሆንም የክልሉ ጤና ቢሮና የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት መገኛ በሆነው ጅንካ ክስተቱን በተመለከተ የክልሉ ልሳን የሆነው የደቡብ ሬድዮና ቴሌቭዥን ድርጅትም፤ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥንንም ሆነ ሌሎች ሚድያዎች ዝምታን መምረጣቸው አነጋጋሪ ሆኗል።”

💥 ዶ/ር ቢኒያም አስራት በአስቸኳይ ወደ ስራው እንዲመለስ እንጠይቃለን! እውነት መናገር መረጃ ለሚዲያ መስጠት ወንጀል አይደለም። የሚመለከታቸው አለም አቀፍ ተቋማት ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ እንጠይቃለን። EHPM ለአለም አቀፍ ተቋማት እና ኤምባሲዎች በቀጣይ ቀናት ደብዳቤ የሚያስገባ ይሆናል።

በጂንካ ያላቹ ጤና ባለሞያዎች ስለ ዶ/ር ቢኒያም እና በMVD ምክንያት ስለሞቱት 6 ሰዎች የተብራራ መረጃ በ በአስቸኳይ ላኩልን!

13/11/2025

.World Health Organization (WHO) is working closely with Ministry of Health,Ethiopia , the Ethiopia Public Health Institute and regional health authorities as part of the rapid response to a suspected outbreak of a viral haemorrhagic fever (VHF) in the Southern Ethiopian Region.

8 people, including health workers, have reportedly been infected.

WHO has deployed experts to the affected towns, along with medicines and other materials to support care for people in need, and personal protective equipment for health workers.

WHO will also be supporting contact tracing in affected communities. Samples have been sent for testing. Further details are expected soon.

I have released US$300,000 from the WHO Contingency Fund for Emergencies to provide immediate support.

WHO’s offices in Ethiopia and South Sudan are collaborating closely to prevent potential cross-border transmission. WHO is ready to scale up support, as and when needed.

I commend Ethiopian health authorities for their timely sharing of information and quick response and offer WHO’s full support.

https://www.afro.who.int/news/ethiopia-reports-suspected-viral-haemorrhagic-fever-outbreak

12/11/2025

ወቅታዊ የጤና ጉዳይን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

Website: moh.gov.et
Facebook: facebook.com/EthiopiaFMoH
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

በጅንካ ጀነራል ሆስፒታል ሰሞኑን ምን ተከሰተ?ከበሽታው ጋር ተያይዞ እስካሁን 5 ሰው የሞቱ ስሆን አንዱ በፅኑ ህመም ውስጥ ይገኛል።ከዚህ ጋር በመያያዝ በከተማዋ የተለያዩ ወሬዎች እየተናፈሱ ...
12/11/2025

በጅንካ ጀነራል ሆስፒታል ሰሞኑን ምን ተከሰተ?
ከበሽታው ጋር ተያይዞ እስካሁን 5 ሰው የሞቱ ስሆን አንዱ በፅኑ ህመም ውስጥ ይገኛል።ከዚህ ጋር በመያያዝ በከተማዋ የተለያዩ ወሬዎች እየተናፈሱ ይገኛል።ይህን ሁኔታ ጋር ተያይዞ በሆስፒታሉ የሚሰሩ አንዳንድ ባለሙያዎች እንዳሉት ሁሉም የሞቱቱ መጀመሪያ ከሞተው ታማም ጋር ንክኪ የነበራቸው መሆኑና በሁሉም ላይ አንድ ምልክቶች መታየታቸው እና በሽታው በአጭር ግዜ(3-5)ቀን ውስጥ ለሞት የሚዳርግ በመሆኑ ሁሉም በፍርኃት ተውጠው እንገኛለን።ለምሳሌ በሽተኛውን በዕለቱ (ከዛሬ አንድ ሳምንት በፊት) እያከመ የነበረ አንድ ዶክተር ትላንት በስቲያ ሰኞ ህይወቱ ያለፈ በመሆኑና በአከባቢው ሌሎችም ንክኪ ያላቸው ብዙ ስዎች በመኖራቸው አስፈላጊ ጥንቃቄ ለማድረግ የክልሉ ጤና ብሮ እና ጤና ጥበቃ ሚንስትር አስፈላጊ መረጃ ለሕዝቡ ይፋ እንድያደርግ።ዛሬም ምሽትም ተጨማሪ ሁለት ሰው ሞቶ አድረዋል።አንዱ የሆስፒታሉ ነርስ ነው
#በውስጥ #መስመር #የተላከ

12/11/2025
ራዲዮሎጂ ጥበብ ነው ፣ ፅድት ያለ ጥበብ ☢️🎭ዛሬ ደሞ አለም አቀፍ የራዲዮሎጂ ቀን ነው። አምላክ ከአዕምሮ በላይ በሆነው ጥበቡ ያበጃጀውን የሰው ልጅ አካል ከውስጥ እስከ ውጭ በአይን ከሚታየ...
09/11/2025

ራዲዮሎጂ ጥበብ ነው ፣ ፅድት ያለ ጥበብ ☢️🎭

ዛሬ ደሞ አለም አቀፍ የራዲዮሎጂ ቀን ነው። አምላክ ከአዕምሮ በላይ በሆነው ጥበቡ ያበጃጀውን የሰው ልጅ አካል ከውስጥ እስከ ውጭ በአይን ከሚታየው እስከማይታየው አብጠርጥረን የምናይበት ጥበብ።

የሰው ልጅ ከፅንሰቱ ጀምሮ እስኪወለድ ድረስ የዕድገት እና የሰውነት ለውጦችን የምንከታተልበት መነፅር

- ለሀኪሙ ጥርጣሬ ማረጋገጫ ሰጪ
- ለቀዶ ህክምና እስፔሻሊስቱ አስተማማኝ አቅጣጫ ጠቋሚ ኮምፓስ
- ለማህፀን እና ፅንስ እስፔሻሊስቱ ብርቱ አጋር
- ለተጨነቀች እናት እረፍት ሰጪ፣ የፅንሷን ሰለም መሆን አብሳሪ::

ጨረራን እንደ ጦር ፣ የድምፅ ሞገድን እንደ አጉይ መነፀር ፣ የመግነጢስ ኃይልን እና የራዲዮ ሞገድን እንደ ስንቅ በመጠቀም ይህን ድንቅ የህክምና ጥበብ የምንሰራ፣ የህክምና ራድዮሎጂ ባለሞያዎች ደሞ ዛሬ ቀናችን ነው 😊

In short, radiology professionals bridge technology and compassion, turning invisible energy into visible answers helping medicine see, decide, and heal with confidence.

መልካም አለም አቀፍ የራዲዮሎጂ ቀን ለሁላችን።
Happy world Radiography day. ☢️💪

Naol Geleta.
Medical Radiology Technologist , lecturer AMU
©Hakim
ጤና ይስጠን-Tena Yisten

01/11/2025
31/10/2025

ይህ ድራማ አይደለም!

ነርስ ይመስገን ጌታ ይባላል ።በአሶሳ ዩኒቨርስቲ በ 2013ዓም 3.9 ይዞ የተመረቀ ነው በአሁኑ ሰዓት በሉማሜ የመ/ደ/ሆስፒታል ነው የሚስራ።ነርስ ይመስገን በሚከፈለዉ ደመወዝ ቤተሰቡን ማስተ...
23/09/2025

ነርስ ይመስገን ጌታ ይባላል ።በአሶሳ ዩኒቨርስቲ በ 2013ዓም 3.9 ይዞ የተመረቀ ነው በአሁኑ ሰዓት በሉማሜ የመ/ደ/ሆስፒታል ነው የሚስራ።ነርስ ይመስገን በሚከፈለዉ ደመወዝ ቤተሰቡን ማስተደደር ስላልቻለ በትርፍ ሰዓቱ ፍራፍሬ እና እንጨት ፈልጦ እየሸጠ ይተዳደራል
።ፍትህ ለጤና ባለሙያዎች።

His name is Yemesgen Geta. He graduated from Asosa University in 2013 with a BSc in Nursing, earning a GPA of 3.9. He currently works at Lumame Primary Hospital. However, because the salary he receives is not enough to feed his family or cover basic living expenses, he is forced to sell fruits and vegetables on the streets to survive. Sadly, Yetages’ struggle reflects the reality of many Ethiopian health professionals. Despite their education and service, they cannot afford to provide for their children or pay their rent. It is heartbreaking to see those dedicated to saving lives being humiliated and pushed into such conditions.
💔🔛

Dr. Mekdelawit Mesfin, MD, FCS-ECSAConsultant Pediatric Surgeon | Assistant ProfessorGraduate of Addis Ababa University,...
21/09/2025

Dr. Mekdelawit Mesfin, MD, FCS-ECSA
Consultant Pediatric Surgeon | Assistant Professor

Graduate of Addis Ababa University, School of Medicine

Fellow of the College of Surgeons of East, Central and Southern Africa (COSECSA)

Associate Member, American College of Surgeons

Currently serving at Yekatit 12 Hospital Medical College, Dr. Mekdelawit Mesfin is a highly trained and dedicated Pediatric Surgeon, committed to advancing surgical care for children and mentoring the next generation of medical professionals.
via Y12 HMC
ጤና ይስጠን-Tena Yisten

Dr Gezahegn Germo,gold medalist from Yirgalem hospital medical college, medicine class of 2025
07/09/2025

Dr Gezahegn Germo,gold medalist from Yirgalem hospital medical college, medicine class of 2025

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጤና ይስጠን-Tena Yisten posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram