Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS

Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS, 9. 046572, 38. 728670, Addis Ababa.

Ethiopian Pharmaceutical Supply service , EPSS
, procure ,manage and distribute RDF & Heath Programme Products for governmental health facilities to supply quality assured essential pharmaceutical with affordable prices & a sustainable manner in Eth

23/12/2025
በጅጅጋ ቅርንጫፍ እየተገነባ የሚገኘው የመድኃኒት ማከማቻ መጋዘን ግንባታ 50% መድረሱ በአገልግሎቱ የበላይ አመራር ጉብኝት ወቅት ተገለፀ፡፡--------------------------------...
23/12/2025

በጅጅጋ ቅርንጫፍ እየተገነባ የሚገኘው የመድኃኒት ማከማቻ መጋዘን ግንባታ 50% መድረሱ በአገልግሎቱ የበላይ አመራር ጉብኝት ወቅት ተገለፀ፡፡
--------------------------------------
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጅጅጋ ቅርንጫፍ በ1.5 ሄክታር መሬት ላይ ለመድኃኒትና የህክምና ግብአት ማከማቻ፣ ለኮልድ ሩም፣ ለቢሮ አገልግሎት፣ ለካፍቴሪያ እና ለአጠቃላይ የስብሰባ አዳራሽ ግንባታ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡

የአገልግሎቱ የጤና ስርአት ማጠናከርና የፋይናንስ አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ በላቸው በሳይቱ ተገኝተው ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ደረጃ፣ የስራ ጥራት፣ የጊዜ ሰሌዳ እና የደህንነት አፈፃፀም ከቅርንጫፉ አመራሮች ጋር በጥልቀት ተመልክተዋል፡፡

ፕሮጀክቱ በተያዘው እቅድ መሠረት እየተካሄደ መሆኑ ተገልጾ፣ ቀሪ 50% ስራዎች በተያዘው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት እንዲጠናቀቁ አሳስበዋል ፡፡

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ፈዋሽነታቸውና ደህንነታቸው የተረጋገጡ መድኃኒቶችንና የህክምና ግብአቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እና ቀጣይነት ለማቅረብ በማስቻል ለማህበረሰቡ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡

ሀላፊው በአገልግሎቱ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ዙሪያም በቅርንጫፍ በመገኘት የስራ መመሪያ ሠጥተዋል።


በበፀሎት የማነ

ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት አርባምንጭ ቅርንጫፍ ጎበኙ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬህይ...
23/12/2025

ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት አርባምንጭ ቅርንጫፍ ጎበኙ

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ፣ የጋሞ ዞን ምክትል አስተዳዳር እና ለሎች ከፍተኛ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት አርባ ምንጭ ቅርንጫፍ አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ ጎበኙ ።

በጉብኝቱ ላይ ውል የተገባለት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓት ተግባራዊ ከሆነ በኃላ መሻሻሎች የመጡ ሲሆን በቀጣይነት ያሉ ቀሪ ስራዎች ላይ በጋራ መሰራት እንዳለበት ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ ያሰሰቡ ሲሆን ፤ በተለይ የማርበርግ ወረረሽኝ ላይ እየተደረገ ላለው ፈጣን ምላሽ የሚበረታታ መሆኑን አንስተዋል ።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት አርባምንጭ ቅርንጫፍ ውስጥ ያለውን የስራ ፍሰት ፣ የህክምና ግብዓቶች እንዴት እየተሰራጨ እንደሚገኝ ፣ ውል የተገባለት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓት አፈፃፀም ፣ የማርበርግ ወረረሽኝ ላይ እየተደረገ ላለው ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን እነዚህንና ሌሎች መሰል ጉዳዮችን የቅርንጫፋ ስራ አስኪያጅ አቶ አንድነት አሰፋ በዝርዝር አስረድተዋል ።

በመጨረሻም የማርበርግ ወረረሽኝ ላይ እየተደረገ ላለው ፈጣን ምላሽ ዕውቅና የሰጡን ሲሆን ይህም ምላሽ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም አሳስበዋል ፡፡

የሐዘን መግለጫ፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጅማ ቅርንጫፍ ባልደረባችን የነበሩት ወ/ሮ የትምወርቅ ጌታቸው በድንገተኛ ህመም ከዚህ አለም በሞት በመለየታቸው የተሰማንን ት...
23/12/2025

የሐዘን መግለጫ
፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጅማ ቅርንጫፍ ባልደረባችን የነበሩት ወ/ሮ የትምወርቅ ጌታቸው በድንገተኛ ህመም ከዚህ አለም በሞት በመለየታቸው የተሰማንን ትልቅ ሀዘን ለመግለፅ እንወዳለን።

አገልግሎቱ ለቤተሰቦቻቸው እና ለስራ ባልደረቦቻቸው መፅናናትን ይመኛል።

የተቀናጀ የመረጃ አያያዝ ስርዓት የተሰናሰለ (Cross functional) እንዲሆን የሚያስችል የመማማሪያ መድረክ ተካሄደ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨አገልግሎቱ ዘመናዊ አሰራርን ለመዘርጋት የተቀናጀ የመረ...
22/12/2025

የተቀናጀ የመረጃ አያያዝ ስርዓት የተሰናሰለ (Cross functional) እንዲሆን የሚያስችል የመማማሪያ መድረክ ተካሄደ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
አገልግሎቱ ዘመናዊ አሰራርን ለመዘርጋት የተቀናጀ የመረጃ አያያዝ ስርዓት (ERP) ሲስተምን ተግባራዊ ያደረገ ሲሆን የፋይናንስ ፤ የሰዉ ሃይል አስተዳደር ፤ የግብዓት ክምችትና ስርጭት ሂደት እንዲሁም አጠቃላይ የአቅርቦት ሰንሰለት ሂደቱ የተሳለጠ እንዲሆን የሚያስችል የመማማሪያ መድረክ በአዳማ ከተማ እንደተፈጠረ የERP ፕሮጀክት ቢሮ ማናጀር ወ/ሮ መንፈሴ ታደሰ ገልፀዋል።

በሲስተም ትግበራ ወቅት የሚገጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ፤ የተቋሙ ዲፓርትመንቶች በተናበበ መልኩ ሲስተሙን እንዲተገብሩና በስራ ወቅት ለሚገጥሙ ችግሮች የመፍትሄ አሰራሮች እንዲቀረፁ ለማስቻል በርቀት ዉይይት(Virtual meeting) እና በአካል በመገናኘት በየወቅቱ ስራዎች እየተገመገሙ እንደሆነ የፕሮጀክቱ ማናጀር ጠቁመዉ ከፕሮሰስ ሻንፒዎኖች እስከ ድጋፍ ሰጪዎች(first line) አልፎም ባለሞያዎች (end user) የእዉቀት ሽግግር እያደረጉ መሆኑን አስገንዝበዋል።

አቶ አቤል ጌቱ የEWM ፕሮሰስ ሻንፒዎን ሲሆን በ4ቱ ቀን ቆይታ ከሁሉም ቅርንጫፍ የተገኙ ERP/SAP ላይ የሚሰሩ ባለሞያዎች የክፍላቸዉን እንዲሁም ከሌሎች ክፍሎች ጋር በሚያገናኟቸዉ ስራዎች (cross functional ) ዙሪያ ዉጤታማ የሚባል የልምድ ልዉዉጥ ጊዜ እንደነበራቸዉ ገልፀዋል።

በስራ ላይ የሚገጥሙ ችግሮች ተለይተዉ መፍትሄ እንዲያገኝና አንዱ ከሌላዉ ትምህርት ያገኘበት መድረክ መሆኑን በመቀሌ ቅርንጫፍ የሰዉ ሃይል ባለሞያ አቶ ሚካኤል መኮንን ተናግረዋል።

በተጨማሪም የማኑዋል ስራዎች ወደ ሲስተም ሲመጡ ወጥ የሆነ አሰራር እንዲኖር ፤ ስህተቶች እንዲቀንሱ ፤ የመፍትሄ ሀሳቦች እንዲንሸራሸሩ ፤ መደጋገፍና ተግባራትን መከለስ እንዲቻል ሁሉም የስራ ክፍል በተቀራረበ መልኩ ተቋማዊ ራዕይን ለማሳካት አቅም የፈጠረ መድረክ እንደሆነ ከ40 ምንጭ ቅርንጫፍ የፋይናንስ ከፍተኛ ባለሞያ የሆኑት አቶ አፈወርቅ ታደሰ አስረድተዋል።

በመጨረሻም ERP/SAP ሞጁሎች በተሻለ መልኩ በየክፍሉ ተቀናጅተዉ ዉጤታማ እንዲሆኑ አዎንታዊ አስተዋፆ እያበረከቱ ላሉ የአገልግሎቱ ባለሞያዎች የእዉቅና መርሃግብር ተካሂዷል። የፕሮጀክቱ ማናጀርና የERP ቢሮ አባላትም የላቀ ምስጋና አቅርበዋል።

#ማገልገል ክብር ነዉ
አማኑኤል ወርቃየሁ

EPSS Deputy Director General Tariku Belachew Visited Kebridehar Branch፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨Yesterday, December 19, 2025 (Tahsas ...
20/12/2025

EPSS Deputy Director General Tariku Belachew Visited Kebridehar Branch
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

Yesterday, December 19, 2025 (Tahsas 10, 2018 EC), the Deputy Director General of the Ethiopian Pharmaceutical Supply Service (EPSS), Mr. Tariku Belachew , conducted a working visit to the medical supplies warehouse at the Kebridehar branch.

The visit focused on key areas aimed at further enhancing the quality of service delivery at the branch.

Mr. Tariku was accompanied by Mrs. Asnakech Lechisa, Manager of the Dire Dawa branch, and Mr. Mohammed Mahmoud, Manager of the Jigjiga branch.

✅Key Focus Areas of the Visit:

✅Performance Review: Discussions were held regarding the branch's operational performance and strengthening efforts.

✅Field Inspection: A physical inspection of offices, cold room facilities, and main warehouses was conducted to assess the current state of infrastructure.

✅Critical Issues Identified During the Visit:
✅Cold Room Floor Maintenance:
The urgent need for epoxy flooring to maintain hygiene and quality standards.

✅Climate Control Systems:
Installation of modern air conditioning equipment to guarantee the safety and efficacy of vaccines.

✅Flood Prevention and Expansion: Implementing measures to mitigate flood risks from the Fafan River and expanding the warehouse compound.

✅Staff Welfare: The necessity of providing transport services (a bus) for employees.

The Deputy Director General emphasized that maintaining domestic and international cold chain standards is critical for the integrity of pharmaceuticals. He further reaffirmed EPSS's commitment to strengthening the Kebridehar branch and addressing identified infrastructure gaps through the head office.

" to serve.
EPSS

📸የኢ.መ.አ.አ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ በላቸው በከብሪደሃር ቅርንጫፍ የስራ ጉብኝት አደረጉ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ትናንት፣ ታህሳስ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ፣ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅ...
20/12/2025

📸የኢ.መ.አ.አ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ በላቸው በከብሪደሃር ቅርንጫፍ የስራ ጉብኝት አደረጉ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ትናንት፣ ታህሳስ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ፣ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (EPSS) ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ በላቸው፣ የከብሪደሃር ቅርንጫፍ የህክምና ግብአቶች ማከማቻ መጋዘንን ጎብኝተዋል።

ጉብኝቱ የቅርንጫፉን አገልግሎት ጥራት ይበልጥ ለማሻሻል የሚያስችሉ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር።

በጉብኝቱ ወቅት የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ አስናቀች ለቺሳ እና የጅጅጋ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ መሐመድ ማህሙድ ተገኝተዋል ።

🚀የጉብኝቱ ዋና ትኩረቶች:

የሥራ አፈጻጸም ግምገማ: የቅርንጫፉን የስራ አፈጻጸም እና የማጠናከሪያ ስራዎችን በተመለከተ ውይይት ተደርጓል።

የመስክ ምልከታ: ቢሮዎች፣ የቀዝቃዛ ክፍል (Cold Room) እና ዋና መጋዘኖች ተጎብኝተው የመሰረተ ልማት ያሉበት አሁናዊ ሁኔታ ታይተዋል።

በጉብኝቱ የተለዩ ወሳኝ ነጥቦች:

🚀የቀዝቃዛ ክፍል ወለል ጥገና:
🚀ለንጽህና እና ጥራት ሲባል የኤፖክሲ ወለል አስፈላጊነት

🚀የአየር ማቀዝቀዣ ስርዓት: የክትባቶችን ደህንነት ለመጠበቅ ዘመናዊ የአየር ማቀዝቀዣ መሳሪያዎች

🚀የጎርፍ መከላከልና ጥገና: የፋፋን ወንዝ የጎርፍ ስጋትን መከላከልና የመጋዘን ግቢውን ማስፋፋት

🚀የሰራተኞች ደህንነት: ለሰራተኞች የትራንስፖርት አገልግሎት (አውቶቡስ) አስፈላጊነት

የምክትል ዋና ዳይሬክተሩ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ የቀዝቃዛ ሰንሰለት ደረጃዎችን መጠበቅ ለመድኃኒቶች ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል።

EPSS በከብሪደሃር የሚሰጠውን አገልግሎት ይበልጥ ለማጠናከርና የተለዩ የመሰረተ ልማት ክፍተቶችን ዋና በመስራሪያ ቤቱ በኩል ለመሙላት ቁርጠኛ መሆኑንም ገልጸዋል።

#ማገልገል ክብር ነው።

EPSS Inaugurates Renovated Warehouses Supported by Gates Foundation and UNICEF፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨The Ethiopian Pharmaceutica...
18/12/2025

EPSS Inaugurates Renovated Warehouses Supported by Gates Foundation and UNICEF
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
The Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service (EPSS) has officially inaugurated renovated warehouses aimed at improving warehouse management and operational efficiency. The renovation project was funded by the Bill & Melinda Gates Foundation and coordinated by UNICEF.

During the inauguration, the Director General of EPSS, Dr. Abdulkadir Gelgelo, stated that the renovations were carried out at Central Warehouse Main 4, as well as the Dessie, Dire Dawa, Jimma, and Semera branches. He noted that to bring these facilities up to international standards, the project included:

✅ Installation of modern canopies,

✅ Upgrading of loading docks,

✅ Application of durable epoxy flooring,

✅ Full renovation of electrical systems.

Dr. Abdulkadir emphasized that renovating centers where essential medicines and vaccines are stored plays a vital role in ensuring their safety and integrity. He added that this milestone accelerates EPSS’s journey toward creating a robust, efficient, and equitable supply chain, ensuring quality medicines reach users on time. He also extended his heartfelt gratitude for the support provided.

The Country Director of the Gates Foundation in Ethiopia, Ms. Sushna, remarked that establishing standard storage facilities enables the service to deliver medical supplies quickly, reduce wastage, and maintain a timely supply chain for health facilities.

Maniko Kagoshima, UNICEF Representative, highlighted that building a strong supply chain is essential to meet the demand for vaccines and basic medicines. Strengthening and modernizing storage capacity allows for a more rapid response to health needs.

The event concluded with a site visit, where officials toured the renovated sections of the warehouse.

to serve

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በጌትስ ፋውንዴሽን እና በዩኒሴፍ ድጋፍ የታደሱ መጋዘኖችን አስመረቀ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የመጋዘን አስተዳደርን...
18/12/2025

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በጌትስ ፋውንዴሽን እና በዩኒሴፍ ድጋፍ የታደሱ መጋዘኖችን አስመረቀ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የመጋዘን አስተዳደርንና ቅልጥፍናን ለማሻሻል በጌትስ ፋውንዴሽን የገንዘብ ድጋፍ እና በዩኒሴፍ አስተባባሪነት የታደሱ መጋዘኖችን አስመርቋል።
እድሳቱ በዋና መጋዘን 4፣ በደሴ፣ በድሬዳዋ፣ በጅማ እና በሰመራ ቅርንጫፎች የሚገኙ መጋዘኖች ላይ መከናወኑን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ ገልፀዋል።

መጋዘኖቹን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ለማድረግም፦
✅ የመሸፈኛ ጣራዎች (Canopies)፣
✅ የመጫኛ መድረኮች ማሻሻያ፣
✅ ጠንካራ የኢፖክሲ (Epoxy) ወለል እና
✅ የኤሌክትሪክ መስመሮች እድሳት መከናወኑን ተናግረዋል።

ዶ/ር አብዱልቃድር አክለውም ለጤና ዋስትና የሆኑ መድኃኒቶች እና ክትባቶች የሚከማቹበት ማዕከላት መታደስ ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲቀመጡ ጉልህ ሚና እንዳለው ገልጸው፤ አገልግሎቱ ጠንካራ፣ ቀልጣፋ እና ፍትሀዊ የአቅርቦት ሰንሰለት ለመፍጠር የሚያደርገውን ጉዞ እንደሚያፋጥነው ገልፀዋል። ለተደረገው ድጋፍም ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል።

የጌትስ ፋውንዴሽን በኢትዮጵያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሱሽና በበኩላቸው፤ ደረጃውን የጠበቀ ማከማቻ መኖሩ አገልግሎቱ የህክምና ግብአቶችን በፍጥነት እንዲያቀርብ፣ ብክነት እንዲቀንስ እና ለጤና ተቋማት ወቅታዊ የአቅርቦት ሰንሰለት እንዲኖረው ያደርጋል ብለዋል።

የክትባት እና መሰረታዊ መድኃኒቶችን ፍላጎት ለማሟላት ጠንካራ የአቅርቦት ሰንሰለት መፍጠር ያስፈልጋል ያሉት የዩኒሴፍ ተወካይ ማኒኮ ካጎሺማ፤ የማከማቻ አቅምን ማጠናከር እና ማዘመን ለድንገተኛ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ያስችላል ሲሉ ተናግረዋል።

በመጨረሻም አመራሮቹ በመጋዘኑ የተከናወኑ እድሳቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

!
ሰላም ይደግ!

EPSS Held an  -Corruption Movement Forum.፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨The Ethiopian Pharmaceutical Supply Service celebrated the 22nd   A...
17/12/2025

EPSS Held an -Corruption Movement Forum.
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
The Ethiopian Pharmaceutical Supply Service celebrated the 22nd Anti-Corruption Day today with a movement forum held under the theme: " for the Generation, for the Institution."

In a message delivered at the forum, the Deputy Director General of the Service, Mr. Solomon Nigussie, described corruption as a "cancer" that stunts national growth and diminishes public benefits. He urged leaders and employees to stand together and fight this enemy of the nation.

Noting that the Service is an institution entrusted with the great responsibility of protecting public health, Mr. Solomon stated that to prevent malpractice, the institution is implementing technology-backed systems and operating based on the principles of integrity, transparency, and accountability.

In his closing remarks, the Deputy Director General, Mr. Aknaw Kawza, expressed the institutional commitment to reducing potential sources of corruption within the pharmaceutical supply chain to "Zero." He emphasized the importance of focusing on mindset changes to prevent corruption effectively.

The Director of the Service’s Ethics and ani corruption Monitoring Directorate Director , Mr. Ashenafi Erena, presented a report regarding the asset registration process of the institution. According to the report:

78% of the asset registration for employees at the head office and all branches has been completed so far.
A goal has been set to reach 100% registration within the coming week.

The participants of the movement forum concluded the event by taking an Oath to fight corruption collectively and to prioritize the public's access to medicine.

to serve

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የፀረ-ሙስና ንቅናቄ መድረክ አካሄደ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት 22ኛውን ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን "ትውልድን በ...
17/12/2025

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የፀረ-ሙስና ንቅናቄ መድረክ አካሄደ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት 22ኛውን ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን "ትውልድን በሥነ-ምግባር፣ ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል በዛሬው ዕለት በንቅናቄ መድረክ አክብሯል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ንጉሴ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሙስና የሀገርን ዕድገት የሚያኮሳምንና የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያመናምን "ካንሰር" መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም አመራሮችና ሠራተኞች ይህንን የሀገር ጠላት በጋራ ሊታገሉት እንደሚገባ አሳስበዋል።

አገልግሎቱ የሕዝብን ጤና የመጠበቅ ትልቅ ኃላፊነት ያለበት ተቋም መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሰለሞን፣ ብልሹ አሠራርን ለመከላከል ተቋሙ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሠራር እየዘረጋ እንደሚገኝና ታማኝነትን፣ ግልጸኝነትንና ተጠያቂነትን መርህ አድርጎ እንደሚሠራ አስታውቀዋል።

በመጨረሻም የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አቅናው ካውዛ በበኩላቸው፣ በመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለቱ ውስጥ ሊፈጠሩ የሚችሉ የሙስና ምንጮችን ወደ "ዜሮ" ለማውረድ ተቋማዊ ቁርጠኝነት መኖሩን ገልጸዋል። ሙስናን ለመከላከልም በአመለካከት ለውጥ ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

የአገልግሎቱ የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ዳይሬክተር አቶ አሸናፊ ኢረና የተቋሙን የሀብት ምዝገባ ሂደት በተመለከተ ሪፖርት አቅርበዋል። በሪፖርታቸውም፦

እስካሁን በአገልግሎቱ ዋና መሥሪያ ቤትና በሁሉም ቅርንጫፎች የሚገኙ ሠራተኞች 78 በመቶ የሚሆነው የሀብት ምዝገባ ተከናውኗል።

በቀጣይ አንድ ሳምንት ውስጥ ምዝገባውን 100 በመቶ ለማድረስ ግብ ተቀምጦ እየተሠራ ይገኛል።

የንቅናቄ መድረኩ ተሳታፊዎች ሙስናን በጋራ ለመታገልና የሕዝብን የመድኃኒት አቅርቦት ቅድሚያ ለመስጠት ቃለ-መሐላ በመፈጸም ተጠናቋል።

!
ሠላም ይደግ

Address

9. 046572, 38. 728670
Addis Ababa

Telephone

+251112763276

Website

https://t.me/epsaethiopia2012

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram