Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ

Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ Disease prevention and control
Maternal and child health
Nutrition
Health care financing

የሀዘን መግለጫ‎‎በጋሞ ዞን ቦረዳ ወረዳ በጋጋ ጎቾ ጤና ጣቢያ በሂሳብ ሰራተኝንት ያገለግሉ የነበሩት አቶ አክሊሉ አበበ ባደረባቸው ህመም በህክምና ስረዱ ቆይትው ጥቅምት 29/2018 ዓ.ም ከ...
09/11/2025

የሀዘን መግለጫ

‎በጋሞ ዞን ቦረዳ ወረዳ በጋጋ ጎቾ ጤና ጣቢያ በሂሳብ ሰራተኝንት ያገለግሉ የነበሩት አቶ አክሊሉ አበበ ባደረባቸው ህመም በህክምና ስረዱ ቆይትው ጥቅምት 29/2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

‎የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ሰራተኞች በባለሙያው ህልፈተ–ህይወት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን በመግለፅ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለሥራ ባልደረቦቹ መፅናናት ተመኝተዋል።

የጨንቻ ሆስፒታል በአቅራብያዉ በምገኙ 5 ጤና ጣብያዎች አስፈላጊዉን ድጋፍ በማድረግ የኦክሲጅን ህክምና በጤና ጣብያ ደረጃ ማስጀመሩ ተገለፀ።‎                        ‎በኦክሲጅን...
08/11/2025

የጨንቻ ሆስፒታል በአቅራብያዉ በምገኙ 5 ጤና ጣብያዎች አስፈላጊዉን ድጋፍ በማድረግ የኦክሲጅን ህክምና በጤና ጣብያ ደረጃ ማስጀመሩ ተገለፀ።

‎በኦክሲጅን መድሃኒት ህክምና ዙርያ በጨንቻ ሆስፒታል ድጋፍና ክትትል ከክልል ጤና ቢሮ ;ከጋሞ ዞን ጤና መምሪያ እና ቻይ (CHAI) ከተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት ለሁለት ተከታታይ ቀናት የተካሄደ ሲሆን ሆስፒታሉ በኦክስጂን መድሃኒት ህክምና ከፍተኛ ለዉጦችን ማስመዝገብ መቻሉ ተገልጿል ።

‎ሆስፒታሉ በኦክሲጅን ህክምና እና በመረጃ አያያዝ ሰፊ መሻሻሎችን ማስመዝገቡን የገለፁት የቻይ ድርጅት ተጠሪ አቶ ሰይድ ሆስፒታሉ በአቅራብያ በምገኙ አምስት ጤና ጣብያዎች አስፈላጊዉን ድጋፍ በማድረግ አገልግሎቱ በጤና ጣብያዎችም እንድጀመር መደረጉ ሆስፒታሉ በኦክሲጅን መድሃኒት ዘርፍ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ወርደዉ ማረጋገጣቸዉን ገልጸዋል ።

‎ አቶ ሰይድ አክለዉ ሆስፒታሉን በኦክሲጅን ህክምና ዘርፍ የጀመራቸዉን በጎ ተግባራትን በማጠናከር ሞዴል ተቋም ለማድረግ ድርጅታቸዉ አስፈላጊዉን ድጋፍ ሁሉ እንደምያደርግ ገልፀዋል።

‎ከጋሞ ዞን ጤና መምሪያ በድጋፍና ክትትል ወቅት የተገኙት አቶ አብዮት እንደገለፁት የጨንቻ ሆስፒታል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከፍተኛ ለዉጦችን እያስመዘገበ መሆኑን ገልፀዉ በኦክሲጅን መድሃኒት ህክምና ሆስፒታሉ ጤና ጣብያዎችን በማብቃት ጭምር ሰፋፊ ስራዎችን እየሰራ መሆኑት በተግባር ማየታቸዉን ገልፀው የዞኑ ጤና መምርያ የኦክሲጅን ህክምናን ከዝህም በላቀ ለማሳደግ በቅርበት ድጋፍ እንደምያደርግ ገልፀዋል።

‎ የሆስፒታሉ ስራ አስክያጅ አቶ ዘላለም ዘዉዱ እንደገለፁት የኦክሲጅን መድሃኒት ህክምናን ከቀድሞ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሳደግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው ለዝህም የሆስፒታል ጤና ጣብያዎች ተናበዉና ተቀናጅተዉ እየሰሩ መሆናቸዉ ለዉጤቱ መገኘት ትልቁን ድርሻ እንደምይዝ ገልፀዉ ቻይ ድርጅት በቅርቡ ከፍተኛ ዋጋ ያላቸዉን ግብዓቶችን ለሆስፒታሉ ድጋፍ በማድረጉ አመስግነዉ በቀጣይም ድጋፋቸዉን አጠናክረዉ እንድቀጥሉ ጠይቀዋል።

የጡትና ማህፀን ጫፍ ካንሰር መቆጣጠርና መከላከል ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተጠቆመ ‎‎አምንጭ ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)‎‎የጡትና የማህፀን ጫፍ ካንሰር መቆጣጠር...
07/11/2025

የጡትና ማህፀን ጫፍ ካንሰር መቆጣጠርና መከላከል ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተጠቆመ

‎አምንጭ ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎የጡትና የማህፀን ጫፍ ካንሰር መቆጣጠርና መከላከል ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ ።

‎ቢሮው በጉዳዩ ዙሪያ በጂንካ ከተማ የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል ።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትልና የጤና ፕሮግራሞች ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ ተላላፊ ካልሆኑ በሽታዎች መካከል የጡት ካንሰር እና የማህፀን ጫፍ ካንሰር ዋነኞቹ መሆናቸውን ገልፀዋል።

‎የካንሰር በሽታ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶች ከፍተኛ መሆናቸውን አመልክተዋል፡፡

‎በቢሮው የበሽታ መከላከልና መቆጣጠርና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ክፍል ኃላፊ ሲስተር ትዕግስት ተሰማ በአገራችን በየአመቱ ከ7 ሺህ በላይ ሴቶች በማህፀን ጫፍ ካንሰር እንደሚያዙ መረጃዎች ይጠቁማሉ ብለዋል፡፡

‎የአርባምንጭ ከተማ ጤና ጽ/ቤት የበሽታ መከላከል አስተባባሪና የማህፀን በር ካንሰር መከላከል ክፍል ኃላፊ አቶ ዲኮርሳ ከበደ በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር አስቀድሞ ምርመራ ማድረግ ተገቢ መሆኑን ጠቁመዋል ።

‎በንቅናቄ መድረኩ የክልል ፣ የዞንና የከተማ ጤና ኃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የደረት ላይ ህመም (Chest Pain) – አደገኛ የልብ ድካም ምልክት ነው!!! ብዙ ሰዎች የደረት ህመም ወይም ጭምድድ አድርጎ የመያዝ ስሜት ለብዙ ጊዜያት አጋጥሟቸው ይሆናል፡፡ ይህ አይነት...
07/11/2025

የደረት ላይ ህመም (Chest Pain) – አደገኛ የልብ ድካም ምልክት ነው!!!

ብዙ ሰዎች የደረት ህመም ወይም ጭምድድ አድርጎ የመያዝ ስሜት ለብዙ ጊዜያት አጋጥሟቸው ይሆናል፡፡

ይህ አይነት ሁኔታ የተወሰኑ የሳንባ እና የልብ በሽታዎች የማስጠንቀቂያ ምልክት መሆኑን ያውቃሉ? እንዲሁም “የልብ ድካም – Heart Attack” ካሉት አደገኛ ምልክቶች አንዱ ነው፡፡

የልብ ድካም (Heart Attack) የደም ፍሰት ሲዘጋ የልብ ጡንቻዎች በበቂ ሁኔታ እንዳይሠሩ በማድረግ የሚከሰት በጣም ከባድ ድንገተኛ የጤና ችግር ነው፡፡

ህመምተኛው ህክምናውን በሰዓቱ ካላገኘ ወደ ድንገተኛ የልብ ድካም ወይም ወደ ሞት ያደርሳል፡፡

የሚከተሉት ምልክቶች ካስተዋሉ ወዲያውኑ ህክምና ማግኘት አለብዎት፡-

የደረት ህመም (Chest pain) እና / ወይም ጭምድድ ማድረግ(ታካሚው በትከሻቸው ፣ በአንገታቸው እና በመንጋጋቸው አካባቢም ህመም ሊኖረው ይችላል)

የደረት አጥንት ታችኛው ጫፍ ላይ በሚኖር ጉዳት ምክንያት የሚከሰት ህመም (Xiphoid process pain) ድካም እና ለመተንፈስ መቸገር ፤ ላብ እና ማቅለሽለሽ ፤ፈጣን የልብ ምት ፤ራስ ማዞር እና ራስን መሳት እንደ ምልክት ተጠቃሽ ናቸው።

