Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS

Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS, 9. 046572, 38. 728670, Addis Ababa.

Ethiopian Pharmaceutical Supply service , EPSS
, procure ,manage and distribute RDF & Heath Programme Products for governmental health facilities to supply quality assured essential pharmaceutical with affordable prices & a sustainable manner in Eth

እንኳን ለ2018 ዓ.ም የመስቀል በዓል በሰላም አደረሳችሁ! !
26/09/2025

እንኳን ለ2018 ዓ.ም የመስቀል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
!

25/09/2025
https://youtu.be/diuzAYhWg7w?si=qKB_9OPCWHGUGWPk
22/09/2025

https://youtu.be/diuzAYhWg7w?si=qKB_9OPCWHGUGWPk

አገልግሎቱ የአቅርቦት ሰንሰለቱን በዲጅታል ስርአት የታገዘ ለማድረግ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ያደረገው የመግባቢያ ሰነድ ፊርማ

ህብረተሰባችንን በታማኝነት እና በቅልጥፍና ለማገልገል ዲጅታል ስርአት መተግበር ትልቅ ሚና አለዉ፡-የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ...
19/09/2025

ህብረተሰባችንን በታማኝነት እና በቅልጥፍና ለማገልገል ዲጅታል ስርአት መተግበር ትልቅ ሚና አለዉ፡-የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የአቅርቦት ሰንሰለቱን በዲጅታል የታገዘ ለማድረግ (Smart Digital Health Supply Chain) የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ፣ የጤና ሚኒስቴር ድኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ ፣ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ ፣ የኢትዮቴሌኮም ም/ስራ አስፈፃሚ አቶ ታሪኩ ደምሴ ፣ የኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ አመራሮች ፣ የአገልግሎቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ማኔጅመንት አባላት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች በተገኙበት ከኢትዮቴሌኮም ጋር የመግባቢያ ሰነድ በስካይ ላይት ሆቴል ተፈራርሟል፡፡

ህብረተሰባችንን በታማኝነት እና በቅልጥፍና ለማገልገል ዲጅታል ስርአት መተግበር ትልቅ ሚና አለዉ ሲሉ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ተናግረዉ ፤ ዲጅታል ስርአቱን በሁሉም ጤና ተቋማት ላይ በማዉረድ ዉጤቱን ሙሉ ማድረግ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡

አክለዉም ግዙፉን ፕሮጀክት ሀገር በቀል ተቋም በሆነዉ ኢትዮቴሌኮም የሚከናወን በመሆኑ ትግበራዉ አስተማማኝ እንዲሆን እንደሚያስችል አንስተዉ ፤ ስርአቱን በፍጥነት ወደ ትግበራ በማስገባት ዉጤቱን ለህብረተሰባችን በምንሰጠዉ አገልግሎት እንድናየዉ ሲሉ አደራ ብለዋል፡፡

የአገልግሎቱ አሰራር ስርአት ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ በመተግበር የማይቋረጥ ሂደት ውስጥ ከገባ መቆየቱን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አንስተው ፤ ፈጣን አቅርቦት ሰንሰለት ካምፓስ (smart supply chain campus) ቅንጅታዊ አሰራርን በመፍጠር የተሳለጠ የአቅርቦት ስርአት እንዲኖር የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል ሲሉ ተናግረዋል።

ቴክኖሎጂን በመጠቀም እንደ ተቋም ከተቀመጡ ስትራቴጂክ ትልሞች በማሳካት ሂደት ዉስጥ ወጪ ቆጣቢ ፣ ጥራቱ የተረጋገጠ እና ከሰዎች አሉታዊ ተፅዕኖ የፀዳ ዉሳኔ ሰጭነትን ለማስፈን እንደሚያስችል ዶ/ር አብዱልቃድር ገልፀዉ ፤ ስርአቱ ያለ ብቁ የሰው ሃይል ውጤት ላይ መድረስ የማይቻል በመሆኑ የተደራጀ እና የበቃ የሰው ሀይል ስምሪቱም ከሲስተም ትግበራው ባልተናነሰ መልኩ የሚሰራበት መሆኑን ጠቁመዋል።

ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማሳለጥ እና ለህይወት አድን እርምጃዎች መሰረቱ ዲጅታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ በመሆኑ ሁላችንም የድርሻችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል።

ከሚተገበሩ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች መካከል በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ CCTV ፣ ተሽከርካሪዎችን ለመቆጣጠር የሚያስችል ዘመናዊ GPS ፣ ፈጣን የቁጥጥር ስርአት (Smart Access Control System )፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የቻርጂንግ ስርአት ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ያቀፈ መሆኑን በፊርማ ስርአቱ ተገልጿል።

#ማገልገል ክብር ነዉ
ሰላም ይደግ

የአገልግሎቱ ባህር ዳር ቅርንጫፍ የወጣቶች እና ስፖርት ቡድን የትምህርት ቁሳቁስ እና የገንዘብ ድጋፍ አደረገ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ...
17/09/2025

የአገልግሎቱ ባህር ዳር ቅርንጫፍ የወጣቶች እና ስፖርት ቡድን የትምህርት ቁሳቁስ እና የገንዘብ ድጋፍ አደረገ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ባህር ዳር ቅርንጫፍ የወጣቶች እና ስፖርት ቡድን የ2017 ዓ.ም የነበረውን እንቅስቃሴ የገመገመ ሲሆን ፤ በበጀት ዓመቱ የሰራተኛውን ጤና ከመጠበቅ እና ብቁ ሰራተኛ ከመፍጠር አንጻር ስፖርት የሚሰጠው ጠቀሜታ ከፍተኛ በመሆኑ ለቡድኑ መጠናከር መስሪያ ቤቱ እያበረከተ ያለው ድጋፍ ከፍተኛ እንደነበር ተገልጷል፡፡

በግምገማዉ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታ እና የበጀት እጥረት ቡድኑ ከዚህ በላይ እንዳይንቀሳቀስ እንቅፋት እንደሆነ የተነሳ ሲሆን ፤ በእለቱ የስፖርት ቡድኑ ከአባላቱ ከሚሰበስበው መዋጮ ወላጆቻቸውን በሞት ላጡ የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች ልጆች እና ለዝቅተኛ የማህበረሰብ ክፍል ልጆች የትምህርት ቁሳቁስ (ዩኒፎርም, ቦርሳ ,ደብተር, እርሳስ,እስክእረቢቶ) እና የገንዘብ ድጋፍ በማድረገ ማህበራዊ ግዴታውን ተወጥቷል፡፡

ለተደረገው ድጋፍ ወላጆች እና ማኔጅመንት አባላት አመስግነው በቀጣይም ቡድኑን ለማጠናከር አስፈላጊዉን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል::

#ማገልገል ክብር ነዉ
ሰላም ይደግ

⩩ ቅርንጫፉ በ2017 በጀት አመት የላቀ የስራ አፈፃፀም ላሳዩ  ሰራተኞች እውቅና ሰጠ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ጳጉሜ 3 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ...
17/09/2025

⩩ ቅርንጫፉ በ2017 በጀት አመት የላቀ የስራ አፈፃፀም ላሳዩ ሰራተኞች እውቅና ሰጠ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ጳጉሜ 3 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት አዳማ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ አስረስ ተሾመ፣የማኔጅመንት አባላት እንዲሁም መላው የቅርንጫፉ ሠራተኞች በተገኙበት በ2017 በጀት አመት የላቀ የስራ አፈፃፀም ላሳዩ ሰራተኞች በቅርንጫፉ በተዘጋጀው መድረክ ላይ እውቅና ተሰጠ።

በተጠናቀቀው በጀት አመት ያቀድናቸውን በአግባቡ እና በተሻለ መልኩ ለመፈፀማችን ሁሉም ሰራተኞ በየደረጃው ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ያበረከቱት፤ ያላሰለሰ ጥረት መሆኑን የቅርንጫፉ ስራ አስኪያጅ ተናግረዋል። አያይዘውም መጪውን አዲስ አመት በአዲስ መንፈስና ተነሳሽነት በተሻለ መልኩ ህብረተሰባችንን የምናገለግልበት እና የተሻለ ውጤት የምናስመዘግብበት እንዲሆን ከመቼውም ጊዜ በላይ ሁሉም የቅርንጫፉ ሰራተኞች የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

ቅርንጫፉ ማህበራዊ ሀላፊነቱን ከመወጣት አንፃር ከፎረሞቹ ጋር በመሆን ለ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የሚሆን የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ለደንበላ ክ/ከተማ እና ለሎጎ ክ/ከተማ ደብተር እና እስክሪፕቶ የተበረከተ ሲሆን፤እንዲሁም በቅርንጫፉ ውስጥ ለሚሰሩ የአቅም ውስንነት ላለባቸው 15 ወላጆች የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ተበርክቶላቸዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአዳማ ሆስፒታልና ሜዲካል ኮሌጅ ጋር በመተባበር ለቅርንጫፉ ሰራተኞች የጤና ትምህርት (Health Education) እና ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች (የደም ግፊትና የስኳር) የጤና ምርመራ ተካሂዷል። በዚህም መሰረት 26 ወንድ እና 25 ሴት በድምሩ 51 የሚደርሱ የቅርንጫፉ ሰራተኞች የጤና ምርመራ አድርገዋል። ከአዳማ ሆስፒታልና ሜዲካል ኮሌጅ የመጡት ረዳት ፕሮፌሰር ታደሰ ኩምሳ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ከፍተኛ የጤና ቀዉስ እያስከተሉ መሆኑን ጠቅሰው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ ፣ አመጋገብን በማስተካከል እና የጤና ምርመራ በማድረግ የራሳችንን ብሎም የቤተሰባችንን ጤና መጠበቅ እንዳለብን አስገንዝበዋል።

በመጨረሻም በ2017 በጀት አመት ከየስራ ክፍሉ ከፍተኛ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ቡድን መሪዎች እና ባለሙያዎች እንዲሁም የህክምና ግብአቶችን በማድረስ ቁርጠኛ ለሆኑ ሹፌሮች፣ የመጋዘን ኃላፊዎች እና የመጋዘን አደራጅ፤ የሰርተፍኬት እና የገንዘብ ሽልማት ተበርክቷል።

በተመሳሳይ ከዚህ ቀደም ቅርንጫፉን በተለያዩ የስራ ክፍሎች ሲያገለግሉ የነበሩና አሁን ላይ ቅርንጫፉን የለቀቁ ሰራተኞችን የሽኝት ፕሮግራም መካሄዱን የቅርንጫፉ ባለሙያ የሆኑት አለምነህ ንጉሴ አድርሰውናል ።

#ማገልገል ክብር ነዉ!!!

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት   የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር አከናወነ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ለሚገኙ ድጋፍ ለሚሹ ማህበ...
16/09/2025

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር አከናወነ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ለሚገኙ ድጋፍ ለሚሹ ማህበረሰቦች የማዕድ ማጋራትና የትምህርት መርጃ መሳሪያ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን ፤ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ የእንኳን አደረሳቹ መልእክት በማስተላለፍ አገልግሎቱ እንደ ከዚህ ቀደሙ ማህበራዊ ሃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝና የህክምና ግብዓት ተደራሽ ከማድረግ ባለፈም የማህበራዊ በጎ አድራጎት ስራዎችም ላይ ትኩረት በመስጠት ተሳታፊ እንደሆኑ ገልፀዋል፡፡

የወረዳው ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ተሰማ እንዳሉት የአገልግሎቱ አመራሮች አቅመ ደካሞችን በማስታወስ እያደረጉ ያለውን ድጋፍ በማመስገን ተቋሙ እየተወጣ ያለዉን ማህበራዊ ሃላፊነት አድንቀዋል፡፡

የአገልግሎቱ የሴቶችና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ አለምፀሀይ ዳታ እንደገለፁት የበጎ አድራጎት ተግባሩ ከአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ድጋፍ ለሚሹ የማህበረሰቡ ክፍሎች በተጨማሪ በአገልግሎቱ ለሚሰሩ ለተለዩ ሰራተኞችም የማዕድ ማጋራትና የትምህርት መርጃ መሳሪያ ድጋፍ እንደተደረገ ጠቁመዋል፡፡

ለፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ት/ቤት 200 ደብተርና እስክርቢቶ እንዲሁም 200 የንጽህና መጠበቂያ ሞዴስ ፣ለእዝነት ድርጅት 100 ዳይፐር፣ 100 ዋይፕስ 100 የልብስ ሳሙና 100 የገላ ሳሙና እንዳሁም ለተስፋአዳስ የካንሰር ማዕከል የምግብ ግብዓቶች ዘይት ፣ በግ ተለግዟል።

እንዳሁም የንፅህና መጠበቂያ የሚያገለግሉ የልብስ ሳሚና፣ የገላ ሳሙና እና ሞዴስ የተበረከተ ሲሆን በተቋሙ ለሚገኙ በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ 70 ሠራተኞች ለምግብ ፍጆታ የሚውሉ ግብዓቶችና የትምህርት መርጃ መሳሪያ ለልጆቻቸው ተበርክቷል።

#ማገልገል ክብር ነዉ
ዘጋቢ አማኑኤል ወርቃየሁ

11/09/2025

መላካም አዲስ አመት 2018

የተከበራችሁ የሀገራችን ህዝቦች፡ የህ/ተ/ም/ቤት የጤና፡የማህበራዊ ልማት፡የባህል ጉዳዮች የቋሚ ኮሚቴ አባላት፡ የአገልግሎቱ ስራ አመራር ቦርድ አባላት፡ የጤናው ሴክተር አመራሮች ፤ሙያተኞች፡የአገልግሎቱ ማኔጅመት አባላት፡ ስራአስኪያጆች፡መላው የአገልግሎቱ ሰራተኞች፤ባለድርሻ አካላት ; የሀገር ውስጥ አምራቾች እና የጤና ተቋማት ደንበኞች በሙሉ

እንኳን ለ2018 የኢትዮጵያውያን አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ/አደረሰን፡፡ አመቱ የጤና፡የደስታ፡የብልጽግና ከመላ ቤተሰቦቻችሁ ጋር እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ፡፡

ያሳለፍነው 2017 ዓመት በመድሃኒት አቅርቦት ሰንሰለቱ ብዙ ስኬቶችን ያስመዘገብንበትን ያህል ተግዳሮቶችን ያስተናገድንበት ነበር፡፡

በችግሮች ሳንደናቀፍ በሙሉ አቅማችን በመስራት የእኛን አገልግሎት ለሚሹ ሀገራችን ህዝቦች የህክምና ግብአቶችን መድረስ ችለናል፡፡
በአዲሱ አመትም መሰረታዊ መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ፤ ቀጣይነት ባለው መልኩ በማቅረብ ልናገልላችሁ ከመቼውም በላይ ቁርጠኞች ነን፡፡

መልካም አዲስ አመት ይሁንልን
ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር

Happy Ethiopian New Year – 2018 🌿

Dear all people of our Nation, MPs, EPSS Board members, Heath sector leaderships, experts, EPSS Management Members, Hub Managers, Stockholders, Donors, local manufacturers HFs Customers and our servant Officers.

As we welcome the New Year, I extend my heartfelt wishes to each of you and your families for good health, happiness and prosperity.

The past year has brought both challenges and achievements, yet with your unwavering guidance and commitment, we have continued to move forward with strength and purpose. I am deeply grateful for your commitment, wisdom and trust.

May this New Year bring us renewed energy and greater accomplishments as we work together to realize our vision and serve our nation with excellence.

Melkam Addis Amet! 🎉🌸

With sincere appreciation
Dr.Abdulkedir Gelaglo
Director General, EPSS

#መልካም አዲስ አመት
#እንቁጣጣሽ

 🇪🇹  Happy Inauguration Day of the Grand Ethiopian Renaissance Dam! Congratulations to our people of Ethiopia!!!   Pharm...
09/09/2025

🇪🇹
Happy Inauguration Day of the Grand Ethiopian Renaissance Dam! Congratulations to our people of Ethiopia!!!
Pharmaceutical Supply Service -

አገልግሎቱ በ2017በጀት አመት የላቀ አፈፃፀም ላሳዩ  ለሰራተኞች እውቅና ሰጠ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፧፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት  የጤና ሚኒስት...
08/09/2025

አገልግሎቱ በ2017በጀት አመት የላቀ አፈፃፀም ላሳዩ ለሰራተኞች እውቅና ሰጠ።

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፧፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ ፣ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ ፣ ም/ ዋና ዳይሬክተሮች ፣የቴክኒካል አማካሪ የቦርድ አባላት ፣ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፣ መላው የዋና መስሪያ ቤት ሠራተኞች በተገኙበት እንዲሁም 19ኙ ቅርንጫፎች በበይነ መረብ በመሳተፍ በ2017በጀት አመት የላቀ አፈፃፀም ላሳዩ ለሰራተኞች ጳጉሜ 3ቀን 2017 ዓ.ም እውቅና ተሠጥቷል።

ውል የተገባለት የአቅርቦት ስርዓትን በመተግበር በ2018 ዓ.ም በገባነው ውል መሰረት የህክምና ግብዓቶችን እንድናቀርብ ከመቼውም በበለጠ ተግተን መስራት ይገባናል ሲሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ አሳስበው ፤ ይህንን የመፈፀም አቅማችንን ከዚህ በላይ በማሳደግ ለአፍሪካ አርአያ የሚሆን እና ተሞክሮ የሚወሰድበት የአቅርቦት ሠንሠለት ተቋም በጋራ መፈጠር አለብን ብለዋል ።

አክለውም በአዲሱ አመት የህክምና ግብዓቶች እስከ ተጠቃሚው ድረስ የሚድረስበትን አግባብ ግልፀኝነት በመፍጠር ጠንክራ ስርዓት መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል ።

ባሳለፍነው አመት የተለያዩ ተግዳሮቶች ቢገጥሙንም በመቋቋም ትልቅ ተቋማዊ ውጤቶችን ተቀናጅተን ያስመዘገብንበት ፣ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎችን ያሳካንበት ነው። እነዚህን የተገኙት ስኬቶች ከላይ እስከታች ባሉ ሠራተኞች ትጋት እንዲሁም በአመራሩ ቁርጥኝነት የተገኙ ስኬቶች በመሆናቸው የህክምና ግብዓቶችን አቅርቦትን በማሻሻል ለህዝባችን የገባነውን ቃል በአገልጋይነት መንፈስ መፈፀም ችለናል ሲሉ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ ተናግረዋል።

ሆኖም ግን አሉ ዋና ዳይሬክተሩ አሁንም የእኛን አገልግሎት የሚፈልጉ ብዙ ዜጎች በመኖራቸው ከዋናው ግባችን ላአፍታም ልንዘናጋ አይገባንም ብለዋል።

መጭው አዲስ አመት 2018 የቅንጅት ስራዎችን በማጠናከር ያቀድናቸውን የምናሳካበት የጤና፣የመተባበር፣የፍቅር፣የአንድነት ፣የብልፅግና እና የስኬት አመት እንዲሆን ዶ/ር አብዱልቃድር መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ እንደተናገሩት ሁላችንም የምናገለግለው ህዝባችንን ነው በተለይም በዚህ ተቋም የሚለየው የዜጎችን ህይወት የሚያድን ስራ ስለምታከናውኑ ትልቅ ኩራት ይገባችኋል ብለው ፤ አገልግሎቱ የህክምና ግብዓት ለማህበረሰቡ ከማድረሱ ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ድጋፍ በማድረጉ አቶ ታረቀኝ ምስጋና አቅርበው ፤ ቀጣይም አጋርነታችሁ አይለየን ሲሉ ተናግረዋል ።

ከየስራ ክፍሉ ከፍተኛ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ቡድን መሪዎች እና ባለሙያዎች ፣ የህክምና ግብዓት በማድረስ ቁርጠኛ ለሆኑ ሹፌሮች ፣ በኢአርፒ(ERP) ትግበራ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከቱ ፕሮሰስ ሻምፒዮኖች ፣ መጋዘን ኃላፊዎች የሰርተፍኬት እና የገንዘብ ሽልማት የተበረከተ ሲሆን ፤ ሶፍትዌር ላበለፀጉ ባለሙያዎች ፣ አዳዲስ ሀሳቦችን በማስተዋወቅ ትልቅ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ልዩ ተሸለሚዎች የሜዳሊያ ፣ የሰርተፍኬት እና የገንዘብ ሽልማት ተሠጥቷል።

አገልግሎቱን ለበርካታ አመታት አገልግለው በጡረታ ለተሸኙ ሰራተኞች የምስጋና ስጦታ ፣ ለፋርሚኮር/ፋርሚድ የቀድሞ ሠራተኞች የመረዳጃ ማህበር የ100 ሺህ ብር ሽልማት ከአገልግሎቱ ተበርክቷል።

በመድረኩ በአፍሪካ የልዕቀት አካዳሚ መድረክ እና የአገልግሎቱ መላው ሰራተኞች ግምገማዊ ስልጠና የተነሱ ጉዳዮች አፈፃፀም ፣ የወዳደቁ ንብረቶች አወጋገድ እና የመዝናኛ ክበብ አፈፃፀሞች አፈፃፀም ሪፖርት በዝርዝር ቀርቧል።

የመድረኩ ዋና አላማ በባለፈው አመት የነበረው አፈፃፀም በመመልከት በቀጣይ ለ2018ዓ.ም ለምንሰራቸው ስራዎች ለማበረታታት ያለመ ሲሆን ፤ የእውቅና ፕሮግራሙ በሁሉም ቅርንጫፎች በተመሳሳይ ሁኔታ ከራሳቸው ነበራዊ ሁኔታ ጋር ባገናዘበ መልኩ እንደሚከናወን ይጠበቃል።

# ማገልገል ክብር ነዉ!
ማኅሌት አበራ

Address

9. 046572, 38. 728670
Addis Ababa

Telephone

+251112763276

Website

https://t.me/epsaethiopia2012

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram