
29/07/2025
"የሀዘን መግለጫ"
⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳
የቅርንጫፋችን የስራ ባልደረባ የነበሩት ወ/ሮ የኔነሽ አያሌው ከየካቲት 20 ቀን 2005 ዓ.ም እስከ ህይወታቸው ህልፈት ድረስ በመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት አዳማ ቅርንጫፍ የፋይናንስ ባለሙያ በመሆን ሲያገለግሉ ቆይተዋል።
ወ/ሮ የኔነሽ አያሌው ባለትዳር እና የሁለት ሴትና የአንድ ወንድ ልጅ እናትም ነበሩ፤
ይሁን እንጂ ወ/ሮ የኔነሽ አያሌው ባጋጠማቸው ድንገተኛ ህመም ምክንያት በተወለዱ በ44 አመታቸው ሐምሌ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል።
ለቤተሰቦቻቸው፤ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለስራ ባልደረቦቻቸው ሁሉ መፅናናቱን እንመኛለን።