15/03/2026
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሉ ጤና ቢሮ ፤ ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ እና አርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ማሰተባባር ማይዕከል በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ እና ሌሎች ወረዳዎች ከመሬት ናዳ ምክንያት ለተፈናቀሉ ህብረተሰብ ክፍሎች እየተደረገ ያለው ክብካበና ድጋፉ ሥራዎች ያለበት ሁነታ የሁለተኛ ቀን ውሉ ግምግማ አድርጓል፡፡
አርባምንጭ መጋቢት 6/2018, ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፍ አቶ እንዳሻው ሽብሩ እና ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃልፍ አቶ ሰይፉ ዋናቃ ሌሎች ክልሉ ከፍተኛ ባለሙያዎች የዞኑ ባለሙያዎች እንዲሁም አጋር ድረጅቶች በተሳተፉበት በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ እና ሌሎች ወረዳዎች በመሬት ናዳ ምክንያት ከቤት ንብረታወc የተፈናቀሉ ህብረተሰብ ክፍሎች በዋናነት እየተደረገ ያለው ድጋፍ ክበካቤና የህክምና ሥራ፤የምግብ ዕጥረት ልይታ የሥነ-አይምሮ እና የሥነ-ልቦና እና ማይበራዊ ድጋፍ እና ምክር አገልግሎት አሰጣጥ ሁነታ ፤የአደጋ ጊዜ ተግባባት እና ተጋለጭነት እን የህብረተሰብ ተሳትፎ ሥራዎች አስፈለጊውን ግብዓት አቅርቦት እና የሀብት ማሳበሰብ ሀነታ ፤ ግምግማ አድረጓል፡፡
በተጨማሪ ቀጣይ ሁሉም ወረዳ መዋቅሮች ፡
1. ከመሬት መንሸራተትና የጎርፍ ሥጋት ውስጥ ያሉት አካባባዎች የቅድሜ ማስተነቀቂያ መረጃዎችን ለህበረተሰቡ ማሰራጨት
2. በደጋማ ቦታዎች እና በዝቅተኛ አካባቢዎች ባለው ማህበረሰብ መካከል ወቅታዊ የመረጃ ልውውጥ እንድኖር ማድረግ
3. የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ ስጋት ያለባቸው አካባቢዎች የሚኖረው ህብረተሰብቡ አስቀድሞ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደረግ የአደጋ ስጋት መኖሩን ማሳወቅ እና ግንዛቤ መፍጠር
4. የመሬት መንሸራተት ምልክቶች (እንደድንጋይ መውደቅ ወይም የመሬት መረጋጋት ለውጥ ያሉ ማንኛውም አዝማማያ ሲታይ ወዲያውን ለአከባቢ መንግስት አካላትን ማሳወቅ
5. በደጋማ አካባቢ ናዳና መሬት መንሸራተት ተከትለው ቆላማ አካባባ መዳማ ስለሆነ በውኃ መሙላትን ተከትለው ተላላፍ በሽታዎች እንደ ወባ፣ኩፍኝ ፤ኮሌራ ሌሎች በሽታዎች ሊከሰቱ ስለሚችል ዝግጀት ማድረግ ሰከስት ወደያው ሪፖርት ማደረግ ተገቢውን ርምጃ መውሰድ
6. የምግብ ዕጥረት ልይታ በትኩሬት መሥራት ያስፈልጋል፡፡