07/02/2025
ሰሚ ካለ‼️
ከ3 ወራት በላይ አልፈዋል፣ አሁንም 159 ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በአክሱም ትግራይ፣ በሒጃባቸው ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ ተደርገዋል፤ የመማር መብት ተነፍገዋል። ምንም እንኳን የትምህርት ሚኒስቴር መመሪያ ሒጃብ ለብሶ መማርን ቢፈቅድም የአክሱም ሙስሊም ሴቶች ሒጃብ ለብሰው መማር ተከልከለዋል። በአገሪቱ ካሉ ትምህርት ቤቶች በተለየ አክሱም ሒጃብ ከልክላለች።
ይህ ሲሆን Ministry of Education Ethiopia እና እና የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር Ministry of Women and Social Affairs ዝምታ መርጠዋል። Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council (የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትም) ደብዳቤ ከመፃፍ የዘለለ የሰራው ስራ አናውቅም።
የነዚህ ልጆች ከትምህርት ገበታ ውጪ መደረግ ከባድ የመብት ጥሰት ነው፤ ብዙ እንድምታዎች አሉት። ከምንም በላይ ተማሪዎቹ እንደ ዜጋ የመብት ጥሰት ሲፈፀምባቸው የሚደርስላቸው አካል በማጣታቸው በአገር፣ በሕግ እና በወገን የነበራቸውን እምነት እንዲሸረሸር አድርጎታል። እነዚህ ልጆች በክልል እና በወረዳ አስተዳደሮች የመብት ጥሰት መብት ሲፈፀምባቸው የትምህርት ሚኒስቴር፣ የሴቶች እና ማሕበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር እንዲሁም በፌደራሉ መጅሊስ የነበራቸውን ወይም ሊኖረቸው ይችል የነበረው እምነት እንዲያጡ ተደረገዋል። አንገታቸውን እንዲደፉ ተደርገዋል። የመማር መብታቸው ተነፍጎ ሊደርስላቸው የሚችል አካል እንደሌለ አይተዋል። ያሳዝናል።
159 ሙስሊም ሴት ተማሪዎች እምነታቸውን ያዘዛቸው ሒጃብ በመልበሳቸው ከትምህርት ገበታ ውጪ ሲደረጉ ምንም አለማድርጋችን ያበሳጫል። እነዚህ ልጆች ሒጃብ በመልበሳቸው ሲባረሩ ምንም ያላደረገ ወይም ያለለ ኢማም/ዳዒ እንዴት ብሎ ነው አፉን ሞልቶ ስለ ሒጃብ ኢስላማዊ ግዴታነት ዳዕዋ የሚያደርገው? 159 ሴቶች ከትምህርት ገበታ ውጪ ሲደረጉ ምንም ያላደረገ የሴቶች ሚኒስቴር በምን ሞራል ነው አንዲትም ሴት ከትምህርት መቅረት የለባትም የሚለው? 159 ሴቶች ከትምህርት ገበታ ውጪ ሲደረጉ ምንም ያላደረገ ትምህርት ሚኒስቴር በምን ሞራል ነው ሴቶችን የማከለ እና አካታች የትምህርት ስርዓት ነው የምከተለው ማለት የሚችለው?
Hagos
of education Ethiopiacation Ethiopiaducation Ethiopia