Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS

Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS, 9. 046572, 38. 728670, Addis Ababa.

Ethiopian Pharmaceutical Supply service , EPSS
, procure ,manage and distribute RDF & Heath Programme Products for governmental health facilities to supply quality assured essential pharmaceutical with affordable prices & a sustainable manner in Eth

01/02/2026
01/02/2026
የተሻለ የህክምና ግብዓት አቅርቦት እንዲፈጠር መፍጠን ፣ መፍጠርና ማጥራት ይገባል።፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የ6 ወር እቅድ ክንዉኑን ከጥር 21_23 ቀን 2018 ዓ.ም...
31/01/2026

የተሻለ የህክምና ግብዓት አቅርቦት እንዲፈጠር መፍጠን ፣ መፍጠርና ማጥራት ይገባል።
፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የ6 ወር እቅድ ክንዉኑን ከጥር 21_23 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በየዘርፉ የገመገመ ሲሆን ዘመናዊ አሰራርን በመተግበር የመድኃኒት መገኘት ጥያቄን ለመመለስ ጅምር ስራዎችን በፍጥነትና ፈጠራ በታከለበት ሁናቴ ማከናወን እንደሚገባ ተገልጿል።

ለ3 ቀናት ሁሉም ዳይሬክቶሬቶች በዋና መስሪያ ቤት አፈፃፀማቸዉን በየዘርፉ የገመገሙ ሲሆን ፤ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጎልበት እንደሚገባና ተቋማዊ ራዕይን ለማሳካት መትጋት እንደሚያስፈልግ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።

አገልግሎቱ ከ5ሺ በላይ ከሚሆኑ የጤና ተቋማት ጋር የ24 ቢሊየን ብር የህክምና ግብዓት አቅርቦት ዉል የገባ ሲሆን የቀጥታ የመድኃኒት ስርጭት አቅሙም አድጓል።

አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም እንዲሁም የገበያ ዋጋን ለማረጋጋት ተቋሙ የጀመረዉን ዉል የተገባለት የአቅርቦት ስርዓት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ ገልፀዋል።

የዉጭ ምንዛሬን ለማዳንና ሀገራዊ አቅምን መጠቀም ስለሚገባ የሀገር ዉስጥ መድኃኒት አቅራቢዎች የተሻለ ግብዓት ማቅረብ እንዲችሉ መደገፍ ይገባል።

የስራ ከባቢን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ምቹና የስራ ፍሰትን የሚያቀላጥፍ እንዲሆን የተጀመሩ ክንዉኖችን ማጠናቀቅ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

የተቋሙ ም/ዋና ዳይሬክተሮች በየዘርፋቸዉ የተከናወኑ አበይት አፈፃፀሞችን ያቀረቡ ሲሆን በመጋዘን አያያዝና አስተዳደር ላይ የተሰሩ የማሻሻያ ተግባራት ፤ የግዥ ሂደትን ማሳጠር ፤ የተቀናጀ የመረጃ አስተዳደር ስርዓት ዉጤታማነትን ማስቀጠል በሚሉና መሰል አስተዳደራዊና የኦፕሬሽን ጉዳዮች ዙሪያ ገለፃ አቅርበዋል።

በእያንዳንዱ የስራ ክፍል በግምገማ የተነሱውጤታማነትን የሚቀንሱ(inefficiency )ተግዳሮቶችን ፈጥኖ በማረም በቀሪ ወራት የድርጊት መርሃ ግብር ወጥቶላቸው እንድተገበሩ በመስማማት ግምገማው ተጠናቋል

#ማገልገል ክብር ነዉ
አማኑኤል ወርቃየሁ

አገልግሎቱ የ6 ወር አፈፃፀሙን እየገመገመ ይገኛል፨፨፨፨፨፨ከጥር 21 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የግማሽ ዓመት ዕቅድ ክንውን ግምገማ መርሃ ግ...
29/01/2026

አገልግሎቱ የ6 ወር አፈፃፀሙን እየገመገመ ይገኛል
፨፨፨፨፨፨
ከጥር 21 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የግማሽ ዓመት ዕቅድ ክንውን ግምገማ መርሃ ግብሩን የሚያካሄድ ሲሆን በዛሬዉ እለት ግምገማዉን ተጀምሯል።

በግምገማው የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለቱን የበለጠ የተሳለጠና ቀልጣፋ ለማድረግ የተወሰዱ አዳዲስ የፈጠራ ሀሳቦች እንዲሁም በቁልፍ የአፈፃፀም መለኪያዎች መሰረት የተከናወኑ ተግባራት በዝርዝር በየዘርፉ እየተገመገመ ይገኛል።

ግምገማው በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ውስጥ የአገልግሎቱ ከፍተኛ አመራሮች ፣ ዳይሬክተሮች ፣ የቡድን መሪዎችና ኦፊሰሮች በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።

#ማገልገል ክብር ነዉ
አማኑኤል ወርቃየሁ

በመድኃኒት አቅርቦት ዙሪያ የልምድ ልውውጥ ተካሄደ----------------------------------------------- የሩዋንዳ ሜዲካል ሠኘላይ (RMS) ልዑካን ቡድን ከኢትዮጵያ መድኃ...
29/01/2026

በመድኃኒት አቅርቦት ዙሪያ የልምድ ልውውጥ ተካሄደ
-----------------------------------------------
የሩዋንዳ ሜዲካል ሠኘላይ (RMS) ልዑካን ቡድን ከኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጋር የልምድ ልውውጥ አከናወኑ፡፡

በአሁኑ ሰአት በሩዋንዳ መድኃኒት አቅራቢ አገልገሎት ውስጥ ዘመናዊ የመድኃኒትና የሕክምና መገልገያዎች ማከማቻ መጋዘን ስራ እንዲሁም ዘመናዊ ትክኖሎጂ የመተግበር ስራ እየተጠናከረ እንደሚገኝና የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከፍተኛ መጠንና ዘመናዊ የመድኃኒት ማከማቻ ያለው በመሆኑ ልምድ ለመቅሠም መገኘታቸው ተገልጿል፡፡

በእለቱ በመጋዘን አያያዝና ፍሠት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መሐመድ ጀማል ገለፃ የተደረገላቸው ሲሆን የአገልግሎቱን የመድኃኒትና የሕክምና መገልገያ ግብአቶች ማከማቻ መጋዘኖችን፣ የተሠሩ መሠረተ ልማት ስራዎች እንዲሁም የቅዝቃዜ ሠንሠለት የተገጠመላቸዉ መጋኖች በዋናው መ/ቤት እና በአዳማ ቅርንጫፍ ጎብኝተዋል፡፡

ልዑካን ቡድኑ የአሠራር ሂደት የግብዓት ቁጥጥር አያያዝ እንዲሁም የመጋዘን መሠረተ ልማት ስራዎች ላይ ያሉ መልካም ተሞክሮዎች በመቅሠም ጠቃሚ ልምድ ለመቅሠም መቻላቸውን ገልፀው ያገኙዋቸው መልካም ተሞክሮዎች በአሁኑ ሠአት በሩዋንዳ እየተገነባ ለሚገኘው ሴንትራል ሜዲካል ስቶር እንደግብአትነት እንደሚጠቀሙበት አስረድተዋል፡፡

#ማገልገል ክብር ነው
በፀሎት የማነ

28/01/2026
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዘመናዊ የደም መመርመሪያ ማሽኖችን ለጤና ተቋማት አስረከበ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ...
28/01/2026

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዘመናዊ የደም መመርመሪያ ማሽኖችን ለጤና ተቋማት አስረከበ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የላቦራቶሪ አገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል በ2018 በጀት ዓመት 295 የCBC (Complete Blood Count) ማሽኖችን ለጤና ተቋማት ለማቅረብ ማቀዱን አስታወቀ።

የዚሁ ዕቅድ አካል የሆነው የመጀመሪያ ዙር የ81 ማሽኖችና የሪኤጀንቶች ርክክብ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም በአገልግሎቱ ዋና መሥሪያ ቤት ተከናውኗል።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬሕይወት አበበ፣ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ሚኒስትር ዴኤታዋ ወ/ሮ ፍሬሕይወት አበበ በወቅቱ እንደገለጹት፣ በጤናው ዘርፍ የተጀመረው ሪፎርም ውጤት እያመጣ ሲሆን፣ በተለይም እነዚህ ማሽኖች የእናቶችና የሕፃናትን ሞት ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት ያግዛሉ።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ በበኩላቸው፣ ማሽኖቹ በተመጣጣኝ ዋጋ ለጤና ቢሮዎች እየቀረቡ መሆኑንና ቀሪዎቹ 214 ማሽኖች እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም ድረስ ለተቋማቱ እንደሚዳረሱ አረጋግጠዋል።

እነዚህ ዘመናዊ ማሽኖች ለአጠቃቀም ምቹ ከመሆናቸው ባለፈ፣ በምርመራ ወቅት ትክክለኛ መረጃን በአጭር ጊዜ ውስጥ መስጠት መቻላቸው ለሕክምናው ሂደት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።

#ማገልገል ክብር ነው!
በአማኑኤል ወርቃየሁ

ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በመቆጣጠር ሙሉ በሙሉ ነፃ ሆናለች -  ክብርት ዶር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስቴር ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ኢትዮጵያ በተቀናጀ እና ጠንካራ የበሽታ መከ...
26/01/2026

ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በመቆጣጠር ሙሉ በሙሉ ነፃ ሆናለች -
ክብርት ዶር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስቴር
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ኢትዮጵያ በተቀናጀ እና ጠንካራ የበሽታ መከላከል መርሐ ግብር የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በመቆጣጠር ሙሉ በሙሉ ነፃ መሆኗን ተገለጸ፡፡

ይህ የተገለጸው በዛሬው ዕለትበተካሄደው ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስን መቆጣጠሯን አስመልክቶ በተዘጋጀው የማብሰሪያ መርሐ ግብር ላይ የጤና ሚኒስትርዋ ዶር መቅደስ ዳባ እንደገለጹት ፤ የማርበርግ ቫይረስን ለመከላከል በተወሰደው የተቀናጀና አስቸኳይ ምላሽ ቫይረሱን ከኢትዮጵያ ማጥፋት መቻሉን አብስረዋል፡፡

በጥቅምት ወር በጅንካ ከተማ ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በተቀናጀ የጤና ስርዓትና አገልግሎት ነፃ ማድረግ እንደተቻለም ከብርት የጤና ሚኒስትርዋ ዶር መቅደስ ዳባ በይፋ ያበሰሩት፡፡

ዶ/ር መቅደስ ለኢትዮጵያ እንግዳ የሆነውን የማርበርግ ቫይረስ መቆጣጠር በመቻሉ እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል፡፡ስኬቱ በሀገራችን ታሪክ ውስጥ ትልቅ አሻራ ያለው ነው ያሉት ሚኒስትሯ÷ በሽታውን ለመቆጣጠር ድጋፍ ላደረጉ የጤና ባለሙያዎች እና ሌሎች አካላት ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ሚኒስተርዋ በዚህ ወቅት እንዳሉት ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው በሽታን በመከላከልና አክሞ ማዳንን መሰረት በማድረግ የዜጎችን የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ለማጠናከር በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑንን ገልጸዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎን ጨምሮ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች፣ የጤና ሚኒስትር ከፍተኛ የስራ ሃለፊዎች እና አጋር አካላት ተገኝተዋል፡፡

የአፍሪካ የህክምና ግብዓት ማኑፋክቸሪንግ ንግድ፣ ኤግዝቢሽንና ኮንፍረንስ (African Health Manufacturing Trade, Exhibition and Conference- AHMTEC 202...
23/01/2026

የአፍሪካ የህክምና ግብዓት ማኑፋክቸሪንግ ንግድ፣ ኤግዝቢሽንና ኮንፍረንስ (African Health Manufacturing Trade, Exhibition and Conference- AHMTEC 2026) አዘጋጅ ኮሚቴዎች አገልገሎቱን ጎበኙ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ኢትዮጵያ የ2026 የአፍሪካ ሀገራት የህክምና ግብዓት ማኑፋክቸሪንግ ንግድ፣ ኤግዚቢሽንና ኮንፍረንስ AHMTEC 2026 ከኦክቶበር 6 እስከ 8 የምታዘጋጅ ሲሆን ፤ በዚህም አዘጋጅ ኮሚቴዎች በአገልግሎቱ ጉብኝት አድርገዋል።

በመድኃኒትና የህክምና መገልገያዎች አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ታሪካዊ የሆነው ኤግዚቢሽንና ኮንፍረንስ በ2025 በጋና አክራ የተከናወነ ሲሆን ሀገራችን በዘርፉ የተደረገው ሰፊ ድጋፍና የተመዘገበውን ተስፋ ሰጪ ውጤት ከግምት በማስገባት AHMTEC-2026 እንድታዘጋጅ ልትመረጥ ችላለች።

ይህንን ተከተሎ ከተለያዩ ሀገራትና ተቋማት የተውጣጡ የአዘጋጆች ቡድን ጤና ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት የቅድመ ዝግጅት ምልከታና ጉብኝት ላይ ሲሆኑ በአህጉሩ አንጋፋ የሆነው የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎትም ቡድኑን በደማቅ አቀባበል በመቀበል ዝግጁነቱን አሳይቷል።

አዘጋጅ ኮሚቴዉ በአገልግሎቱ በመገኘት በቅድመ ዝግጅቱ ዙሪያና አጠቃላይ በመድኃኒት አቅርቦቱ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ፤ የአቅርቦት ሰንሰለት ስትራቴጂዎች እንዲሁም ተቋሙ የፋርማሲዩቲካል አምራች ዘርፉን ለመደገፍ የሄደበት ርቀትና ቀጥይ ስራዎችን በማቅረብ ሰፊ ገለጻ ተደርጎ ውይይት ተከናዉኗል፡፡

ኤግዚቢሽንና ኮንፈረንሱ በሀገራች በጤናው ዘርፉ ለአምራች ኢንዱስትሪው የተሰጠውን ትኩረትና የተገኙት መልካም ተሞክሮዎችን ከመቀመርና ማስፋት ባሻገር በአፍሪካ የዘርፉን አህጉራዊ ጥምረት በማጠናከር ጥራትና ፈዋሽነታቸው የተረጋገጠ መድኃኒቶች ለዜጎች ቀጣይነት ባለው ዓግባብ ለማቅረብ ያነገብነውን ተልእኮ እውን ለማድረግ የማይተካ ሚና እንደሚኖረው የአገልግሎቱ ም/ዋ ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ንጉሴ ተናግረዋል።

የመድኃኒት እና መገልገያ መሳሪያዎች አምራች ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ታደሰ ተፈሪ እንደተናገሩት ኤግዚብሽኑ እንደ ሀገር አቅማችንን እና በፖሊሲ ረገድ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለአፍሪካዊያን እና ለዓለም ለማሳየት ፤ ለአምራቾች የገበያ ትስስርን ለመፍጠር እንዲሁም ወደ ኢትዮጵያ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በኤግዚብሽን እና ጉባኤዉ በዋናነት ሁሉም የአፍሪካ ሀገራት እንዲሁም ሌሎች አለም አቀፍ አምራቾች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

#ማገልገል ክብር ነዉ!
ሰላም ይደግ

18/01/2026

እንኳን ለ2018 ዓ.ም ለ ጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

ጤና የሁሉ ነገር መሠረት ነው! ጤና ይስጠዎት እንጂ ጤናዎ እክል ካጋጠመዎ፣

ላለፉት 78 ዓመታት ያህል መድኃኒቶችን፣ የህክምና መገልገያዎችን፣የህክምና መሳሪያዎች እና የላቦራቶሪ ሬኤጀንቶችን ከ5ሺ በላይ የጤና ተቋማት አሰራራችንን "ERP" በተባለ የተቀናጀ ዘመናዊ በቴክኖሎጂ ታግዞ በማቅረብ ለሀገራችን የጤና ዘርፍ የደምስር በመሆን በህብረተሰባችን በማገልገል ላይ የሚገኝ አንጋፋ ተቋም ነው ።

"በዚህ የሕይወት ዘመን፣አገልግሎታችን ባካበትነው ከፍተኛ ልምድ እና ትጉህ ሰራተኞቹ ታግዞ ፣ዘመናዊ የመድኃኒት የአቅርቦት ሰንሰለት ስርዓት በመዘርጋት ለሀገራችን የጤናው ሴክተር የደምስር በመሆን ጥራታቸው በተጠበቀ ፣ፈዋሽነታቸው የተረጋገጠ መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እና ቀጣይነት ባለው መልኩ ወደ ሁሉም የጤና ተቋማት በ አራቱም ማእዘናት ባሉን 19 ቅርንጫፎች በኩል ያደርሳል ።"

ለህብረተሠቡ በነፃ የሚቀርቡ የጤና ፕሮግራም እና የተገላባጭ ፈንድ መደበኛ መድኃኒታችን እንገዛለን፣እናስተዳዳደራለን፣እናከማቻለን ፣እናሰራጫለን።

በአዲሱ በተሻሻለው አዋጅ 1354/2017 አገልግሎታችን በጤና ዘርፍ የተሰጠውን ተልዕኮ በተሻለ ሁኔታ እንዲወጣ ወደርየለሽ ሚና በመጫወት ላይ ይገኛል ።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት(EPSS) በአዲሱ አዋጅ መሠረት "ውል የተገባለት የአቅርቦት ሥርዓትን" (Committed Demand and Supply system - CDSS) በመተግበር ሀገራችን የመድኃኒት አቅርቦቱ አስተማማኝ እንዲሆን ከመቼውም በላይ በታላቅ ቁርጠኝነት ወደ ስራ ገብተናል ።

ለዚህ ቁልፍ ስራችን ውጤታማነት ጤና ተቋማት የግብአት ፈላጎታቸውን በመመጠን ፣ በቂ በጀት አስቀድመው መያዝ እና ውል በመግባት ሀላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል።

ይህም ጥራታቸው የተጠበቀ መሠረታዊ መድኃኒቶች ያለመቆራረጥ እንዲቀርብ እና ለህብረተሰባችን ጤና ለማስጠበቅ የሚገኝ ውጤታማ ተልዕኮ ነው።

"የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት፣ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ፦ እንኳን ለ2018 ዓ.ም ጥምቀት በዓል በድጋሚ በሰላም አደረሳችሁ እያለ፣ይህ ዓመት የጤና፣ የብልግና እና የአዲስ ስኬት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን ።"

ማገልገል ክብር ነው!!

ለመሠረታዊ የህክምና ግብአቾች አቅርቦት፣

"የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ። "

እንኳን ለ2018 ዓ.ም የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የጤና እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን።የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (EPSS) #ማገልገል ክ...
17/01/2026

እንኳን ለ2018 ዓ.ም የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የጤና እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (EPSS)
#ማገልገል ክብር ነው!!!

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት  ፤ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮችና ለደንበኞቹ በሙሉ፦እንኳን ለ2018 ዓ.ም  #የገና  #በዓል በሰላም አደረሳችሁ!በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የ...
06/01/2026

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ፤ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮችና ለደንበኞቹ በሙሉ፦

እንኳን ለ2018 ዓ.ም #የገና #በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የደስታ እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን።

#ለመሠረታዊ የህክምና ግብአቾች አቅርቦት:
#የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ።

#ማገልገል ክብር ነው!!

Address

9. 046572, 38. 728670
Addis Ababa

Telephone

+251112763276

Website

https://t.me/epsaethiopia2012

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram