23/01/2026
በቅርቡ ህክምና ማጥናት ላያስፈልግ ይችላል - ኤሎን መስክ
አሜሪካዊው ቢሊየነር ኤሎን መስክ፣ በቅርቡ ዶክተር ለመሆን ህክምና ማጥናት ላያስፈልግ እንደሚችል መግለጹን ተከትሎ፣ በወደፊቱ የህክምና ዕጣፈንታ ላይ አዲስ ክርክር አስነስቷል።
ማስክ ከፒተር ዲያማንዲስ ጋር በMoonshots ፖድካስት ላይ ሲናገር፤ በሦስት ዓመት ውስጥ በኤአይ የሚታገዙ ሮቦቶች የሰው ቀዶ ጥገና ሃኪሞችን ሊልቁ እንደሚችሉ ሞግቷል፡፡
ሃኪሞችን ለማሰልጠን በጣም ረጅም ጊዜ እንደሚፈጅ የጠቆመው ቢሊየነሩ፤ በዚያ ላይ የስራ ሰአታቸው ውስን ነው ብለዋል፡፡ የሰው ሃኪሞች ስህተት ሊሰሩ እንደሚችሉም ጠቁሟል፡፡
"ምን ያህል ታላላቅ የቀዶ ጥገና ሐኪሞች አሉ? ያን ያህል አይደሉም" ብሏል መስክ፡፡
ሰዎች አሁንም የሕክምና ትምህርት ቤት መሄድ አለባቸው ወይ ተብሎ ለተጠየቀው ሲመልስም፤ “አዎ፣ ከንቱ ነው” ሲል መልሷል፡፡
©addisadmas
እርስዎስ ምን ይላሉ በዚህ ዙርያ?
ጤና ይስጠን-Tena Yisten