Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS

Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS, 9. 046572, 38. 728670, Addis Ababa.

Ethiopian Pharmaceutical Supply service , EPSS
, procure ,manage and distribute RDF & Heath Programme Products for governmental health facilities to supply quality assured essential pharmaceutical with affordable prices & a sustainable manner in Eth

19/03/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

ኢዲ ሙባረክ!

Baga Geessan!
Hawaasa Amantii Islaamaa hundaaf baga ayyaana Iid Al-Fixrii waggaa 1447ffaan nagaan isin gahe.

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ።በዓሉ የሰላም፣የጤና፣ የፍቅር ፣ የደስታ፣የአብሮነት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን።የኢትዮ...
19/03/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

በዓሉ የሰላም፣የጤና፣ የፍቅር ፣ የደስታ፣የአብሮነት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት

ኢዲ ሙባረክ!

Baga Geessan!
Hawaasa Amantii Islaamaa hundaaf baga ayyaana Iid Al-Fixrii waggaa 1447ffaan nagaan isin gahe.

Ayyaanichi kan nagaa, fayyaa, jaalalaa, gammachuu fi tokkummaa akka isiniif ta’u hawwii keenya ni ibsina.

Tajaajila Dhiyeessii Madda Qorichaa Itoophiyaa.

Iid Mubaarak!

አገልግሎቱ ታላቁን የረመዳን ጾምን ምክንያት በማድረግ  የአብሮነት የኢፍጣር መርሃ ግብር አካሄደ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የረመዳን ጾምን ምክንያት በ...
18/03/2026

አገልግሎቱ ታላቁን የረመዳን ጾምን ምክንያት በማድረግ የአብሮነት የኢፍጣር መርሃ ግብር አካሄደ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የረመዳን ጾምን ምክንያት በማድረግ የጤና ሚኒስቴር ዴኤታዎች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው የተጠሪ ተቋማት ኃላፊዎች እንዲሁም የአገልግሎቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ሙስሊም ሰራተኞች በተገኙበት በጋራ የአፍጥር ፕሮግራም አከናውኗል።

ረመዳን የሰላም፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ የአንድነት እና የመረዳዳት ወር በመሆኑ ከማህበረሰባችን ጋር መቀራረብን በመፍጠር ሁላችንም ከፈጣሪ ዘንድ ምስጋና ለማግኘት ጉልህ ሚና አለው ሲሉ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ ተናግረው ፤ አክለውም ለ1447ኛው የኢድ አል ፈጥር በአል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።

ረመዳን የእዝነት ወር በመሆኑ በዚህ ቀን ተሰባስበን ፈጣሪ የሚወደዉን መርሀ -ግብር በማዘጋጀት ለተደረገው የኢፍጣር ፕሮግራም ተሳታፊዎች ለአገልግሎቱ ምስጋና አቅርበዋል።


ሰላም ይደግ

VACANCY ANNOUNCEMENTDeadline: Registration Deadline March 23, 2026Registration Venue: EPSS Headquarters, near to St. Pau...
17/03/2026

VACANCY ANNOUNCEMENT

Deadline: Registration Deadline March 23, 2026
Registration Venue: EPSS Headquarters, near to St. Paul's Hospital Millennium Medical College-SPHMMC

በሲዳማ ክልል ዉል የተገባለት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓትን ለማጠናከር  እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ዉል የተገባለት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓትን ለማሻሻል በትኩረ...
16/03/2026

በሲዳማ ክልል ዉል የተገባለት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓትን ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ዉል የተገባለት የመድኃኒት አቅርቦት ስርዓትን ለማሻሻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ከኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት ሀዋሳ ቅርንጫፍ ጋር በመተባበር ባዘጋጁት መድረክ ላይ መገለፁ ታውቋል፡፡

መድረኩ ላይ የተገኙት የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ በመልዕክታቸው ፦ከ2015 ዓ/ም አጋማሽ ጀምሮ ''ለውጤት እንስራ" ኢኒሼቲቭ እንደ ክልል የጤናውን ዘርፍ አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ሞዴል ለማድረግና ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለዘርፉ ስኬት የመድሃኒት አቅርቦት መሟላት ወሳኝ መሆኑንም አንስተዋል።

ኃላፊዋ አያይዘውም በጤናው ሴክተር የመድሀኒት አቅርቦትና አስተዳደር ስራ ለማጠናከር ፣የህዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ፣በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ የሚያቀርቡ የህዝብ መድኃኒት ቤቶችን ለማስፋፋት እየተሰሩ ባሉ ጠንካራ ስራዎች የተመዘገቡ ውጤቶች አበረታችና ተስፋ ሰጪ መሆናቸውን አውስተዋል ።

ይሁን እንጂ ቀጣይነት ያለው የአቅርቦት ስርአት እንዲጎለብት፣ ወቅቱን የጠበቀ አቅርቦት ለመፍጠር፣ ብክነትን ለመቀነስ እንዲሁም ጠንካራ እና የማይበገር የጤና ስርአት ከመገንባት ረገድ አልፎ አልፎ የሚታዩ የፍላጎትና የአቅርቦት አለመጣጣም ጉድለት በትኩረት መስራት እንደሚገባ ዶ/ር ሰላማዊት በአፅንኦት አሳስበዋል።

ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተየያዘ የህብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ ያስችል ዘንድ የተጣለብንን ሀላፊነት በብቃት ለመወጣት የህክምና ግብአቶችን ሳይቆራረጡ ለማቅረብ ቴክኖሎጂን ጨምሮ የመድኃኒት አስተዳደር ስርዓቱን የሚያሻሽሉ የለውጥ መሳሪያዎች እና አሰራሮችን በተገቢው አቀናጅተን መፈጸም ይጠበቅብናል ሲሉ በአፅንኦት ተናግረዋል ።

በክልሉ በዚህም የተገኙ ጠንካራ ጎኖችን ለማጎልበት ያጋጠሙ ችግሮችን ለመገንዘብና በጋራ ለመፍታት የተወሰዱ እርምጃዎችን ለመገምገም የስምንት ወር አፈጻጸም ሪፖርቶች ከክልሉ ጤና ቢሮ እንዲሁም
ከኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት ሀዋሳ ቅርንጫፍ ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

በጉዳዩ ላይ ከመድረኩ ከተሳታፊዎች አንዳንዶች በሰጡት አስተያየት ለጤና ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ መጎልበት ቁልፍ የሆነውን የጤና ግብኣት አቅርቦት ስርኣት ማሻሻል ላይ የተሻለ አፈጻጸም በቀጣይ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ እና በአንጻሩ ጊዜ ሳይወስዱ በአስቸኳይ ሊታረሙ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ ጠንካራ ውይይት በማድረግ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በመጨረሻም መድረኩ ላይ የክልሉ ጤና ቢሮቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ፣ የቢሮው የማኔጅመንት አባላት፣ የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሀዋሳ እና ደቡብ ክላስተር ስራ አስኪያጅ አቶ ዘመን ለገሠ ፣ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ የአራቱም ዞኖች ጤና መምሪያ /ዴስክ ሀላፊዎች፣ የወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሀላፊዎች፣ የሆስፒታል ስራ አስኪያጆች ፣ ከቢሮው የዘርፉ ባለሙያዎች እንዲሁም የኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት ሀዋሳ ቅርንጫፍ ባለሙያዎች ተሳታፊ መሆናቸው ታውቋል።


ምንጭ ፦ የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ




የሀዘን  መግለጫ
14/03/2026

የሀዘን መግለጫ

የኢፌድሪ ጤና ሚንስትር መቅደስ ዳባ (ዶ/ር) በጋሞ ዞን በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገለፁ ሚንስትሯ በማህበራዊ ትስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፥ በደቡብ ኢት...
12/03/2026

የኢፌድሪ ጤና ሚንስትር መቅደስ ዳባ (ዶ/ር) በጋሞ ዞን በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገለፁ

ሚንስትሯ በማህበራዊ ትስር ገፃቸው ባሰፈሩት መልዕክት፥ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ በዜጎቻችን ላይ በደረሰው የህይወት መጥፋት እና ድንገተኛ አደጋ የተሰማኝን ልባዊ ሀዘን እየገለፅኩ ለተጎጂ ቤተሰቦች እና ለመላው ኢትዮዽያውያን መፅናናትን እመኛለሁ ብለዋል።

የጤና ሚኒስቴር ከአደጋ ስጋት ኮሚሽን እና ከክልሉ ጤና ቢሮ እንዲሀም የኢትዮዽያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዮት ጋር በመተባበር የድንገተኛ ጤና ፈጣን ምላሽ እና የህክምና ቡድኑን ወደ አካባቢው መላኩን የገለፁ ሲሆን ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉም መልዕክታቸውን አስፍረዋል።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በቅርንጫፎች በኩል የሚያከናውነውን የሕክምና ግብዓት የማቅረብ ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨አገልግሎቱ በሀገሪቱ በሚገኙ ሁ...
12/03/2026

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በቅርንጫፎች በኩል የሚያከናውነውን የሕክምና ግብዓት የማቅረብ ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
አገልግሎቱ በሀገሪቱ በሚገኙ ሁሉም ክልሎች የመድኃኒት አቅርቦትን በማስፋፋትና ተደራሽነቱን በማሻሻል፣ ለጤና ተቋማት ቀጣይነት ያለው የሥርጭት ሥራ እያከናወነ ይገኛል።

በያዝነው በጀት ዓመት የአቅርቦት ሥርዓቱን ትርጉም ባለው መልኩ ለማሻሻል ከተተገበሩ ቁልፍ ተግባራት መካከል የቅድሚያ ውል የተገባለት የአቅርቦት ሥርዓት (CDSS) ዋናው ሲሆን፣ አገልግሎቱ ከ5,000 በላይ ከሚሆኑ የጤና ተቋማት ጋር ውል በመግባት እስካሁን ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ግብዓቶችን በሽያጭ አስተላልፏል።

የአገልግሎቱ የመድኃኒትና ሕክምና መገልገያዎች ሥርጭት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ናሆም ገመቹ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በበጀት ዓመቱ እስካሁን ባለው ጊዜ ውስጥ በተገላባጭ ፈንድ 13.9 ቢሊዮን ብር እንዲሁም በጤና ፕሮግራም 50.1 ቢሊዮን ብር፣ በድምሩ 64 ቢሊዮን ብር የሚገመቱ መድኃኒቶችና የሕክምና መገልገያዎችን ለጤና ተቋማት ማሰራጨት ተችሏል።

ከዚህ ውስጥ 13 ቢሊዮን ብር ግምት ያላቸው ግብዓቶች የኤች.አይ.ቪ፣ የቲቢ እና የወባ በሽታ መድኃኒቶች ይገኙበታል።

ልዩ ትኩረት የሚሹና ግጭት የሚስተዋልባቸውን አካባቢዎች የሕክምና ግብዓት ተደራሽ ለማድረግ ከአጋር ድርጅቶች ጋር በተሰራ ቅንጅታዊ ሥራ በመደበኛ 2,218,541,949.21 ብር እንዲሁም በጤና ፕሮግራም 7,977,228,811.37 ብር፣ በድምሩ 10,195,770,760.58 ብር የሚገመት ግብዓት ተሰራጭቷል።

በበጀት ዓመቱ ከማዕከል ወደ ትግራይ ክልል ቅርንጫፎች 4,652,757,214.77 ብር የሚገመት ግብዓት እንዲደርስ የተደረገ ሲሆን፣ በክልሉ ለሚገኙ የጤና ተቋማት የተሰራጨው መጠን ደግሞ 3,490,079,640 ብር መሆኑን ዳይሬክተሩ አክለው ገልጸዋል።

በየካቲት ወርም ዋጋቸው ከ260 ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ የጤና ፕሮግራም ግብዓቶች ከማዕከል ተልከዋል።

በተጨማሪም በጤና ሚኒስቴር በኩል ተገዝተው በትግራይ ክልል ለሚገኙ የጤና ተቋማት የተመደቡ፣ 24,038,451.29 ብር ግምት ያላቸው 24 የፀሐይ ብርሃን ኃይል ማመንጫዎች (Solar Panels) ሥርጭት እየተከናወነ ይገኛል።

በአሁኑ ወቅት በሁለቱም ቅርንጫፎች(መቀሌ ና ሽሬ) በተገላባጭ ፈንድ እና በጤና ፕሮግራም 2,443,255,561.15 ብር ዋጋ ያለው የግብዓት ክምችት በመጋዘን ውስጥ ይገኛል።

በዚህ ክምችት ላይ በተሰራ የትንተና ውጤት መሠረት፣ በተለይም የጤና ፕሮግራም ግብዓቶች በተገቢው ሁኔታ ለጤና ተቋማት እንዲሰራጩ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ይሠራል።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የማኅበረሰቡን ጤና ለመጠበቅ የሚያስችሉ ግብዓቶችን ተደራሽ የማድረግ ተግባሩን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ይገልጻል።

በመሆኑም የሚላኩ የሕክምና ግብአቶች ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ በየደረጃው ያሉ የሚመለከታቸው አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪውን ያስተላልፋል።

#ማገልገል ክብር ነው!

በመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት የአገልግሎት ጥራትን ለማጠናከርና ከሽልማት ወደ ላቀ ስኬት ለመሻገር አዳዲስ አቅጣጫዎችን አስቀመጠ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አ...
08/03/2026

በመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት የአገልግሎት ጥራትን ለማጠናከርና ከሽልማት ወደ ላቀ ስኬት ለመሻገር አዳዲስ አቅጣጫዎችን አስቀመጠ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ተቋማዊ የጥራት ደረጃውን ለማሻሻል በውስጥ ኦዲት ሲያከናውን ቆይቷል ፤ በመሆኑም በውስጥ ኦዲት በተገኙ ግኝቶች ላይ በማኔጅመንት አባላት ጋር በመገምገም ለቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል ።

በውይይቱ ወቅት እንደተገለጸው ተቋሙ በኦዲት ሂደት ወቅት የተሰጡ ሙያዊ አስተያየቶችን እንደ ግብዓት በመጠቀም የአሰራር ሂደቶችን ለማሻሻል ትኩረት ይሰጣል።

"የአቅርቦት ሰንሰለቱን የአሰራር ሂደት ጥራት መሰረት ባደረገ መልኩ የሚሰሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል ይገባል" ያሉት የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር፣ የተሰጡ አስተያየቶችን እንደ ተቋም በጋራ ለማስተካከልና ውጤታማነቱን ለማረጋገጥ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

የአገልግሎቱ የመድኃኒትና ህክምና መሳሪያዎች የጥራት ቁጥጥርና ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሀብቱ በርሄ በበኩላቸው ማኔጅመንቱ በውስጥ ኦዲት ግኝቶች በመጠቀም የጥራት ስታንዳርድ ለማሻሻል የሰው፣ የፋይናንስ፣ የመሠረተ ልማት እና የቴክኖሎጂ ሀብቶችን አጠቃቀም ምን እንደሚመስል አስረድተው ፤ ወደ ድርጅታዊ የጥራት ግቦች (የKPI ስኬት) በየዳይሬክቶሬቱ ያለው ድርሻ ፣ ለ ISO የምስክር ወረቀት እና ለ13ኛው ዙር የEQA ብሔራዊ ውድድር እንዴት መዘጋጀት እንደሚቻል ጠቅሰዋል ።

የመድኃኒትና የህክምና ግብዓቶች ጥራት ቁጥጥርና ክትትል ቡድን መሪ አቶ አበበ በየነ በሪፖርታቸውም በውጥና በውጪ በኦዲት የተገኙ ግኝቶች ላይ ሊወሰዱ የሚገቡ የማስተካከያ እርምጃዎችን ዝርዝር አቅርበዋል ።

በዕለቱ የጥራት አስተዳደር ስርዓት አዲሱ ፖሊሲን አስመልክቶ በቀረቡ ሀሳቦች ላይ የጋራ መግባባት የተደረሰ ሲሆን፣ ለቀጣይ ስራዎችም በዳይሬክቶሬቶቹ የሚሠሩ ተግባራት ግልጽ አቅጣጫ ተቀምጧል።

ዘጋቢ፦ ማኅሌት አበራ

07/03/2026
ከጌትስ ግብረሰናይ አለም አቀፍ ድርጅት የተወጣጣ ቡድን አገልግሎቱን ጎበኙ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከጌትስ ግብረሰናይ አለም አቀፍ ድርጅት ለበርካታ አመ...
06/03/2026

ከጌትስ ግብረሰናይ አለም አቀፍ ድርጅት የተወጣጣ ቡድን አገልግሎቱን ጎበኙ

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከጌትስ ግብረሰናይ አለም አቀፍ ድርጅት ለበርካታ አመታት በተለያዩ ዘርፎች በጋራ ሲሰራ የቆየ አጋር ድርጅት መሆኑ ይታወቃል ፤ በመሆኑም የቤተሰብ ምጣኔ ዘርፍ እና የበሽታ መከላከያ ክትባት ዘርፍ ከዋናው መስሪያ ቤትና የክልል ቢሮ ም/ ዳይሬክተሮች ፣ በኢትዮጵያ የጌትስ ፋውንዴሽን ባለሙያዎች የተወጣጣ ቡድን አገልግሎቱን ጎብኝተዋል ።

አጠቃላይ ተቋማዊ መዋቅር ፣ የግዥ ኦፕሬሽን ማሻሻያ ፣ የህክምና ግብዓት አቅርቦት ስልት ፣ የአቅርቦት ስርዓቱ የትራንስፎርሜሽን ማዕቀፍ ፣ የሀገር ውስጥ አምራቾች የገበያ ድርሻ ፣ የስርጭት መጠን ፣ የቆጠራ ትክክለኝነት ፣ የብክነት መጠን አፈፃፀም ፣ የአቅርቦት ሰንሰለት ውህደትን ማጠናከር ፣ የደንበኛ እርካታን ማሳደግ እነዚህንና ሌሎች ጉዳዮችን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ በዝርዝር አቅርበዋል ።

በተቋሙ የመጡ ለውጦችን ፣ በዚህ ወቅት ቅድሚያ ተሰጥቷቸው እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን የተመለከቱ ሲሆን ፤ ጥያቄዎችን አንስተው በዋና ዳይሬክተሩ ምላሽ ተሰጥቷቸዋል ።

በመጨረሻም የህክምና ግብዓት መጋዘን በመዘዋወር ምልከታ አካሂደዋል ።

ዘጋቢ ማኅሌት አበራ
#ማገልገል ክብር ነዉ

እንኳን ለ130ኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!አድዋ የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ የኩራት ምንጭ፣ የነፃነት ተምሳሌት እና የኢትዮጵያዊያን የአንድነት ማህተም ነው!ጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻ...
01/03/2026

እንኳን ለ130ኛው የአድዋ ድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

አድዋ የጥቁር ሕዝቦች ሁሉ የኩራት ምንጭ፣ የነፃነት ተምሳሌት እና የኢትዮጵያዊያን የአንድነት ማህተም ነው!

ጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻችን በደማቸውና በአጥንታቸው የፃፉት ታሪክ ዛሬም ድረስ በፅናት እንድንቆም ብርታት ይሆነናል።

እኛም በኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት፣ ይህንን የአባቶቻችንን የድል አድራጊነት መንፈስ በመውረስ፣ የሕዝባችንን ጤና ለመጠበቅና ጥራት ያለው መድኃኒት በየደረጃው ለሚገኝ የጤና ተቋም በተመጣጣኝ ዋጋ ለማድረስ የምናደርገውን ጥረት አጠናክረን እንቀጥላለን።

የአድዋ ድል የሁላችንም ኩራት ነው!


Address

9. 046572, 38. 728670
Addis Ababa

Telephone

+251112763276

Website

https://t.me/epsaethiopia2012

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram