ጤና ይስጠን-Tena Yisten

ጤና ይስጠን-Tena Yisten ጤና ነክ መረጃዎች የሚተላለፉበት እና ትምህርታዊ ጽሁፎች የሚለጠፉበት መድረክ ነው።

ጤና ይስጠን: ጤና ይስጣችሁ።
Tena-Yisten Medical Information. add a member...

በብዙ እንቅልፍ አልባ ሌሊቶች የተገኘ የወርቅ ሜዳልያ📌የዶክተር ሜሮን ለገሰ ድል  | አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት በተለያዩ የሕክምና ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 263 አዳዲስ ባለሙያዎችን...
21/03/2026

በብዙ እንቅልፍ አልባ ሌሊቶች የተገኘ የወርቅ ሜዳልያ

📌የዶክተር ሜሮን ለገሰ ድል

| አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት በተለያዩ የሕክምና ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 263 አዳዲስ ባለሙያዎችን ሲያስመርቅ፣ የአንድ ወጣት ጥረትና ጽናት በክብር አዳራሹ ውስጥ በልዩ ድምቀት ተስተጋብቷል።

ለዓመታት የዘለቁ አድካሚ የጥናት ሌሊቶች፣ እረፍት የሌላቸው ቀናትና ፈታኝ ፈተናዎች ዛሬ በደስታ እንባና በድል አክሊል ተተክተዋል። በዚህ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ከመላው ተመራቂዎች የላቀ 3.95 ውጤት በማስመዝገብ የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ለመሆን የበቃችው ዶክተር ሜሮን ለገሰ የዕለቱ ደማቅ ኮከብ ሆናለች።

የስኬቱ ምስጢር፡ ትጋትና ድጋፍ

ዶክተር ሜሮን ስኬቷን አስመልክቶ ለጋዜጣ ፕላስ በሰጠችው ቃል፣ መንገዱ አልጋ በአልጋ እንዳልነበረ ገልጻለች። "ፈተናው ቢነገር አያልቅም" የምትለዋ ሜሮን፣ ለዚህ ክብር እንድትበቃ የሚከተሉት ወሳኝ ነበሩ ብላለች፦

* የፈጣሪ እገዛ፡ በሁሉም እርምጃዎቿ አጋዥ እንደነበራት።

* የቤተሰብና የመምህራን ድጋፍ፡ ከጎኗ ያልተለዩዋት የቤተሰቧ አባላትና ዕውቀት ያጋሯት መምህራኖቿ።

* የጊዜ አጠቃቀም፡ ሰፊ ንባብና ከፍተኛ ትኩረት የሚጠይቀውን የሕክምና ትምህርት በብቃት ለመወጣት ጊዜዋን በአግባቡ የመጠቀም ጥበቧ።

"ትምህርቱ ሰፊ የማንበብ ጊዜና ትኩረት የሚጠይቅ ነበር፤ ነገር ግን ያን ጊዜ በአግባቡ መጠቀሜ ዛሬ ለዚህ ስኬት አብቅቶኛል" — ዶክተር ሜሮን ለገሰ

ዶክተር ሜሮን በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሴት ተማሪዎች ውጤታማነት እየጨመረ መምጣቱ ለሌሎች ተነሳሽነት እንደሚፈጥር ጠቅሳለች። ትምህርቷን አጠናቃ ስትመረቅ ግን የያዘችው ትልቁ ራዕይ ሜዳልያውን ማጥለቅ ብቻ አይደለም፤ ሕዝቧንና ሀገሯን በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል ነው።
ጤና ይስጠን-Tena Yisten

17/03/2026

Meet Dr. Meron Legesse, the gold medalist from Addis Ababa University's medicine class of 2026, with a CGPA of 3.95.

10/03/2026

Award vs Reality: The Truth About Ranking

Every hospital seems to be claiming first place in the FMoH national quality competition… and some of them are the exact places having terrible patient care.

A few years back, when I was working at a hospital, the FMoH evaluators were coming. Staff rushed to the card room, pulled out every chart, and started changing things to look perfect on paper. Then I saw that hospital being announced as 1st place on national TV and I just thought, “Wait… what?!”

The truth is, these rankings often reflect paperwork and appearances more than what patients actually experience.

10/03/2026
03/02/2026

ጤና ባለሙያው እየሞከረ እና እየመከረ ነው!
Cc Ministry of Health,Ethiopia
Office of the Prime Minister-Ethiopia
የወጡ መመሪያዎች ተፈፃሚ ይሁኑ። ያልተመለሱ ጥያቄዎች ይመለሱ ✊ የኢትዮጲያ ህዝብ ጦርነት በቃው!

03/02/2026

Who is the voice for health professionals in today’s parliament?
Dr Mohammed Shikur is the owner, founder, and CEO of Amin General Hospital. He is an internist and gastroenterologist who received his medical training at Addis Ababa University and Cairo University. He is widely recognized for his strong commitment and valuable contributions to the community.
We extend our sincere appreciation to Dr Mohammed.
It is inspiring to see physicians representing and advocating for health professionals in parliament. This kind of leadership is exactly what the healthcare sector needs.
When knowledgeable voices rise to express professional concerns with confidence, it gives real hope for a better future

በቅርቡ ህክምና ማጥናት ላያስፈልግ ይችላል - ኤሎን መስክአሜሪካዊው ቢሊየነር  ኤሎን መስክ፣ በቅርቡ  ዶክተር ለመሆን ህክምና ማጥናት ላያስፈልግ እንደሚችል  መግለጹን  ተከትሎ፣ በወደፊቱ የ...
23/01/2026

በቅርቡ ህክምና ማጥናት ላያስፈልግ ይችላል - ኤሎን መስክ

አሜሪካዊው ቢሊየነር ኤሎን መስክ፣ በቅርቡ ዶክተር ለመሆን ህክምና ማጥናት ላያስፈልግ እንደሚችል መግለጹን ተከትሎ፣ በወደፊቱ የህክምና ዕጣፈንታ ላይ አዲስ ክርክር አስነስቷል።

ማስክ ከፒተር ዲያማንዲስ ጋር በMoonshots ፖድካስት ላይ ሲናገር፤ በሦስት ዓመት ውስጥ በኤአይ የሚታገዙ ሮቦቶች የሰው ቀዶ ጥገና ሃኪሞችን ሊልቁ እንደሚችሉ ሞግቷል፡፡

ሃኪሞችን ለማሰልጠን በጣም ረጅም ጊዜ እንደሚፈጅ የጠቆመው ቢሊየነሩ፤ በዚያ ላይ የስራ ሰአታቸው ውስን ነው ብለዋል፡፡ የሰው ሃኪሞች ስህተት ሊሰሩ እንደሚችሉም ጠቁሟል፡፡

"ምን ያህል ታላላቅ የቀዶ ጥገና ሐኪሞች አሉ? ያን ያህል አይደሉም" ብሏል መስክ፡፡

ሰዎች አሁንም የሕክምና ትምህርት ቤት መሄድ አለባቸው ወይ ተብሎ ለተጠየቀው ሲመልስም፤ “አዎ፣ ከንቱ ነው” ሲል መልሷል፡፡
©addisadmas
እርስዎስ ምን ይላሉ በዚህ ዙርያ?
ጤና ይስጠን-Tena Yisten

🎉
06/12/2025

🎉

16/11/2025

#ሰበር — የጂንካ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ከስራ ተባረሩ !

መርበርግ የተባለ አደገኛ ቫይረስ የ6 ሰዎችን ህይወት በቀጠፈ ማግስት የሆስፒታሉ ሜዲካል የዳይሬክሩ መባረር አነጋጋሪ ሆኗል።

ሜዲካል ዳይሬክተሩ የተባረሩትም አለማቀፉ ሚድያ በቫይረሱ የሞቱ ዜጎች መኖራቸውን በማረጋገጣቸው እንደሆነም የውስጥ ምንጮች ነግረውናል።

ከሰሞኑ ምንነቱ ባልታወቀ በሽታ የ 6 ሰዎች ህልፈትን ተከትሎ የማህበራዊ ሚድያዎች ትኩረት በጂንካ ሆስፒታል ላይ አነጣጥሯል።

ቫይራል ሄሞሬጅክ ፌቨር የተሰኘው አደገኛ የቫይረሶች ቡድን ተከተሰተ መባሉን ተከትሎ በተደረገ የሟቾች የደም ናሙና ምርመራ ውጤት ማርበርግ የተሰኘ አደገኛ ወረርሽኝ መከሰቱ ተሰምቷል።

የሟቾቹ የናሙና ምርመራ ውጤትን መነሻ በማድረግ በፌደራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና በኢትዮጽያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት በኩል የወረርሽኙን ክስተት ያረጋገጡ መግለጫዎችም በማህበራዊ ሚድያ ገጾቻቸው ያሰራጩ ሲሆን አለም ዓቀፉ የጤና ድርጅትም አፋጣኝ የገንዘብ፣ የሙያተኛና የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉም ይፋ ማድረጉ ይታወሳል።

ይህንን ተከትሎ ከጀርመን ድምጽ ራድዮ ጣቢያ ዶቼቬሌ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የጂንካ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ቢኒያም አስራት የወረርሽኙ ክስተት ሞት ማስከተሉን ያረጋገጡበትን ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ 4 ታካሚዎችና የህክምና እርዳታ ያደረጉላቸው 2 ሀኪሞች፤ 1 ዶክተርና 1 ነርስ ህይወት ማለፍን ያረጋገጡት ሜዲካል ዳይሬክተሩ የሟቾችን ቁጥር መግለጻቸው ተከትሎም ሜዲካል ዳይሬክተሩ ከስራቸው መባረራቸው ተሰምቷል።

የቀረበው ውንጀላም ለአለማቀፉ የሚድያ ተቋም DW የተከሰተውን ሃቅ ያረጋገጠ መረጃ ሰጥተሃል በሚል ውንጀላ መሆኑንም ከሆስፒታሉ የመረጃ ምንጮች ለማረጋገጥ ችለናል።

የፌደራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት በሰጡት በመግለጫ በሆስፒታሉ በቫይረሱ የተጠረጠሩ ሰዎችን እንጂ የሞቱ ሰዎች መኖራቸውን ያልገለጹ ቢሆንም ዳይሬክተሩ ይህንኑ ይፉ ማድረጋቸውን ተከተሎ ከስራ መታገዳቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ደርሷቸዋል።

የተከሰተው ቫይረስ እጅግ አደገኛና ገዳይ መሆኑ እየተገለጸ የሟቾችን ቁጥር መደበቅ ለምን እንደተፈለገ የታወቀ ነገር ባይኖርም ሃቁን ባለመደበቃቸው የተወነጀሉት ሜዲካል ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቢኒያም አስራት አደገኛ ዛቻና የእስር ማስፈራሪያ እየደረሱባቸው መሆኑንም ለማረጋገጥ ችለናል።

ከስራ የተባረሩበት ደብዳቤ የደረሳቸው ሜዲካል ዳይሬክተሩን ለማነጋገር ተደጋጋሚ ጥረት ብናደርግም በዚህ ጉዳይ ምንም አስተያዬት ለማንም መስጠት እንደማይፈልጉ በመግለጽ ስልካቸውን ዘግተዋል።

ሆኖም ግን የእገዳ ደብዳቤው በክልሉ የጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ ጫና አድራጊነት የተጻፈባቸው መሆኑን ከሆስፒታሉ የውስጥ ምንጮች ለማረጋገጥ ችለናል።

በስራው ታታሪና ትጉህ የሆነው የጂንካው ተወላጅ ዶ/ር ቢኒያም ሆስፒታሉን ለማሻሻል እየተጋ ቢሆንም በተደጋጋሚ ጫና ውስጥ መቆየቱን ጠቁመው እውነተኛ መረጃ መስጠት ኃላፊነቱን በመወጣቱ ሊመሰገን ሲገባው ከስራ መታገዱ ተገቢ አይደለም ብለዋል።

በአለማቀፉ የጤና ተቋም ተረጋግጦ በመንግስት መግለጫ በተሰጠበት ጉዳይ መረጃ ምንም አይነት ክልከላ በሌለበት፤ ዶ/ሩ መባረር እውነታን ለመደበቅ የሚፈልግ አካል ሴራ ሊሆን ይችላል የሚሉት ምንጮቹ ሃቀኛ መረጃ እንዲሸፈን የተፈለገበት ምክንያት ግን ምን ሊሆን እንደሚችል አናቅም ብለዋል።

አስደንጋጭ እልቂት ያስከትላል የሚለው የቫይረሱ ስጋት ባጠላበት ጂንካ ሆስፒታል ከሟቾች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው በርካታ ዜጎች በተጠርጣሪነት ተለይተው በሚገኙበት በዚህ ወቅት

በከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ የሚገኘው ነዋሪ ከመንግስት የሚሰጡ መመሪያዎችና የጥንቃቄ መልዕክት እየተጠባበቀ ቢሆንም የክልሉ ጤና ቢሮና የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት መገኛ በሆነው ጅንካ ክስተቱን በተመለከተ የክልሉ ልሳን የሆነው የደቡብ ሬድዮና ቴሌቭዥን ድርጅትም፤ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥንንም ሆነ ሌሎች ሚድያዎች ዝምታን መምረጣቸው አነጋጋሪ ሆኗል።”

💥 ዶ/ር ቢኒያም አስራት በአስቸኳይ ወደ ስራው እንዲመለስ እንጠይቃለን! እውነት መናገር መረጃ ለሚዲያ መስጠት ወንጀል አይደለም። የሚመለከታቸው አለም አቀፍ ተቋማት ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ እንጠይቃለን። EHPM ለአለም አቀፍ ተቋማት እና ኤምባሲዎች በቀጣይ ቀናት ደብዳቤ የሚያስገባ ይሆናል።

በጂንካ ያላቹ ጤና ባለሞያዎች ስለ ዶ/ር ቢኒያም እና በMVD ምክንያት ስለሞቱት 6 ሰዎች የተብራራ መረጃ በ በአስቸኳይ ላኩልን!

13/11/2025

.World Health Organization (WHO) is working closely with Ministry of Health,Ethiopia , the Ethiopia Public Health Institute and regional health authorities as part of the rapid response to a suspected outbreak of a viral haemorrhagic fever (VHF) in the Southern Ethiopian Region.

8 people, including health workers, have reportedly been infected.

WHO has deployed experts to the affected towns, along with medicines and other materials to support care for people in need, and personal protective equipment for health workers.

WHO will also be supporting contact tracing in affected communities. Samples have been sent for testing. Further details are expected soon.

I have released US$300,000 from the WHO Contingency Fund for Emergencies to provide immediate support.

WHO’s offices in Ethiopia and South Sudan are collaborating closely to prevent potential cross-border transmission. WHO is ready to scale up support, as and when needed.

I commend Ethiopian health authorities for their timely sharing of information and quick response and offer WHO’s full support.

https://www.afro.who.int/news/ethiopia-reports-suspected-viral-haemorrhagic-fever-outbreak

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጤና ይስጠን-Tena Yisten posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram