Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS

Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS, 9. 046572, 38. 728670, Addis Ababa.

Ethiopian Pharmaceutical Supply service , EPSS
, procure ,manage and distribute RDF & Heath Programme Products for governmental health facilities to supply quality assured essential pharmaceutical with affordable prices & a sustainable manner in Eth

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሽሬ ቅርንጫፍ ሠራተኛን ማዕከል ያደረገ የሕፃናት ማቆያ አስመረቀ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሽሬ ቅርንጫፍ፣ የ...
12/05/2026

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሽሬ ቅርንጫፍ ሠራተኛን ማዕከል ያደረገ የሕፃናት ማቆያ አስመረቀ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሽሬ ቅርንጫፍ፣ የሠራተኞችን የሥራ ጫና በማቃለል ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ያስገነባውን የሕፃናት የቀን ማቆያ ክፍል በይፋ ሠሞኑን ማስመረቁን የአገልግሎቱ ሽሬ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ሙልየ አብርሃ ተናገሩ።

የማቆያው ዋና ዋና ጥቅሞች

✅እናቶች ልጆቻቸው በአቅራቢያቸውና አስተማማኝ ቦታ መሆናቸውን በመተማመን ሙሉ ትኩረታቸውን ለሥራቸው እንዲሰጡ ያስችላል።

✅ በሠራተኞች ላይ ሊፈጠር የሚችለውን የስነ-ልቦና ጫና በመቀነስ የሥራ ተነሳሽነትን ከፍ ያደርጋል።

✅ ሰራተኞች በስራቸው ላይ እንዲያተኩሩ በማድረግ የቅርንጫፉን የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት እና ፍጥነት ያሻሽላል።

በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙት የሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ አለምጸሐይ ዳታ፤ የሕፃናት ማቆያው መገንባት ሴቶችን ከማብቃት እና የሥርዓተ-ፆታ እኩልነትን ከማረጋገጥ ባሻገር የሕፃናት ደህንነትና መብቶች ተጠብቀው እንዲያድጉ የላቀ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

በመርሃ-ግብሩ ላይ የሰሜን ምዕራብ ዞን አስተዳደር፣ የሽሬ ከተማ ከንቲባ፣ የመዘጋጃ ቤት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊዎች፣ የከተማው አፈ-ጉባኤ፣ የምክር ቤት ተወካዮች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።

ማገልገል ክብር ነው!

የሀዘን መግለጫ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨በኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (ኢመአአ) የድሬዳዋ ቅርንጫፍ የስራ ባልደረባችን የነበሩት አቶ ጌታቸው ከበደ ወልደዮሀንስ ባደረባቸው ህመም በህክምና ...
12/05/2026

የሀዘን መግለጫ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (ኢመአአ) የድሬዳዋ ቅርንጫፍ የስራ ባልደረባችን የነበሩት አቶ ጌታቸው ከበደ ወልደዮሀንስ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው፣ በ58 ዓመታቸው ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ላይ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

አቶ ጌታቸው በድሬዳዋ ቅርንጫፍ በሹፌርነት በሰሩባቸው ዓመታት ሁሉ ሙያቸውን በቅንነትና በትጋት ያገለገሉ፣ "ደከመኝ ሰለቸኝ" የማያውቁ ብቁ ሰራተኛ ነበሩ።

ላሳዩት የላቀ የስራ አፈጻጸምም በተለያዩ ጊዜያት የዕውቅና ተሸላሚ መሆናቸው ይታወሳል። በግል ህይወታቸውም ባለትዳርና የሁለት ሴት እንዲሁም የሁለት ወንድ ልጆች አባት ነበሩ።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በአቶ ጌታቸው ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለሥራ ጓደኞቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ ከ9.4 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባቸውን የህፃናት ማቆያ ማዕከል እና የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት መርቆ አገ...
11/05/2026

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ ከ9.4 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባቸውን የህፃናት ማቆያ ማዕከል እና የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት መርቆ አገልግሎት ላይ አዋለ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በምረቃ ስነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ እንደገለጹት፤ ተቋሙ የአገልግሎት አሰጣጡን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ከማዘመን ባለፈ፣ የሰራተኞቹንና የህዝብን የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ እያከናወነ ያለው ተግባር አርአያነት ያለው ነው። አዲሱ የህፃናት ማቆያ ማዕከል በተለይም ለሰራተኛ እናቶች ምቹ የስራ አካባቢን እንደሚፈጥርና የተቋሙን የውሃ ችግር በዘላቂነት እንደሚቀርፍም አክለዋል።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ አካቶ ትግበራ ዳይሬክተር ወ/ሮ አለምፀሀይ ዳታ በበኩላቸው፤ ተቋሙ ለህፃናትና ለሴቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት መሰል ግንባታዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ሀገር 19 ቅርንጫፎች ያሉት ይህ ተቋም፤ እንደ ወባ፣ ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ እና ቲቢ ያሉ መድኃኒቶችን ለጤና ተቋማት በነፃ እያከፋፈለ ይገኛል።

ወ/ሮ አለምፀሀይ አክለውም፣ የመድኃኒት አቅርቦቱን 100 በመቶ ለማድረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑንና የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎችም ጭምር በቻርተር አውሮፕላን በመታገዝ የህክምና ግብዓቶችን ተደራሽ እያደረጉ መሆኑን አስታውቀዋል።

የጎንደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይሔይስ ስብሐት እንደተናገሩት፤ ቀደም ሲል የነበረው የህፃናት ማቆያ ለህፃናት ምቾት የማይሰጥ በቆርቆሮ የተገነባ ነበር። አሁን የተገነባው ዘመናዊ ማዕከል ግን አጥቢ እናቶች ስራቸውን በተረጋጋ ሁኔታ እንዲያከናውኑ ትልቅ ፋይዳ አለው። በተጨማሪም የተቋሙን የውሃ ጥም ለመቅረፍ የከርሰ ምድር ውሃ ልማት መከናወኑን ገልጸዋል።

ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቱ በአሁኑ ወቅት ለ6 ዞኖች አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፤ በእጁም ከ837 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የህይወት አድን መድኃኒቶች ክምችት እንዳለውና ስርጭቱም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመድረኩ ተገልጿል።

አገልግሎቱ ከUSG SCS ፕሮጀክት በስትራቴጂካዊ አጋርነት ላይ ቴክኒካል ትብብር እና የአሰራር ድጋፍ ላይ ውይይት ተደረገ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት እና የአ...
09/05/2026

አገልግሎቱ ከUSG SCS ፕሮጀክት በስትራቴጂካዊ አጋርነት ላይ ቴክኒካል ትብብር እና የአሰራር ድጋፍ ላይ ውይይት ተደረገ

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት እና የአሜሪካ መንግስት አቅርቦት ሰንሰለት ማጠናከሪያ (SCS) ፕሮጄክት የኢትዮጵያን አገራዊ የጤና አጋርነት ኦፕሬሽን ቴክኒካል ትብብር፣ የቴክኒክ አጋርነት ትብብር ስርዓትን ለማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ የፕሮጀክት ልዑካን ቡድን ከፍተኛ አመራር እና የቴክኒክ ቡድን አባላትን ጨምሮ
ዋና አስተዳዳሪ በሆኑት በአቶ ኤድመአለም እጅጉ በተገኙበት ሰፊ ውይይት ተካሂዷል ።

የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ እንዳሉት ጠንካራ ፣ ቀልጣፋ እና ቀጣይነት ያለው የጤና ግብዓት አቅርቦት ሰንሰለት ስርዓት ለመገንባት ጠንካራ ተቋማዊ አጋርነት ያለውን ጠቀሜታ አጽንኦት ሰጥተው ፤ በመላ ሀገሪቱ አስፈላጊ የሆኑ የጤና ግብዓቶች ያለማቋረጥ ተደራሽ ለማድረግ የተቀናጀ ርብርብ ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል።

አቶ ኤድመአለም እጅጉ በትብብር ለመስራት የታቀዱ አካባቢዎችን ሰፋ ያለ መግለጫ ያቀረቡ ሲሆን ፤ ከቀረቡት አንኳር ጉዳዮች መካከል የ SCS ፕሮጀክትን ድጋፍ EPSS ቅድሚያ ከሚሰጣቸው እቅዶች ጋር መጣጣሙ ፣ ውጤታማ ትግበራና የሚለካ ውጤት ለማስመዝገብ ስትራቴጅካዊ ቁጥጥር መደረጉ ፣ የቴክኒክ ቅንጅት እና የአፈፃፀም ክትትልን የሚሸፍን የተዋቀረ የአስተዳደርና የቅንጅት ማዕቀፍም መዘጋጀቱ ፣ የሰው ሃይል ልማት ፣ እንዲሁም ERP ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ድጋፍ በሚደረግባቸው አንዳንድ የቴክኒክ ድጋፍ ዘርፎች ላይ ትኩረት የተሰጠባቸው ጉዳዮች ቀርበዋል ።

የአደጋ ጊዜ ምላሽ ስትራቴጂካዊ አስተዳደር ፣ አጋርነትና ቅንጅት የአቅርቦት ሰንሰለት ፣ ስጋት አስተዳደር እና ግብዐት የመገኘት ምጣኔ ፣ ስልታዊ ግዥ ትንበያ እና የተቀናጀ የብሔራዊ አቅርቦት እቅድ እና ተቋማዊ ብስለት በመጨመር የስርጭት ስርዓቶች እና የመጨረሻ ማይል አቅርቦት ማመቻቸት ቀዳሚ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ውይይት ተከናውኗል ።

የታቀዱት የድጋፍ ቦታዎች ከEPSS ስትራቴጂክ እቅድ ጋር ስላላቸው አግባብነት እና መጣጣም ያላቸውን አድናቆት ገልፀው ዶ/ር አብዱልቃድር ፤ ተቋማዊ ብስለትን እና የረዥም ጊዜ የስርአት አፈጻጸምን በሁሉም የስራ ደረጃዎች ለማስቀጠል የአቅርቦት ሰንሰለት የሰው ሃይል እና የአመራር ልማት ወሳኝ ምሰሶ መሆኑን አስምረውበታል።

የስብሰባው አላማ በEPSS እና በUSG SCS ፕሮጀክት መካከል ያለውን አጋርነት ለማረጋገጥ እንደ አስፈላጊ መድረክ ሆኖ ያገለገለ ሲሆን ፤ በአገር አቀፍ ደረጃ አስፈላጊ የሆኑ የጤና ምርቶች ወጥነት ያለው አቅርቦት እንዲኖር ሁለቱም ወገኖች ቅንጅታዊ አሰራርን ፣ ተቋማዊ አቅምን እና የአሰራር ቅልጥፍናን በማጠናከር ላይ ገንቢ ውይይት አድርገዋል።

# ማገልገል ክብር ነው!
ማኅሌት አበራ

06/05/2026

EPSS Wins Global “SMB Transformation Project of the Year 2025” Award

06/05/2026

EPSS Wins Global Digital Transformation Award as Pharmaceutical Sales Reach 11.5 Billion Birr

May 6, 2026

Ethiopian Pharmaceutical Supply Service has secured the “SMB Transformation Project of the Year” award at the 2025 ERP Today Awards, following a large-scale digital overhaul of Ethiopia’s pharmaceutical supply chain system.

The international recognition comes as EPSS reported 11.5 billion Birr in pharmaceutical sales to health facilities over the last nine months, reflecting a sharp increase in operational scale and procurement coordination across the public health sector.

The award recognizes organizations generating under one billion dollars in annual revenue that demonstrate measurable institutional and operational transformation through technology implementation.

The recognition was awarded for “Project SMILE,” a reform initiative that replaced fragmented manual processes with an integrated SAP S/4HANA platform linking procurement, warehousing, finance, inventory management, and distribution operations.

Speaking on the transformation, Dr. Abdulkedir Gelgelo, Director General of Ethiopian Pharmaceutical Supply Service, said the agency previously lacked a coordinated system to measure pharmaceutical demand and manage nationwide supply planning efficiently.

Additionally, Dr. Abdulkedir mentioned that the digital platform enabled EPSS and health facilities to implement a contract-based supply chain system that improved visibility over procurement needs, financing, and inventory flows.

He noted that EPSS’s annual procurement volume stood at around 3 billion Birr five years ago, while approved procurement financing later increased to approximately 8 billion Birr. Over the past nine months alone, however, the agency recorded 11.5 billion Birr in pharmaceutical sales to health facilities, excluding products currently in the procurement pipeline.

“For the first time, we are able to quantify aggregate pharmaceutical demand across health facilities nationally at around 24 billion Birr,” he said.

Officials say the integrated system has improved forecasting accuracy, reduced operational fragmentation, and strengthened medicine distribution efficiency across the public healthcare network.

The project was implemented with technical support from SEIDOR and Deloitte Consulting, while The Global Fund provided financial and strategic support.

The recognition comes as Ethiopia accelerates digital reform initiatives across public institutions under the Digital Ethiopia 2030 strategy, with growing emphasis on technology-led efficiency and institutional modernization.

Follow EBR for the latest business news, trends, and expert analysis:

Telegram (https://t.me/ebr_news)
Facebook (https://bit.ly/3OodjMF)
LinkedIn (https://lnkd.in/eAVk65Xv)
WhatsApp (https://bit.ly/4tH4NIR)

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የ “ERP Today Award”  ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ሽልማት አሸናፊ ሆነ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በ...
05/05/2026

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የ “ERP Today Award” ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ሽልማት አሸናፊ ሆነ

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በዓለም አቀፍ የኢንተርፕራይዝ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ከፍተኛ ክብር የሚሰጠውን የ2025 “ Transformation Project of the Year " The ERP today Award-Winner የአሸናፊነት ተሸላሚ ሆነ ።

ተቋሙ በዓለም አቀፍ የቢዝነስ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ከፍተኛ ስም ካላቸው ሽልማቶች አንዱ የሆነውን Transformation Project of the Year Award" አሸናፊ መሆን የቻለው በ2024 በሁሉም ቅርንጫፎች ከአንድ ቋት የሚነሳ የቴክኖሎጂ አሰራር “Project SMILE” SAP S/4HANA የተሰኘውን ዘመናዊ የቴክኖሎጂ የተቀናጀ የዲጂታል ለውጥ ስራውን በስኬት በማጠናቀቁ ነው።

አገልግሎቱ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስራውን ከመጀመሩ በፊት ባካሄደው ጥናት፣ 60% የሚሆኑት የሥራ ሂደቶች በእጅ (manual) የሚከናወኑና ለብክነት የተጋለጡ እንደነበሩ ተለይቷል። በተጨማሪም 42% የሚሆኑት አሰራሮች ለተቋሙ ምንም አይነት ተጨማሪ እሴት የማይጨምሩ (non-value add) ሆነው ተገኝተዋል።

ይህንን ተግዳሮት ለመፍታት የተዘረጋው የዲጂታል አሰራር የሚከተሉትን ዋና ዋና ውጤቶችን አስመዝግቧል

- የመረጃ ማዕከልነት (Single Source of Truth): ፋይናንስ፣ ግዥ፣ ክምችት፣ መጋዘን እና የሰው ኃይል አስተዳደርን በአንድ ማዕከላዊ የSAP አሰራር ስርዓት በመተግበር የተቀናጀ የሪፖርት ሥርዓት ተዘርግቷል።
- የቅጽበት ክትትል (Real-time Tracking)፦ የመድኃኒት ስርጭትን መከታተል የሚያስችል አቅም መፈጠሩ።
- ግልጽነትና ተጠያቂነት:- የታመነ የግዥ ስርዓት መዘረጋት ፣ የሃብት ብክነትን በመቀነስ የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለቱን ቀልጣፋና አስተማማኝ ደረጃ በማድረጉ ላይ​ ይገኛል ።

​ይህ ታላቅ ዓለም አቀፍ እውቅና የጤና ሚኒስቴር አመራር ቁርጠኝነት፣ የተቋሙ መላው አመራር እና ሰራተኞች ጥረት እንዲሁም የዓለም አቀፍ አጋሮች ( The Global Fund፣ SEIDOR እና Deloitte Consulting) በተቀናጀ የአጋርነት እና የጋራ ትብብር ውጤት ነው።

ይህ ስኬት ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የጀመረችው የዲጂታይዜሽን ጉዞ ማሳያ ከመሆኑም ባለፈ፣ለሀገራችን የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የጀርባ አጥንት ለሆነው 'Digital Ethiopia 2030' ስትራቴጂ የዲጂታል ልማት ግብ በተግባር ማሳያ ሆኖ ይቆጠራል ።

​የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (EPSS) ይህንን ሽልማት ማግኘቱ በአፍሪካ ቀዳሚና ዘመናዊ የመድኃኒት አቅርቦት ተቋም ለመሆን የሰነቀውን ራዕይ ለማሳካት ተጨማሪ ጉልበት እንደሚሆነው እና በቀጣይነት ያለሁ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ጥራቱን የጠበቀና የተቀላጠፈ የጤና አገልግሎት ግብዓት አቅርቦት ስርዓቱን በመዘረጋት ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ።

​ለተጨማሪ መረጃ፦
ዝርዝር መረጃዎችን የዓለም አቀፍ የሽልማት ድርጅቱ ድረ-ገጽ https://erp.today/erp-today-2025-awards-smb-transformation-project/ወይም በ LinkedIn http://erp.today ገፃችን በመጫን መረጃዎችን መከታተል ትችላላችሁ።

​"ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለተቀላጠፈ የጤና አገልግሎት!"

05/05/2026
አገልግሎቱ በጌትስ ግብረሰናይ ድርጅት ፈንድ የሚደረጉ አጋር አካላት ጋር ተወያየ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በጌትስ ግብረሰናይ ድርጅት ፈንድ የሚደረጉ አጋር ...
01/05/2026

አገልግሎቱ በጌትስ ግብረሰናይ ድርጅት ፈንድ የሚደረጉ አጋር አካላት ጋር ተወያየ

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በጌትስ ግብረሰናይ ድርጅት ፈንድ የሚደረጉ አጋር አካላት ጋር የተሰሩ ስራዎችና የገጠማቸው ተግዳሮቶች ፣ ለቀጣይ ያሉ እድሎችን ለአገልግሎቱ ለማቅረብ በመንግስት በኩል የተሰጠ አዲስ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ ካለ እንዴት በቀጣይ ስራዎች ላይ ማካተት እንደሚቻል ተወያይቷል ።

በውይይቱ ላይ ከተነሱ ጉዳዮች መካከል የአቅርቦት ሰንሰለቱን ዘመናዊ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት ላይ ያበረከቱት አስተዋፅኦ ምን እንደሚመስል ፣ የመረጃ ጥራትን ማሻሻል ፣ የዲጂታላይዜሽን መሰረት ልማት ግንባታ ፣ በአቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ ያሉ ክፍተቶችን በመለየት የመፍትሔ አቅጣጫ ማስቀመጥ ፣ የሰው ሀብት አቅምን ማጎልበት ፣ ከፆታ እኩልነት አንፃር የተከናወነው ተግባራት ፣ የቀዝቃዛ ሰንሰለት አስተዳደር ማዘመን ፣ የመገኘት ምጣኔን ለመከታተል የሚያስችል አሰራር መዘርጋት ፣ የሀገር ውስጥ አምራቾች አፈፃፀም ለማሻሻል የሚከናወኑ ተግባራት በዋነኝነት ይጠቀሳሉ ።

የአቅርቦት ሰንሰለት ላይ የጌትስ ፋውንዴሽን ያበረከተው አስተዋፅኦ በተለያየ መንገድ በርካታ መሆኑን አንስተው የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ ፤ በቀጣይ ዲጂታላይዜሽን በማጠናከር ህብረተሰቡ አገልግሎትን በራሱ የሚያገኝበት መንገድ መፍጠር መንግስት ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ በመሆኑ ይህንን የግብዓት አቅርቦቱ ዘርፍ ለማሳካት ትኩረት ተሰጥተው መስራት እንደሚገባ አቅጣጫ ተሰጥተዋል ።

በጌትስ ግብረሰናይ ድርጅት ከፍተኛ የፕሮግራም ኦፊሰር ዶ/ር ቃልኪዳን ላቀው ተናግረው ውይይቱ የተሰሩ ስራዎችን ላይ ለመነጋገር ጥሩ እድል እንደፈጠረ ገልፀው ፤ ለቀጣይ የተሰጠው አቅጣጫ በመውሰድ ለማከናወን ጥረት እንደሚያደረግ ተናግረዋል ።

በመጨረሻም የአዲሱን ህንፃ ጉብኝት አድርገዋል ።

የህክምና ግብዓት አቅራቢዎች የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና መስሪያ ቤትን ጎበኙ፨፨፨፨፨፨የህክምና ግብዓት አቅራቢዎች የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (EPSS) ዋና መስሪ...
30/04/2026

የህክምና ግብዓት አቅራቢዎች የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ዋና መስሪያ ቤትን ጎበኙ
፨፨፨፨፨፨
የህክምና ግብዓት አቅራቢዎች የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (EPSS) ዋና መስሪያ ቤትን ሚያዝያ 21 ቀን 2018ዓ.ም ጎብኝተዋል።

የጉብኝቱ ዋና ዓላማ ተቋሙ በመድኃኒት እና ህክምና ግብዓት አቅርቦት ላይ እያከናወነ ያለውን ስራ ለማየትና የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከር ሲሆን ፤ በጉብኝቱ ወቅት ተቋሙ የጀመረውን ዘመናዊ የግዥ ሂደት እና በውል ላይ የተመሰረተ የአቅርቦት ስርዓት ወደ ስራ መግባቱ በዝርዝር ቀርቧል።

የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ አቅናው ካውዛ በዚህ አጋጣሚ እንደገለፁት፣ የጤና ተቋማትን በበቂ ደረጃ መድኃኒት እንዲያገኙ ማድረግ የተቋሙ ቀዳሚ ተልዕኮ መሆኑን ገልፀዋል። በዚህም የመጋዘን አያያዝን ማዘመን፣ የሎጂስቲክስ ስርዓትን ማሻሻል እና ከአቅራቢዎች ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።

ም/ዋና ዳይሬክተሩ ተቋሙ በርካታ የሪፎርም ስራዎችን እየፈጸመ እንደሆነ አስታዉሰዉ ፣ የመድኃኒት እጥረት እንዳይኖር በሁሉም ተጠቃሚ አካላት መካከል የተቀናጀ ስራ መኖሩ አማራጭ የሌለው መሆኑን ገልፀዋል።

አቅራቢዎችም በተቋሙ የተጀመሩ ለውጦች ላይ አድናቆታቸዉን የሰጡ ሲሆን፣ በቀጣይ ጊዜም ከተቋሙ ጋር በተቀናጀ መልኩ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን አሳዉቀዋል።

ጉብኝቱ በአጠቃላይ የመድኃኒት አቅርቦትን ለማሻሻል በመካከለኛና በረዥም ጊዜ የሚያገለግሉ ትብብሮችን ለማጠናከር ጠቃሚ መድረክ እንደሆነ ተገልጿል።

#ማገልገል ክብር ነዉ
አማኑኤል ወርቃየሁ

29/04/2026

🇪🇹 የመጋዘን እና የስርጭት ሥርዓታችንን ዲጂታላይዝ እያደረግን ነው –የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት

አገልግሎ፣ የክምችት መጋዘኖቹንና የመድኃኒት ሥርጭት ሥርዓቱን ወደ ዲጂታል የመቀየር ሰፊ ሥራ እያከናወነ መሆኑን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር አብዱልቃድር ገልገሎ (ዶ/ር) ከ5ኛው ዓለም አቀፍ የመድኃኒት አቅራቢዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

💻 ተቋሙ ከኤሌክትሮኒክ የመንግሥት ግዥ ሥርዓት በተጨማሪ፣ ሁሉንም 19 ቅርንጫፎቹን እርስ በእርስ የሚያገናኝ የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒንግ (ERP) የቴክኖሎጂ ሥርዓት እየተገበረ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

📹 ዋና ዳይሬክተሩ የዲጂታል ሥርዓቱን ፋይዳን በተመለከተ የሰጡትን ማብራሪያ ከቪዲዮው ይመልከቱ፡፡

✅ ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | 📲 መተግበሪያ | 👉 X

Address

9. 046572, 38. 728670
Addis Ababa

Telephone

+251112763276

Website

https://t.me/epsaethiopia2012

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS:

Share