ከ20-30 ደቂቃዎች እነዚህ ምልክቶች ይስተዋላሉ ነገር ግን ሁሉ ጊዜ ምልክቶች ካሉዎት የልብ ድካም (Heart Attack) ችግር ስለሚኖር ወዲያውኑ ህክምና ማግኘት ይኖርብዎታል፡፡

ምንም እንኳን አደገኛ በሽታ ቢሆንም ራስዎን በመጠበቅ መከላከል ይቻላል፡፡ ሰዎች ጥሩ ምግብ መመገብ፣ ተደጋጋሚ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና ዓመታዊ የጤና ምርመራ ማድረግ አለባቸው ፡፡

እንደ ስኳር በሽታ፣ የደም ግፊት፣ ከፍ ያለ ኮሌስትሮል፣ ወዘተ ያሉ ለችግሩ ተጋላጭ ሊያደርጉን የሚችሉ በሽታዎችን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወባ ስርጭት ለመቀነስ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ ገለፀ በክልሉ በ2018 የመጀመሪያ ሶስት ወራት የወባ በሽታ ስርጭት ለመቀነስ ጠንካራ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ...
06/11/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወባ ስርጭት ለመቀነስ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ ገለፀ

በክልሉ በ2018 የመጀመሪያ ሶስት ወራት የወባ በሽታ ስርጭት ለመቀነስ ጠንካራ ሥራ እየተሠራ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ ገልጿል፡፡

ቢሮው የክልሉን ወቅታዊ የወባ በሽታ ስርጭት ሁኔታን ከባለድርሻ አካላት ጋር በጂንካ ከተማ እየገመገመ ይገኛል፡፡

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ በዚህ በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ወባን ለመከላከል ርብርብ ተደርጓል፡፡

የአልጋ አጎበሮችን በማሰራጨትና ህብረተሰቡን በማሳተፍ የኬሚካል ርጭት በማድረግ የበሽታውን ስርጭት ለመቆጣጠር የተደረገውን ጥረት በአብነት ጠቅሰዋል፡፡

በሩብ አመቱ ከ785 ሺህ በላይ ሰዎችን የወባ ምርመራ ማድረጋቸውን ምክትል ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡

በተከናወኑ ተግባራት በክልሉ በወባ በሽታ የሚከሰተውን ህመምና የሞት መጠን ለመቀነስ እየተሠራ ነው ያሉት ምክትል ኃላፊው የታማሚዎችን ቁጥር 60 በመቶ ለመቀነስ ታቅዶ እየተመራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ባለድርሻ አካላት ለወባ በሽታ መከላከል ንቅናቄ የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል ሲሉም አቶ መና መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት ያከናወናቸውን ተግባራት  ከባለድርሻ አካለት ጋር በመሆን መገምገሙ ተነገረ፤አርባምንጭ፡ ጥቅምት 26/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤ...
05/11/2025

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ በበጀት ዓመቱ በመጀመሪያ ሩብ ዓመት ያከናወናቸውን ተግባራት ከባለድርሻ አካለት ጋር በመሆን መገምገሙ ተነገረ፤

አርባምንጭ፡ ጥቅምት 26/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ):

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ በበጀት ዓመቱ በሶስት ወራት ውስጥ በጤናው ዘርፍ የተከናወኑ አበይት ተግባራትን የዞኑ ጤና መምሪያ የማናጅመንት አባላት፣ አጠቃላይ የመምሪያው ሠራተኞች እና የአጋር ድርጅቶች ተወካዮች በተገኙበት በጥልቀት መገምገሙ ታወቋል፡፡

በዞኑ በለፉት ሶስት ወራት ውስጥ 10,569 እናቶች በሠለጠነ ባለሙያ የወሊድ አገልግሎት አግኝተዋል፣ አድሜያቸው በመውለድ ክልል ውስጥ ለሚገኙ 46,250 ሴቶች የቤቴሰብ ዕቅድ አገልግሎት አንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል፣ 15,752 ነፍሰጡር እናቶች የመጀመሪያ ዙር የቅድመ ወሊድ ምርመራ ማግኘታቸው ታወቋል፣ በሌላ በኩል እድሜያቸው ከ አንድ አመት በታች የሆኑ 12,102 ህጻናት ሁሉንም አይነት ክትባት ወስደው እንዲጨርሱ ተደርጓል፡፡

በዞኑ 134 ቀበሌያት ሜዳላይ ከመጸዳዳት ነጻ መሆናቸው በሪፖርቱ ተጠቁሟል፤ 404 የሚሆኑ የህብረተሠብ ክፍሎች ላይ የሳንባ በሽታ የተገኘባቸውና ተገቢውን ህክምና በመከታተል ላይ መሆናቸው ተጠቁሟል፤ የወባ በሽታን ከመከላከል ረገድ በተመረጡ 4 ወረዳዎች የቤት ለቤት የኬሚካል ርጭት በማካሄድ 149,490 ሰዎችን ከበሽታው መጠበቅ ተችሏል፡፡ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ከመከላከል አንጻር 48,988 የህብረተሠብ ክፍሎች ለደም ግፊት አንዲሁም 3,900 ለስኳር በሸታ የልዬ ስራ የተሠራ ሲሆን 2,301 ሴቶች የማህጸን በር ካንሰር የምርመራ አገልግሎት ማግኘታቸውን የቀረበው የበሽታ መከላከልና ጤና ማበልጸግ ዳይሬክቶሬት ሪፖርት ጠቁሟል፡፡

በዞኑ በሶስት ወራት ውስጥ በአጠቃላይ 574,650 የማህበረሰብ ክፍሎች የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት ያገኙ ሲሆን 4,995 ሰዎች የተኝቶ ህክምና አገልግሎት አግኝተዋል፡፡ በተመሣሣይ መልኩ 5,665 የማህበረሠብ ክፍሎች የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ማግኘታቸውን የህክምና አገልግሎቶች ዳይሬክቶሬት ሪፖርት ጠቁሟል፡፡

በሶስት ወራት ውስጥ 14,281 የሚሆኑ የማህበረሠብ ክፍሎችን ለኤች.አይ.ቪ ኤድስ ምርመራ እንዲያደርጉ ማድረግ የተቻለ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 40 የሚሆኑ ሰዎች ላይ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሲሆን ለነዚህ ግለሰቦች አስፈላጊው ህክምና በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ በሌላ በኩል 253 ቫይረሱ በደማቸው ለሚገኝባቸው የማህበረሠብ ክፍሎች እና 1215 ለሚሆኑ ወላጅ አጥና ተጋለጭ ህጻናት ልዩ ልዩ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል፡፡ በ 3 ወራት ውስጥ ለ 2 መድሃኒት መደብር እና መካከላኛ ክልኒክ ፈቃድ መሰጠቱን በሪፖርት ቀርቧል፡፡ በዞኑ ባሣለፍነው ሶስት ወራት ውስጥ ለ 38 የተለያዩ ባለሙያዎች ቅጥር በመፈጸም ወደ ወረዳዎች ምደባ ተሰጥቷል፡፡

በአጠቃላይ በዞኑ ለሚገኙ ወረዳዎች የፕሮግራሞችን አፈጻጸም ለመከታተል ዘርፈ ብዙ የሆነ ድጋፋዊ ክትትል ስራዎች መካሄዳቸው ታውቋል፡፡ በዞኑ የኤልክትሮኒክስ የመረጃ ስርአት በተጀመረባቸው 9 ወረዳዎች 151,574 ቤቴሠብ እና 673,906 የቤቱስብ አባላት መመዝገባቸው ታውቋል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ 9,178 በጤና ተቋማት የወለዱ እናቶች የወሊድ ሰርተፊኬት ከወሳኝ ኩነት እንዲያገኙ የተደረገ መሆኑን የልማት ዕቅድና ኢኮኖሚ አስተዳዳር ሪፖርት የጠቆመ ሲሆን በአጠቃላይ በጥንካሬ የተገመገሙ ጉዳይች ይቀጥሉ ዘንድ እንዲሁም እንደ ክፍተት የታዩ ጉዳዮች ለቀጣይ ጊዚያት የድርጊት መርሃ ግብር በማወጣት ሁሉም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለፕሮግራሞቹ ስኬት ርብርብ እንዲያደረጉ አቅጣጫ ተቀምጧል።

👉 ስትሮክ (Stroke) ምንድን ነው?           👇👇👇ስትሮክ እጅግ በጣም አሳሳቢ የሆነ በሽታ ሲሆን በአለም ላይ በየሁለት ሰከንዱ አንድ ሰው በስትሮክ ሕመም ይጠቃል።ይህም የአካል ጉዳ...
05/11/2025

👉 ስትሮክ (Stroke) ምንድን ነው?
👇👇👇
ስትሮክ እጅግ በጣም አሳሳቢ የሆነ በሽታ ሲሆን በአለም ላይ በየሁለት ሰከንዱ አንድ ሰው በስትሮክ ሕመም ይጠቃል።

ይህም የአካል ጉዳት እና ሞትን ከሚያስከትሉ በሽታዎች አንዱ ነው ። ስትሮክ ጭንቅላታችን ውስጥ ያሉ ሴሎች ኦክሲጅን እንዳያገኙ በማድረግ እና በሰውነታችን ውስጥ በቂ የደም ዝውውር እንዳይኖር በማድረግ የሚከሰት ህመም ነው።

ሁለት አይነት የስትሮክ አይነቶች አሉ።

1)Hemorrhagic ወይም የሚደማ:- በጭንቅላታችን ውስጥ ደም ሲፈስ ወይም አርተሬዎቻችን ተጎድተው ደም ወደ ውጪ በመፍሰሱ ምክንያት የሚከሰት አይነት ነው።

2)Ischemic ወይም የኦክሲጅን እጥረት:- የደም ዝውውር ሲገታ ወይም መተላለፍ ሳይችል ሲቀር እና በቂ ኦክሲጅን ወደ ሰውነታችን መዘዋወር በለመቻሉ ምክንያት የሚከሰት አይነት ነው።

👉 የበሽታው ምልክቶች
# ራስ ምታት
# የእጅ / የእግር መዛል/ መድከም/ ፓራላይሲስ
# የተወሰነ የሰውነት ክፍል ለመንቀሳቀስ ወይም ለመራመድ መቸገር
# ለመናገር የአፍ መተሳሰር ወይም ቃላት ለማውጣት መቸገር
# የፊት መጣመም

👉 የስትሮክ በሽታ በምን ምክንያት ሊከሰት ይችላል?

# ዋንኛው የደም ግፊት በሽታ ሲሆን የደም ግፊት ፤ የስኳር ፤ የልብ ፤የኮልስትሮል ህመም ያለባቸው ሰዎች መድሃኒታቸውን በአግባቡ ካለመውሰድ ወይም በማቋረጣቸው ምክንያት ለስትሮክ ይጋለጣሉ።

# አልኮል አዘውትሮ በመጠጣት
# ሲጋራ በማጨስ
# ሆርሞናል ኢንባላንስ ወይም በተለያዩ መድሃኒቶች ምክንያት የሆርሞን መዛባት መከሰት
# የእድሜ መግፋት

👉 የበሽታው መከላከያ መንገዶች

# ጤናማ የአመጋገብ ስርዓት መከተል እንደ ቅባት ጮማ የበዛባቸው ምግቦች አለመመገብ
# አልኮል አለመጠጣት
# ሲጋራ አለማጨስ
# አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ
# እንደ ደም ግፊት ፤ የስኳር ፤ የልብ ፤የኮልስትሮል ህመም ያለባቸው ሰዎች መድሃኒታቸውን በሕክምና ባለሙያዎች ትእዛዝ መሰረት በአግባቡ መውሰድ

# በአቅራቢያዎ ወደሚገኙ የጤና ተቋማት በመሄድ የምርመራ የጤና ክትትል ማድረግ

ለበለጠ መረጃ በነጻ የስልክ ጥሪ 952 ይደውሉ የጤና ምክርና መረጃ ያግኙ!!

የስኳር በሽታ ኩላሊት ላይ የሚፈጥረው ችግር የስኳር በሽታ ትንንሽ የደም ስሮችን ይጎዳል። ኩላሊት ውስጥ የሚገኙት ትንንሽ የደም ስሮች ሲጎዱ፤ ኩላሊታችን ደምን የማጣራት ተግባሩን በትክክል መ...
04/11/2025

የስኳር በሽታ ኩላሊት ላይ የሚፈጥረው ችግር

የስኳር በሽታ ትንንሽ የደም ስሮችን ይጎዳል። ኩላሊት ውስጥ የሚገኙት ትንንሽ የደም ስሮች ሲጎዱ፤ ኩላሊታችን ደምን የማጣራት ተግባሩን በትክክል መከወን አይችልም።

ይህ ማለትም፣ ሰውነታችን መያዝ ከሚገባው በላይ ውሃ እና ጨው ይይዛል ማለት ነው። ይህ ደግሞ ለክብደት መጨመር እና የእግር ማበጥ ያጋልጣል

የሽንት መጠን በሽንት ፊኛ ውስጥ በሚበዛበት ጊዜ የሚፈጠረው ግፊት፣ ሽንት ወደ ኋላ ማለትም ወደ ኩላሊቶች እንዲመለስ ስለሚያደርገው ኩላሊትን ለ ኢንፌክሽን ሊያጋልጠው ይችላል።

ምን ያህሉ የስኳር ህመምተኞች ለኩላሊት በሽታ የተጋለጡ ናቸው?

30 በመቶ የሚሆኑት የአይነት 1 ስኳር ህመምተኞች እንዲሁም ከ 10 እስከ 40 በመቶ የሚሆኑት የአይነት 2 ስኳር ህመምተኞች ለከፍተኛ የኩላሊት ጉዳት የተጋለጡ ናቸው

የስኳር ህመምተኞች ላይ በመጀመሪያ የሚታዩ የኩላሊት ህመም ምልክቶች ምንድን ናቸው?

በስኳር ህመምተኞች ላይ የሚታየው የመጀመሪያው ኩላሊት ህመም ምልክት ፦ክብደት መጨመር፣ የእግር ማበጥ፣ ከወትሮው በተለየ ሌሊት ላይ ለሽንት መነሳት፣ የደም ግፊት መጨመር በተያያዥነት ሊታዩ የሚችሉ የኩላሊት ህመም ምልክቶች ተጠቃሽ ናቸው።

በተወሰኑ ወራት አንዴ የደም ግፊት እንዲሁም የደምና የሽንት ምርመራ ማድረግ ችግሩ ሳይከሰት ቶሎ ለመከላከል ይረዳል።

የስኳር ህመምተኞች ላይ በሂደት (በስተመጨረሻ) የሚታዩ የኩላሊት ህመም ምልክቶች ምንድን ናቸው? ማቅለሽለሽ፣ ማስመለስ፣ የምግብ ፍላጎት መቀነስ፣ ከፍተኛ የድካም ስሜት፣ የሰውነት ማሳከክ፣ የጡንቻ ህመም (በተለይ እግሮች ላይ) እና የ ደም ማነስ።

የኩላሊቶች የመስራት አቅም እየተመናመነ በሚሄድበት ጊዜ ሰውነታችን የሚጠቀመው የኢንሱሊን መጠን እያነሰ ይሄዳል። ይህም የሚሆነው ኩላሊታችን ኢንሱሊንን በተገቢው መልኩ ማጣራት ስለማይችል ነው።

በስኳር ህመምተኞች ላይ የሚታዩ የኩላሊት ህመም ምልክቶች:- በሽንት ውስጥ የሚታይ ፕሮቲን (አልቡሚን) ፤ ከፍተኛ የደም ግፊት ፤የእግር ማበጥ ፤ሌሊት በተደጋጋሚ ለሽንት ከእንቅልፍ መነሳት ፤በደም ውስጥ ከፍተኛ የክሪያቲኒን መጠን ፤ ከበቂ በታች የስኳር መድሃኒቶች ማስፈለግ፤ የጠዋት ማቅለሽለሽ ፤ ድካም፣ የደም ማነስ፣ መገርጣት እና ማሳከክ ነቸው።

የኩላሊቶቻችንን ጤንነት ለመጠበቅ ማድረግ የሚገቡን ነገሮች:- የደማችንን የስኳር መጠን ማስተካከል፤ ከፍተኛ የደም ግፊትን መቆጣጠር፤ የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽንን በጊዜ መታከም ፤ከሽንት ጋር የተያያዙ ችግሮችን መቅረፍ፤ ኩላሊትን ሊጎዱ የሚችሉ መድሃኒቶችን (በተለይም የህመም ማስታገሻ መድሃኒቶችን) በብዛት አለመጠቀም የመሳሰሉት ናቸው።

ከዕለት ተዕለት ምግባችን ውስጥ የ ፕሮቲንን መጠን መቀነስ ሊኖርብን ይችላል። ከነዚህ በተጨማሪ የኩላሊቶችን ጉዳት ለመቀነስ ከሃኪም የሚሰጡ ምክሮችን ተግባራዊ ማድረግ ይገባል።

በስኳር ህመምተኞች ላይ የሚከሰት የመጨረሻ ደረጃ የኩላሊት መድከም ይታያል።ይህ የሚከሰተው የኩላሊቶች ጉዳት መመለስ ከሚቻልበት አቅም በላይ ሲሆን ነው። ይህም ማለት የኩላሊቶች የመስራት አቅም ከ 10 እስከ 15 ፐርሰንት ሲሆን ነው።

በዚህም ጊዜ በማሽን ኩላሊትን የማጣራት ተግባር (ዳያሊሲስ) አልያም የኩላሊት ንቅለ ተከላ ያስፈልጋል።

የጤና ፍትሃዊነትን ለማስፈን፡ የመክፈል አቅምን መሰረት ያደረገ የጤና መድህን ክፍያ ስርዓት ተዘርግቷል፡፡‎‎ምንጭ ጥቅምት 25/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)‎‎ዜጎች በህክምና ወጪ...
04/11/2025

የጤና ፍትሃዊነትን ለማስፈን፡ የመክፈል አቅምን መሰረት ያደረገ የጤና መድህን ክፍያ ስርዓት ተዘርግቷል፡፡

‎ምንጭ ጥቅምት 25/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎ዜጎች በህክምና ወጪ ስጋት ወደ ጤና ተቋማት ከመሄድ እንዳይቆጠቡ ያስቻለ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ ተግባራዊ መሆኑን የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት አስታወቀ፡፡

‎በኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት፣ የአባላት አስተዳደርና ሀብት አሰባሰብ መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ጉደታ አበበ እንደገለጹት፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ በ1 ሺህ 1 መቶ 95 ወረዳዎች የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው፣ በአጠቃላይ ከ63 ሚሊየን በላይ ዜጎች በጤና መድህን ስርዓቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡

‎የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ ባልተጀመረባቸው ዘመናት፣ ለህክምና የሚሆን ገንዘብ በማጣት በርካታ ዜጎች ለረጅም ጊዜ ህመምና ለሞት የሚዳረጉበት ጊዜ እንደነበር አስታውሰው፣ አሁን ዜጎች በህክምና ወጪ ስጋት ወደ ጤና ተቋማት ከመሄድ እንዳይቆጠቡ ያስቻለ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተሰጠ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

‎የጤና መድህን ስርዓት ዋናዋና ዓላማዎች በዜጎች መካከል ፍትሃዊ የሆነ የህክምና አገልግሎት እንዲኖር ማስቻል፤ ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት ለዜጎች ለመስጠትና የመረዳዳት ባህልን በማሳደግ፣ ግለሰቦች እንደ አቅማቸው አዋጥተው በህመማቸው ልክ የህክምና አገልግሎት በየትኛውም ህክምና እርከን እንዲያገኙ ማስቻል መሆኑን ስራ አስፈጻሚው አስገንዘበዋል፡፡

‎በሁሉም አካባቢ የሚገኘው የህብረተሰብ ክፍል፣ ገቢ የሚያገኝበት ወቅትና የመክፈል አቅሙም ልዩ ልዩ መሆኑን የጠቆሙት ስራ አስፈጻሚው፤ መንግስት ይሄንኑ ጉዳይ ታሳቢ በማድረግ የመክፈል አቅምን መሰረት ያደረገ የክፍያ ስርዓት መዘርጋቱን አስረድተዋል፡፡

‎በዚህም መሰረት በአዲስ አበባ ከጥቅምት አንድ ጀምሮ ለሁለት ወራት ያህል የአባላት ምዝገባና እድሳት የሚካሄድ ሲሆን በሌሎች ክልሎች ከህዳር አንድ ጀምሮ እንደየአካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ የምዝገባና እድሳት ስራው እንደሚከናወን አቶ ጉደታ ገልጸዋል፡፡

‎በዘርፉ ባለፉት 14 ዓመታት በርካታ ስኬቶች የተመዘገቡ ቢሆንም በተለይም ከመድኃኒት አቅርቦት ጋር በተያያዘ በርካታ ተግዳሮቶች በብዙ የጤና ተቋማት ማጋጠማቸውን አስረድተዋል፡፡ ችግሩን ለመፍታት መንግስት በሀገር ውስጥ መድኃኒት በማምረት ሰፊ ስራዎች እየሰራ መሆኑን ጠቁመው የማህበረሰብ መድኃኒት ቤቶችን በማስፋፋት፣ የከነማ መድኃኒት ቤቶችን በመጠቀም ችግሩን ለመፍታት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አቶ ጉደታ ገልጸዋል፡፡

‎ምንጭ፡-ኢጤመአ

የጤና ክብካቤ ሠራተኞች የማህበራዊ ጤና መድህን 👇👇👇
03/11/2025

የጤና ክብካቤ ሠራተኞች የማህበራዊ ጤና መድህን 👇👇👇

በቆጎታ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤ ሥር በሚገኘዉ ኤዞ ጤና ጣቢያ የእናቶች ማቆያ ቤት የምረቃ ስነ ሰርዓት ተካሄደ‎‎ምንጭ ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)‎‎በቆጎታ ወረዳ ...
03/11/2025

በቆጎታ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤ ሥር በሚገኘዉ ኤዞ ጤና ጣቢያ የእናቶች ማቆያ ቤት የምረቃ ስነ ሰርዓት ተካሄደ

‎ምንጭ ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎በቆጎታ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤ ሥር በሚገኘዉ ኤዞ ጤና ጣቢያ የእናቶች ማቆያ ቤት የምረቃ ስነ ሰርዓት ተካህዷል።

‎በሀገሪቱ በጤናው ዘርፍ የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ ቀጣይነት እንዲኖረው ለማድረግ እና የእናቶች እና ሕጻናትን ሞት ለመቀነስ ግብ ተጥሎ አየተሠራ ይገኛል።

‎በዚህም በቆጎታ ወረዳ ይህንን ከግብ ለማድረስ የእናቶች ማቆያ ለእናቶች ጤና ተብሎ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።

‎እንደ ሀገር በጤና ፖሊሲ የተቀመጡ መመሪያዎችን መሠረት በማድረግ ለማኅበረሰቡ ቀልጣፋ የጤና አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛልም ተብሏል።

‎የእናቶች ማቆያ ግንባታ ወደ ዉጤት ለማድረስ የወረዳ መንግስት፣ቀበሌያት ድጋፍ እና አስተዋጾኦ ያበረከቱ ሲሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱት የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።

‎በምረቃ መርሐ ግብሩ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ተወካይ አቶ አጥናፉ አበራ፣የቆጎታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪን ጨምሮ አስተባባሪ አካላት፣የቆጎታ ወረዳ ህዝብ ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ አሰፋ አየለ የጨንቻ አጠቃላይ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘላለም ዘዉ፣ የጤና ጥበቃ ቦርድ አባላት የቆጎታ ወረዳ የጤና ጥበቃ ጽ/ቤት እና ኤዞ ጤና ጣቢያ የሥራ ኃላፊዎችና ባለሞያዎች፣የቀበሌ ሊቀመናብርት እና ሥራ ሥራ አሰኪያጆች ተገኝተዋል።

‎አንድም እናት በወሊድ ምክንያት መሞት የለባትም!

የሰላምበር ከተማ ጤና ጣቢያ የ2018 ዓ.ም 1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ከባለድርሻ አካላት ጋር እየገመገመ ይገኛል ‎‎ምንጭ ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)‎‎የሰላ...
03/11/2025

የሰላምበር ከተማ ጤና ጣቢያ የ2018 ዓ.ም 1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ከባለድርሻ አካላት ጋር እየገመገመ ይገኛል

‎ምንጭ ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም ( የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎የሰላምበር ከተማ ጤና ጣቢያ የ2018 ዓ.ም 1ኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ከባለድርሻ አካላት ጋር እየገመገመ ይገኛል

‎በዕለቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ የሰላምበር ከተማ አስተዳደር ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌትነት ጋንታ በ2017 ዓ.ም በጤናው ዘርፍ የተሠሩ ተግባራት ተስፋ ሰጪ ቢሆኑም፤ ከአስተዳደራዊ ወሰን መጨመሩ ጋር በተገናኘ የጤና ሥራ ከዓምናው በላይ የሥራ ጫና ያለበት በመሆኑ ሁሉም ጤና ባለሙያዎች እና ባለድርሻ አካላት ከመቼውም ጊዜ በላይ ተጠናክረው ሊሠሩ ይገባል ስል አሳስበዋል።

‎የ2018 ዓ.ም 1ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም ሪፖርት በሰላምበር ከተማ ጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ ሶፎንያስ ባርዛ በኩል እየቀረበ የሚገኝ ሲሆን በመጨረሻ በተነሱ ጉዳዮች ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል

Address

Shecha Sub City, Beside Zone Administration
Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram