Ethiopian Health professionals

Ethiopian Health professionals Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Health professionals, Medical and health, Addis Ababa.

Break silence and liberate Ethiopian health system ,we health professionals need fair wage, house allowance ,duty payment,medical insurance ,risk payment ,work env't safety

===በጣም ያሳዝናል‼️====🗯በቃላት ደረጃ እንኳ መልስ ከሰጡን ብዬ ሙሉ ቪዲዮውን ተመለከትኩት። ቅስም በሚሰብር ሁኔታ ባለሙያዎች የጠየቁትን ጥያቄ ትተው ስለ ሌላ ጉዳይ ሲያወሩ፣  ጊዜው አ...
23/06/2025

===በጣም ያሳዝናል‼️====

🗯በቃላት ደረጃ እንኳ መልስ ከሰጡን ብዬ ሙሉ ቪዲዮውን ተመለከትኩት። ቅስም በሚሰብር ሁኔታ ባለሙያዎች የጠየቁትን ጥያቄ ትተው ስለ ሌላ ጉዳይ ሲያወሩ፣ ጊዜው አለቀ። ክፍል ሁለት ቢኖረው ብዬ ተመኘው።

⚓️አንዳንድ ቦታ ላይ የሚያሳዝኑ ንግግሮች ሁላ ነበሩ። ከነዚህም ውስጥ፦

📌1ኛ፦ "እኔ እና እናንተ ለቀጣይ 15 - 20 ዓመታት ቀበቷችንን ጠበቅ አድርገን ለጊዜውም ቢሆን እንቸገር፣ እኛ ባያልፍልን እንኳ ልጆቻችን ያልፍላቸዋል" ሲሉ ይደመጣሉ።

💥እኛ የጤና ባለሙያዎች ራበኝ፣ ታረዝኩ፣ ልጆቼን ማስተዳደር፣ ማስተማር አልቻልኩም ያልነው እንደት ብለን ቀበቷችንን እናጥብቅ? ረሀብ 20 ዓመት ይጠብቀናል? ልጆቻችን ምን በልተው አድገው ፣ እንዴት ተምረው ነው ወደፊት ጥሩ ኑሮ የሚኖሩት?

💥እርስዎንና እኛን እኩል ቀበቷችንን ጠበቅ እናድርግ ሲሉ እርሱዎ ተርበዋል? ታርዘዋል? ልጅ ለማሳደግ ተቸግረዋል? የዕውነት በጣም ያሳዝናል።

📌ሌላኛው ደግሞ " የትኛውም የአፍሪካ ሀገር የኢትዮጵያ መንግሰትን ያህል ለጤና ሴክተር የበጀት ድጋፍ አያደርግም" የሚለው ነው።

💥እንግዲህ ሚጢጢዬዋ ሩዋንዳ አንድ ሆስፒታል ለማደስ ፤ ለመስራት ሳይሆን ለማደስ፤ 250 ሚሊዮን ዶላር ትመድባለች።
በ 2024/25 እንኳ 462 ቢሊየን ዶላር ለጤና ዘርፍ መድባለች -just ለ 14.5 ሚሊየን ህዝብ ( 2025 Data)።

🗯ይህ ማለት ሩዋንዳ ለአንድ ሆስፒታል ማደሻ ብላ የምትበጅተው ገንዘብ Almost ለእኛ ለጤናው ዘርፍ ከሚማደበው በጀት ጋር እኩል ነው -- 130 ሚሊዮን ህዝብ ይዘን።

🗯 ራበኝ ብዬ ስጠይቅ፣ ጋዎን የለበስክ ፖለቲከኛ ነህ የሚል ማሸማቀቂያ ከተሰጠኝ፤ ብዙ ተስፋ ያደረኩበት የጠቅላይ ሚንስትሩ ስብሰባ በዚህ መልኩ ከተደመደመ ከዚህ በኋላ ተስፋዬ ማነው⁉️

Henok Abraham

የህክምና ባለሞያዎች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር ሰኔ 14/2017 ባካሄዱት ውይይት ላይ የተነሱ በአራት ዘርፍ የተደራጁ ጥያቄዎች
22/06/2025

የህክምና ባለሞያዎች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር ሰኔ 14/2017 ባካሄዱት ውይይት ላይ የተነሱ በአራት ዘርፍ የተደራጁ ጥያቄዎች

ለአዳዲስ ና ለቪዲዮ መረጃዎች youtube ቻናላችን subscribe ያድርጉ👇🏻👇🏻
22/06/2025

ለአዳዲስ ና ለቪዲዮ መረጃዎች youtube ቻናላችን subscribe ያድርጉ👇🏻👇🏻

Fair wage ,working environment safety ,house allowance ,risk payment ,respect for Ethiopian health professionals Professionals and profession must be respected 💪💪💪

21/06/2025

ለጤና ባለሙያዎች ጥያቄ ተገቢውን ; ወቅትን የዋጀ መልስ መሰጠት አዲስ ለምመጣው ትውልድ ተስፋም ጭምር ነው
ባለሙያዎች የሚያቀርቡት ጥያቄ ለዚህ ትውልድ እና ለሚመጣው ትውልድ ተስፋም ነው
ባለመመለስ የምከሰት የጤና ስርዓቱ ውድቀት ለመታደግ የተጣለ ሀላፊነትም ጭምር ነዉ::

Ethiopian Health professionals

21/06/2025

ስብሰባው ተጠናቋል። የተገቡት ቃሎች ይፈፀሙ አይፈፀሙ የምናየው ይሆናል። ጤና ባለሙያውን የሚያሳፍር ውዳሴ ሲያዥጎደጉዱ የዋሉ እንደነበሩም ታዝበናል። ብዙ ውሸቶች የተንፀባረቁበትም ነበር። ስድብ እና ንቀት በተወሰነ መልኩ እንደበፊቱ እንዳልነበረም ሰምተናል። የተብራራው የውይይቱን ይዘት ይዘን የምንመለስ ይሆናል።

ሆኖም ውይይቱ ጤና ባለሙያውን እንደማይወክል እና በ 2ወር ጊዜ ውስጥ ለህልውና ጥያቄያችን ተጨባጭ መልስ እንዲሰጠን አበክረን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ እናሰራጭ፤ እናሳውቅ።

አንድነት ሀይል ነው።

🤔🤔By the time it 's edited and released, we might need a recap of what it even was Today's session with regional health ...
21/06/2025

🤔🤔By the time it 's edited and released, we might need a recap of what it even was
Today's session with regional health bearue cadres

21/06/2025

an Ethiopian

የኢትዮጵያ ህክምና ባለሙያዎች የEthiopia Brightest mind ያላቸው እድሉን ቢያገኙ የትም አለም ላይ compete አድርገው መስራት የሚችሉ ናቸው። Infact አቅም እና እድል አግኝተው እንደ USMLE ያሉ International Medical licencing ፈተናዎችን የሚፈተኑት በብቃት እያለፉ የሌሎች ሀገራትን የህክምና ባለሙያዎች outperform ጭምር የሚያደርጉ እንቁዎች ናቸው። በእጃችን ስላሉ አይቅለሉብን። ይሄ ሁሉ አመት ተምረው ለፍተው በየከተማ እና ገጠሩ ቀን ከለሊት እየለፉ እየሰሩ ራበን ሲሉ ያማል። ያበሳጫል። Imagine የስንቶቻችን እናት, አባት, እህት, ወንድም, ባል, ሚስት በነሱ ምክንያት እንደተረፉ? ሆዳችንን ጭንቅላታችንን ልባችንን ቀደው የሚያክሙን እነሱ ናቸው። ይሄን ማድረግ የሚፈልገውን ግዜ እና ልፋት አስቡት...... እና እነዚህ ሰዎች ራበን ሲሉ ከዚህ በላይ ምን መውረድ አለ?

የዛሬ እነሱን እያዩ የአሁን ልጆች ትምህርት ምን ያደርጋል እያሉ ነው። ሀገሪቷ የመሀይሞች ጥርቅም እየሆነች ነው።

የነዚህ ህክምና ባለሙያዎች ጥያቄ እንደ እነሱ ጥያቄ ብቻ የሚታይ መሆን የለበትም። ሀገራችን የደረሰችበትን ደረጃ የሚያሳይ ነው። የህክምና ባለሙያዎች እንቁዎቻችን ናችሁ:: You guys deserve much better! ♥️

 #ኢትዮጵያ በኑሮ ውድነት ከ  #አፍሪካ ቀዳሚ ደረጃ መያዟን ሪፖርት አመላከተኢትዮጵያ ለመኖር እጅግ ውድ ከሆኑ የአፍሪካ ሀገሮች መካከል ቀዳሚ ደረጃ ስትይዝ ከዓለም 53ኛ ደረጃ ላይ መቀመጧ...
19/06/2025

#ኢትዮጵያ በኑሮ ውድነት ከ #አፍሪካ ቀዳሚ ደረጃ መያዟን ሪፖርት አመላከተ

ኢትዮጵያ ለመኖር እጅግ ውድ ከሆኑ የአፍሪካ ሀገሮች መካከል ቀዳሚ ደረጃ ስትይዝ ከዓለም 53ኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ሪፖርት አመላከተ።

የዓለማችን ትልቁ የኑሮ ውድነት የመረጃ ቋት ባወጣው አዲስ ሪፖርት እንዳስታወቀው፤ ኢትዮጵያውያን አሁን ላይ እንደ ምግብ እና ትራንስፖርት ባሉ መሰረታዊ ነገሮች ላይ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ዜጎች የበለጠ ገንዘባቸውን ያወጣሉ።

በሪፖርቱ መሰረት፣ በኑሮ ውድነት ኢትዮጵያ ከዓለም 53ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠችው 46.5 የኑሮ ውድነት ጠቋሚ ነጥብ በመስመዝገብ ሲሆን፣ ይህም አፍሪካ ውስጥ ካሉ አገሮች ሁሉ ከፍተኛው ነው።

በሀገሪቱ የሚታየው የሸቀጦች ዋጋ መወደድ በኑሮ ውድነት ደረጃ አንደኛ እንድትሆን ምክንያት መሆኑ ተገልጿል። ይህም በተለይ በቋሚ ወይም በዝቅተኛ ገቢ የሚኖሩ ሰዎች ሳምንታዊ ወጪያቸውን ለመሸፈን እየከበዳቸው መምጣቱን የሚያሳይ ነው መባሉን ኤፒኤ ኒውስ ዘግቧል።

#አዲስ ስታንዳርድ

  FROM TIGRAY INTERIM ADMINISTRATION FOR TIGRAY HEALTH PROFESSIONALSየትግራይ ግዚያው ኣስተዳዳደር  ፕሬዝዳንት ታደሰ ወረደ(ሌተነል ጀነራል) በጤና ባለ...
18/06/2025

FROM TIGRAY INTERIM ADMINISTRATION
FOR TIGRAY HEALTH PROFESSIONALS

የትግራይ ግዚያው ኣስተዳዳደር ፕሬዝዳንት ታደሰ ወረደ(ሌተነል ጀነራል) በጤና ባለሙያዎች ዙርያ የተነሱ ጥያቄዎች እውቅና በመስጠት ክልሉ በሚችላው አቅም ለመፍታት ለሚመልከታች መስራ ቤቶች እንዲፈፀም በሚል ለ16 ጥያቄዎች ምላሽ እና መፍትሄ ኣስቀምጧል።እነዚህም
1-እውቅና-የጤና ባለ ሙያዎች -ኣርበኛ ናቸው።የእውቅና መድረክ ተዘጋጆቶ እውቅና ይሰጣቸዋል።
2-የመኖርያ ቤት-መሬት ይሰጣቸው መስርያው ደሞ የትግራይ ጤና ቤሮ ከፋይናንስ ተቋማት ብድር እንዲያመቻች።
3-ለግል ሆስፒታል እና ክሊኒክ የሚሆን መስርያ ቦታ-ተደራጅቶ ለመጡ እና መስፈርቱ ላማሉ በሊዝ ዋጋ እንዲሰጠ፣ነፃ ቀረጥ እና ብደር እንዲመቻችላቸው።
4-መኪና-የኤሌክትሪክ መኪና ከፌደራል ጋር በመነጋገር tax free እንዲመቻች,መኪና ያላቸው ደሞ ነዳጅ ቅደሚያ እንዲሰጣቸው።
5,6,7,፣ነፃ ህክምና ፣የህግ ከለላ፣ሆስፒታል ውስጥ የህፃናት መቆያ እንዲዘጋጅ
8-የDuty ክፍያ መምርያ እንዲስተካከል።ተረኛ የሆስፒታል መኪና እንዲጠቀም
16-ደሞዝ ጭማሪ-ፌደራል የሚመለከት ጥያቄ ነው።

18/06/2025

Just for the sake of fun 🤔🤔
Put your answer
If all humans suddenly lost the ability to lie, what occupation would collapse first

18/06/2025

Free him now without any preconditions

⚓በጣም ዘግይቶ በደረሠን ዜና✋ገጣሚ ዘውድ አክሊል ከታሰሩት ሀኪሞች ጋር አብሮ ታስሮ ነበር። አብዛኛው የጤና ባለሙያ/ሀኪሞች ሲፈቱ እሱ ግን እንዳልተፈታ ያለን መረጃ ያሳያል።ገጣሚ ዘውድ አክ...
18/06/2025

⚓በጣም ዘግይቶ በደረሠን ዜና

✋ገጣሚ ዘውድ አክሊል ከታሰሩት ሀኪሞች ጋር አብሮ ታስሮ ነበር። አብዛኛው የጤና ባለሙያ/ሀኪሞች ሲፈቱ እሱ ግን እንዳልተፈታ ያለን መረጃ ያሳያል።

ገጣሚ ዘውድ አክሊል "እኔም ዶ/ር ነኝ" በሚለው ግጥሙ ለጤና ባለሙያዎች አጋርነቱን ማሳየቱ የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው።

Address

Addis Ababa

Website

https://www.youtube.com/@EthiopiaHealthprofessionals

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Health professionals posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram