Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ

Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ Disease prevention and control
Maternal and child health
Nutrition
Health care financing

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሉ ጤና ቢሮ ፤ ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ እና አርባምንጭ ከተማ አስተዳደር  የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ማሰተባባር ማይዕከል  በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ እና ሌሎች ወረዳዎች   ከመ...
15/03/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሉ ጤና ቢሮ ፤ ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ እና አርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ማሰተባባር ማይዕከል በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ እና ሌሎች ወረዳዎች ከመሬት ናዳ ምክንያት ለተፈናቀሉ ህብረተሰብ ክፍሎች እየተደረገ ያለው ክብካበና ድጋፉ ሥራዎች ያለበት ሁነታ የሁለተኛ ቀን ውሉ ግምግማ አድርጓል፡፡
አርባምንጭ መጋቢት 6/2018, ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፍ አቶ እንዳሻው ሽብሩ እና ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃልፍ አቶ ሰይፉ ዋናቃ ሌሎች ክልሉ ከፍተኛ ባለሙያዎች የዞኑ ባለሙያዎች እንዲሁም አጋር ድረጅቶች በተሳተፉበት በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ እና ሌሎች ወረዳዎች በመሬት ናዳ ምክንያት ከቤት ንብረታወc የተፈናቀሉ ህብረተሰብ ክፍሎች በዋናነት እየተደረገ ያለው ድጋፍ ክበካቤና የህክምና ሥራ፤የምግብ ዕጥረት ልይታ የሥነ-አይምሮ እና የሥነ-ልቦና እና ማይበራዊ ድጋፍ እና ምክር አገልግሎት አሰጣጥ ሁነታ ፤የአደጋ ጊዜ ተግባባት እና ተጋለጭነት እን የህብረተሰብ ተሳትፎ ሥራዎች አስፈለጊውን ግብዓት አቅርቦት እና የሀብት ማሳበሰብ ሀነታ ፤ ግምግማ አድረጓል፡፡
በተጨማሪ ቀጣይ ሁሉም ወረዳ መዋቅሮች ፡
1. ከመሬት መንሸራተትና የጎርፍ ሥጋት ውስጥ ያሉት አካባባዎች የቅድሜ ማስተነቀቂያ መረጃዎችን ለህበረተሰቡ ማሰራጨት
2. በደጋማ ቦታዎች እና በዝቅተኛ አካባቢዎች ባለው ማህበረሰብ መካከል ወቅታዊ የመረጃ ልውውጥ እንድኖር ማድረግ
3. የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ ስጋት ያለባቸው አካባቢዎች የሚኖረው ህብረተሰብቡ አስቀድሞ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደረግ የአደጋ ስጋት መኖሩን ማሳወቅ እና ግንዛቤ መፍጠር
4. የመሬት መንሸራተት ምልክቶች (እንደድንጋይ መውደቅ ወይም የመሬት መረጋጋት ለውጥ ያሉ ማንኛውም አዝማማያ ሲታይ ወዲያውን ለአከባቢ መንግስት አካላትን ማሳወቅ
5. በደጋማ አካባቢ ናዳና መሬት መንሸራተት ተከትለው ቆላማ አካባባ መዳማ ስለሆነ በውኃ መሙላትን ተከትለው ተላላፍ በሽታዎች እንደ ወባ፣ኩፍኝ ፤ኮሌራ ሌሎች በሽታዎች ሊከሰቱ ስለሚችል ዝግጀት ማድረግ ሰከስት ወደያው ሪፖርት ማደረግ ተገቢውን ርምጃ መውሰድ
6. የምግብ ዕጥረት ልይታ በትኩሬት መሥራት ያስፈልጋል፡፡

14/03/2026
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሉ ጤና ቢሮ እና ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ በዞን ደረጃ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ማሰተባባር ማይዕከል  በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ እና ሌሎች ወረዳዎች ላይ ከመሬት ናዳ ምክንያት ...
14/03/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሉ ጤና ቢሮ እና ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ በዞን ደረጃ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች ማሰተባባር ማይዕከል በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ እና ሌሎች ወረዳዎች ላይ ከመሬት ናዳ ምክንያት ለተፈናቀሉ ህብረተሰብ ክፍሎች እየተደረገ ያለው ክብካበና ድጋፉ ሥራዎች ያለበት ሁነታ ዕለታዊ ግምግማ አድርጓል፡፡
አርባምንጭ መጋቢት 5/2018, ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃልፍ አቶ እንዳሻው ሽብሩ ፣የደቡብ ኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት ኃልፍ አቶ አጉነ አሾሌ እና ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃልፍ አቶ ሰይፉ ዋናቃ በተሳተፉበት በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ እና ሌሎች አካባቢዎች በመሬት ናዳ ምክንያት ከቤት ንብረታወc የተፈናቀሉ ህብረተሰብ ክፍሎች እየተደረገ ያለው ክብካቤና ድጋፍ ሥራዎችና ተጨማሪ ጉዳት ሳያስከተል እንዲያገገሙ ለማድረግ ከክልል ጤና ቢሮ , ከጋሞ ዞን ጤና መምሪያ እና አርባምንጭ ከተማ አሰተዳደር የተወጣጠ ቡዱን የህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደገዎች ማስተባባሪያ ማይዕከል ከናዳው ጋር ተያይዞ የደረሰው ጉዳት መጠን ፣የተፈናቀለ ቤተስብ ብዛት ፣የተፈናቀለ ቤተሰብ አባላት ብዛት፣ በዞኑ ወስጥ ተመሳሰይ ችግር ያለባቸው ቀበሌዎች፣በአደጋው የተገዱ ሰዎች የሚደረገው ድጋፍና ክብካቤ ሥራዎች በተላይ የህክምና የሚሰጥ ቡዱን በቦታው ሆነው አየሠራ ያሉ ሥራዎችና የሁነታ ፤ ግምግማ አድረጓል፡፡

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የጎርፍ እና መሬት መንሸራተት አደጋዎች ቅድመ ማስጠንቀቅያ መልዕክት አስተላልፏል።‎‎መልዕክቱም እንደሚከተለው ነው፥
11/03/2026

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የጎርፍ እና መሬት መንሸራተት አደጋዎች ቅድመ ማስጠንቀቅያ መልዕክት አስተላልፏል።

‎መልዕክቱም እንደሚከተለው ነው፥

በጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በዶ/ር ደምሴ አድማሱ የተመራ ከፍተኛ ልዑክ በጋጮ ባባ ወረዳ ላካ ቀበሌ፣ ባኖ ንዑስ መንደር በመሬት ናዳ አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች ቤተሰቦች በቦታው ተገኝቶ ...
11/03/2026

በጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ በዶ/ር ደምሴ አድማሱ የተመራ ከፍተኛ ልዑክ በጋጮ ባባ ወረዳ ላካ ቀበሌ፣ ባኖ ንዑስ መንደር በመሬት ናዳ አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች ቤተሰቦች በቦታው ተገኝቶ መጽናኛ አጽናኑ

​በልዑኩ ውስጥ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪን ጨምሮ የሥራ አስፈጻሚና የካቢኔ አባላት፣ የፌደራልና የክልል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እንዲሁም የፌደራልና የክልል ተጠሪ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

​ልዑኩ በአደጋው ሕይወታቸውን ባጡ ዜጎች የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ፣ ጉዳት የደረሰባቸውን ቤተሰቦችና ነዋሪዎችን አጽናንቷል።

ይህ ጉብኝት መንግሥት በአስቸጋሪ ወቅት ከሕዝቡ ጎን መሆኑን ለማሳየትና የተጎዱ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑ ተገልጿል።

የጋሞ ዞን አደጋ ስጋት ስራ አመራር ግብረ-ኃይል በወቅታዊ የአደጋ ሁኔታና የመፍትሔ አቅጣጫዎች ላይ ተወያየ‎‎​አርባምንጭ ፡ መጋቢት 2፣2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)‎‎​በዞኑ ከጣለ...
11/03/2026

የጋሞ ዞን አደጋ ስጋት ስራ አመራር ግብረ-ኃይል በወቅታዊ የአደጋ ሁኔታና የመፍትሔ አቅጣጫዎች ላይ ተወያየ

‎​አርባምንጭ ፡ መጋቢት 2፣2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎​በዞኑ ከጣለው ከባድ ዝናብ ጋር ተያይዞ በተከሰቱ አደጋዎች ለተጎዱ ወገኖች አስቸኳይ ድጋፍ ለማድረግና ዘላቂ መፍትሔ ለማስቀመጥ የሚያስችል የምክክር መድረክ ተካሂዷል።

‎ግብረ-ኃይሉ ባካሄደው በዚህ መድረክ በደጋማ አካባቢዎች በደረሰው ጉዳት ዙሪያ ዝርዝር ግምገማ በማድረግ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

‎​የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በዞኑ በተለያዩ አካባቢዎች በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ ናዳና በጎርፍ አደጋ የሰው ህይወት በመጥፋቱ የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸዋል።

‎አያይዘውም በአደጋው ምክንያት ተፈናቅለው ለችግር የተጋለጡ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም የመጠለያ፣ የምግብና የህክምና እርዳታ በልዩ ትኩረትና በአስቸኳይ ሊቀርብ እንደሚገባ አሳስበዋል።

‎​ዋና አስተዳዳሪው አክለውም ​በጎርፍና በናዳ ምክንያት የተቋረጡ የትራንስፖርት መሰረተ ልማቶችን ለመጠገንና የተጎዱ ትምህርት ቤቶችን መልሶ ስራ ለማስጀመር ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

‎የተዘጋውን መንገድ ለማስከፈት የሚያስፈልጉ ከባድ ማሽነሪዎችን ከሌላ አካባቢ ለማስመጣት በሂደት ላይ መሆኑን የተናገሩት አስተዳዳሪው ህብረተሰቡ በቀጣይ ሊከሰቱ ከሚችሉ ተጨማሪ አደጋዎች ራሱን እንዲጠብቅ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

‎​እስካሁን ባለው መረጃ መሰረት በአደጋው የሟቾች ቁጥር 30 መድረሱ የተገለጸ ሲሆን፣ ጉዳቱ ሰፊ በመሆኑ ቁጥሩ ሊጨምር እንደሚችል ተገምቷል።

‎በመሆኑም ከአንድ ማዕከላዊ ቋት (Command Post) ፈጣን እና ተአማኒ የሆነ የመረጃ ልውውጡ በማድረግ ለህዝብ ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።

‎​ አስቸኳይ የምግብ፣ የመጠለያና የህክምና እርዳታ የሚሹ ስሆች እየተለዩ በመሆናቸው፣ ይህንን ክፍተት ለመሙላት የተቀናጀ የሀብት ማሰባሰብ ስራ እንደሚከናወንም ተገልጿል።

‎ድጋፉን በተቀናጀና ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመምራት የተለያዩ ንዑሳን ኮሚቴዎች ተደራጅተው ወደ ስራ ገብተዋል። ከእነዚህም መካከል የሀብት አሰባሰብ፣ የምግብና ጤና፣ የመረጃ (ኮሙዩኒኬሽን)፣ የመጠለያ ዝግጅትና ሌሎች አስፈላጊ ኮሚቴዎች ይገኙበታል።

‎​በመጨረሻም፣ የግብረ-ኃይሉ የአፈጻጸም ሂደት በየጊዜው እየተገመገመ እንዲሄድና የተጀመሩ የነፍስ አድንና የመልሶ ማቋቋም ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ዋና አስተዳዳሪው ጥሪ አቅርበዋል።

‎ለዚህ አደጋ የተከፈተ የሀብት ማሰባሰብያ አካውንት

‎የጋሞ ልማት ማህበር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውት 1000021467174

‎የጋሞ ዞን አደጋ ስጋት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውት 10000321312865

ከጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የተሰጠ የሀዘን መግለጫ‎‎​በዞናችን በተለያዩ አካባቢዎች በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት፣ በተለይም በደጋማ አካባቢዎች በተከሰተ የናዳና የጎርፍ አደጋ የ30 ወገኖቻችን ...
10/03/2026

ከጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የተሰጠ የሀዘን መግለጫ

‎​በዞናችን በተለያዩ አካባቢዎች በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት፣ በተለይም በደጋማ አካባቢዎች በተከሰተ የናዳና የጎርፍ አደጋ የ30 ወገኖቻችን ህይወት በማለፉ የዞኑ አስተዳደር ገልጿል ።

‎​በደረሰው ድንገተኛ አደጋ ህይወታቸውን ባጡ ወገኖቻችን የተሰማውን ጥልቅ መምሪያው እየገለጸ፤ ለአደጋው ሰለባ ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶችና ለመላው የዞኑ ህዝብ መጽናናትን ይመኛል።

‎በተጨማሪም በዞኑ በሁሉም አከባቢዎች ​ወቅቱን ያልጠበቀ ከባድ ዝናብ እየዘነበ በመሆኑ የውሀ ሙላት፤ የጎርፍ አደጋ፤ እንዲሁም የመሬት መንሸራተት አደጋዎች ከመከሰታቸው በፊት አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ መልዕክቱን ያስተላልፋል።

ለማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚዎች የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ ተደራሽ በማድረጉ ረገድ የኮሙኒኬሽን ተቋማት ሚና የጎላ መሆኑ ተገለጸ‎‎አርባምንጭ ፡ መጋቢት 1፣2018 ዓ.ም ...
10/03/2026

ለማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚዎች የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ ተደራሽ በማድረጉ ረገድ የኮሙኒኬሽን ተቋማት ሚና የጎላ መሆኑ ተገለጸ

‎አርባምንጭ ፡ መጋቢት 1፣2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)


‎የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት አርባምንጭ ቅርንጫፍ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባላትን መረጃ ከብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ "ፋይዳ" ጋር ለማስተሳሰር ከክልሉ ጤና ቢሮና ከመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጋር በመተባበር ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ እያካሄደ ይገኛል።

‎በመድረኩ የተገኙት የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ አዜብ ዘውዱ እንደገለጹት "ፋይዳ” ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ የጤና መድህን አገልግሎትን 100% ተደራሽ ለማድረግ የኮሙኒኬሽን ተቋማት ሚና የጎላ ከመሆኑም ባሻገር ቀልጣፋ የጤና አገልግሎት ስርዓትን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

‎መንግስት በ2030 ለማሳካት ከያዛቸው የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ግቦች አንዱ የሆነውን የፋይዳ መታወቂያ በክልሉ ለሚገኙ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ተጠቃሚ አባላት ጋር በማስተሳሰር መሰራቱ ቀልጣፋ እና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው ያሉት ሀላፊዋ ተግባሩን ውጤታማ ለማድረግ የኮሙኒኬሽን ተቋማት አንዱ አጀንዳ በማድረግ የተለያዩ የሚዲያ አማራጮችን በመጠቀም ትኩረት ሰጥቶ ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል ።

‎በኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት አርባምንጭ ቅርንጫፍ ስራአስኪያጅ አቶ ጨንቻ መላው እንደገለጹት የጤና መድህን አገልግሎቱን ዘመናዊና የተቀላጠፈ በማድረግ ለዲጂታል ጤና ስርአት ግንባታ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ፋይዳ ተኪ የሌለው ተግባር ነው ሲሉ ተናግረዋል።

‎የኮሙኒኬሽን ተቋማት ከጤና ተቋም ጋር በመቀናጀት የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚዎች ሙሉ በሙሉ የፋይዳ መታወቂያ እንዲኖራቸው የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን ገልጸዋል ።

‎ የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ዳዊት ደሳለኝ በበኩላቸው የፋይዳ መታወቂያ ከጤና መድህን የአባላት ምዝገባ እና እድሳት ጋር መተሳሰሩ የታካሚ መረጃ በመለየት የህክምና ታሪክ ለመከታተልና የጤና አገልግሎት ለማሻሻል ሚናው የጎላ መሆኑን ጠቅሰው የተሻለ የታካሚ ደህንነት በመጠበቅ ጊዜና ወጪ ቆጣቢ መሆኑን ገልጸዋል።

‎በጤና ሴክተር የሚሰሩ የመንግስት ሰራተኞች የማህበራዊ ጤና መድህን ዋስትና እንዲረጋገጥ የህክምና ወጪ ሙሉ በሙሉ በመንግስት መሸፈኑን የገለጹት ኃላፊው በጤናው ዘርፍ የታቀደውን ግብ ለማሳካት የባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደሚጠይቅ አመላክተዋል።

‎የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አባላትን የፋይዳ መታወቂያ በሚፈለገው ፍጥነት ለማስተሳሰር የፋይዳ መታወቂያ የሌላቸው አባላት በማውጣት ለስራው ስኬታማነት የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

‎የፋይዳ መታወቂያ ከጤና መድህን ማስተሳሰር የሚያስችል ሰነድ ቀርቦ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

‎በመድረኩ ከሁሉም ዞኖችና ከተማ አስተዳደር የተገኙ የጤና መምሪያ ኃላፊዎችና የኮሙኒኬሽን ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል።

‎ #የጥንቃቄ መልዕክት‎‎የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከሰሞኑ በሚጥለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት ሕብረተሰቡ ከድንገተኛ የደራሽ ውኃ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አስታወቀ‎‎ አርባምንጭ ፡ መጋቢት 1፣...
10/03/2026

‎ #የጥንቃቄ መልዕክት

‎የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከሰሞኑ በሚጥለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት ሕብረተሰቡ ከድንገተኛ የደራሽ ውኃ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አስታወቀ

‎ አርባምንጭ ፡ መጋቢት 1፣2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎ትላንት ምሽትን ጨምሮ ከሰሞኑ በሚጥለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በተለይም በከተማዋ ወንዝ ተፋሰስ አካባቢ የደራሽ ውኃ መጥለቅለቅ መከሰቱ አስተዳደሩ ገልጿል።

‎በተከሰተው የደራሽ ውኃ መጥለቅለቅ በድርጅቶችና በመኖሪያ ቤቶች ላይ ከከባድ እስከ ቀላል የንብረት ውድመት የደረሰ ሲሆን ይበልጥ የከፋ እንዳይሆንና አደጋውን ለመከላከል ከተማ አስተዳደሩ ባሉት ማሽኖችና በባለሀብቶች አጋዥነት ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝም አስታውቋል።

‎አስተዳደሩ ለዚሁ የጥንቃቄ ሲባል በአኪባቢው የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጡን የገለፀ ሲሆን በአዲስ ከተማ የኖክ ሳይት የመኖሪያ መንደር ለሚገኙ ነዋሪዎች፣ድርጅቶችና ተቋማት ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉም አሳስቧል።

ይህ ታሪካዊ ድል የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ለጤና ስርዓቱ መሻሻል ያበረከቱት የላቀ ጥረት ውጤት ነው - ዶ/ር አምባቸው ዱማ‎‎አርባምንጭ፡ የካቲት 29/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ...
08/03/2026

ይህ ታሪካዊ ድል የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ለጤና ስርዓቱ መሻሻል ያበረከቱት የላቀ ጥረት ውጤት ነው - ዶ/ር አምባቸው ዱማ

‎አርባምንጭ፡ የካቲት 29/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ) )

‎​የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል በሀገር አቀፍ ደረጃ በተደረገ የሆስፒታሎች የጥራትና የአገልግሎት አሰጣጥ ግምገማ 3ኛ ደረጃን በመያዝ የሁለት ሚሊዮን ብር ተሸላሚ ሆኗል።

‎ለልኡክ ቡድኑ በተደረገው ደማቅ የአቀባበል ስነስርዓት ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ዋና ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አምባቸው ዱማ ይህ ታሪካዊ ድል የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ለጤና ስርዓቱ መሻሻልና ለታካሚዎች ደህንነት ሌሊትና ቀን ያበረከቱት የላቀ ጥረት ውጤት መሆኑን ገልፀዋል።

‎በሀገር አቀፍ ደረጃ በ90 ሆስፒታሎች መካከል በተደረገው ውድድር ሆስፒታሉ 3ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ የሁሉም ባለድርሻ የነቃ ተሳትፎ መሆኑን ገልፀው ለተገኘው ውጤት አስተዋጽኦ ላደረጉ የክልልና የዞን ጤና መዋቅሮች፣ የቦርድ አባላትና ለመላው የሆስፒታሉ ባለሙያዎች ምስጋና አቅርበዋል።

‎አክለው ሆስፒታሉ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደግሞ የ1ኛ ደረጃን በመያዝ የክልሉና የዞኑ የኩራት ምንጭ መሆኑም ነው ዶ/ር አምባቸው የጠቆሙት።

‎​ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰይፉ ዋናቃ በበኩላቸው ይህ ውጤት ሆስፒታሉ በቀጣይ የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጥ ለአመራሩና ሠራተኛው ትልቅ መነቃቃትን የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።

‎ሆስፒታሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ አዳዲስ አሰራሮችን ወደ ተግባር በመቀየር ለህብረተሰቡ ተደራሽ እየሆነ መምጣቱን ገልፀው ውጤቱ የመተባበር፣ የአንድነትና የላቀ ትጋት ምልክት መሆኑን ተናግረዋል።
‎​
‎​የሆስፒታሉ ምክትል ዳይሬክተር ዶ/ር አዲሱ ተስፋዬ ሆስፒታሉ ቀደም ሲልም በተለያዩ ጊዜያት ተሸላሚ መሆኑን አስታውሰው፣ አሁን የተገኘውን ውጤት ለተሻለ ስራ የሚያነሳሳ ከመሆኑም በላይ ሆስፒታሉ በቀጣይ ይህንን ጥረቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል።


‎ በመድረኩ የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር አምባቸው ዱማ፣የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰይፉ ዋናቃን ጨምሮ የሆስፒታሉ ሠራተኞች እንድሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል

በሀገር አቀፍ ደረጃ የላቀ ውጤት በማስመዝገብ የ2 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ የሆነ አርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ልዑካን ወደ አርባምንጭ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።‎‎አርባምንጭ፡ ...
08/03/2026

በሀገር አቀፍ ደረጃ የላቀ ውጤት በማስመዝገብ የ2 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ የሆነ አርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ልዑካን ወደ አርባምንጭ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

‎አርባምንጭ፡ የካቲት 29/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎ሆስፒታሉ በክልል 1ኛ እንድሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ 3ኛ በመውጣት ነው የተሸለመው

‎በአቀባበል ስነ ስርዓቱ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ሰራተኞች እንድሁም የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የካምባ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የዓለም ምግብ ፕሮግራም የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወር ስርዓተ-ምግብ ተኮር ተግባራት ግምገማ መድረክ እያካሄደ። ‎አርባ ምንጭ፡ የካቲት 28/2018 ዓ.ም (...
07/03/2026

የካምባ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የዓለም ምግብ ፕሮግራም የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወር ስርዓተ-ምግብ ተኮር ተግባራት ግምገማ መድረክ እያካሄደ።

‎አርባ ምንጭ፡ የካቲት 28/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

በመርሃ ግብሩ ተገኝተው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የወረዳው ዋና አስተዳደርና የስርዓተ-ምግብ ስትርንግ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ አዴ አለሙ እንዳሉት ጤናማ ምግብ ጤናማ ህይወት በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ዉይይት መድረክ ከቃል አልፎ በተግባር ያየንበት ነው ብለዋል።

የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሐንዲሱ በይና በበኩላቸው ፕሮግራሙ በወረዳችን የእናቶችና ህፃናት ስርዓተ-ምግብ ከፍተኛ ትኩረት እየተሰጠ መኖሩን በማሳሰብ ከአምና አፈጻጸም አኳያ ስታይ የስርዓተ-ምግብ ልየታ ሽፋን ለሴቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት በአግባቡ እየተካሄደ መሆኑን አሳስበዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ በሽታ መከላከልና ጤና ማበልጸግ ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ በአቶ ቻለው ንጋቱ በኩል የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ፍኖተ ካርታ አተገባበር ያለበት ደረጃ እና የትራንስፎርሜሽን አጀንዳዎች አተገባበር ላይ ሠነድ ያቀረቡ ሲሆን በቀረበው ሰነድ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡

በመጨረሻም በፕሮግራሙ አፈጻጸም ከፍተኛ አስተዋዕፆ ላበረከቱ ባለድርሻ አካለት ማለትም ለቀበሌ የሴቶች ልማት ቡድን መርዎች፣ለቀበሌ በጎ መልዕክተኞች፣ ለቀበሌ ሊቀነመናብርቶች፣ ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሞያዎች፣ ለጤና ጣቢያ ሥርዓተ-ምግብ ባለሞያዎች፣ ለጤና ጣቢያ ኃላፍዎች፣ ለዓለም ምግብ ፕሮግራም ባለሞያዎችና ለከምባ ዙርያ ወረዳ አስተዳደር የተከበሩ አቶ አዴ አለሙ ጭምር የሥርዓተ-ምግብ ስራን አቀናጅተው በመምራት ከፍተኛ ውጤት እንድመዘገብ ጉልህ ሚና የተጫወቱ በመሆኑ ሽልማትና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል ።

Address

Shecha Sub City, Beside Zone Administration
Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram