Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ

Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ Disease prevention and control
Maternal and child health
Nutrition
Health care financing

ይህ ታሪካዊ ድል የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ለጤና ስርዓቱ መሻሻል ያበረከቱት የላቀ ጥረት ውጤት ነው - ዶ/ር አምባቸው ዱማ‎‎አርባምንጭ፡ የካቲት 29/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ...
08/03/2026

ይህ ታሪካዊ ድል የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ለጤና ስርዓቱ መሻሻል ያበረከቱት የላቀ ጥረት ውጤት ነው - ዶ/ር አምባቸው ዱማ

‎አርባምንጭ፡ የካቲት 29/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ) )

‎​የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል በሀገር አቀፍ ደረጃ በተደረገ የሆስፒታሎች የጥራትና የአገልግሎት አሰጣጥ ግምገማ 3ኛ ደረጃን በመያዝ የሁለት ሚሊዮን ብር ተሸላሚ ሆኗል።

‎ለልኡክ ቡድኑ በተደረገው ደማቅ የአቀባበል ስነስርዓት ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ዋና ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አምባቸው ዱማ ይህ ታሪካዊ ድል የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ለጤና ስርዓቱ መሻሻልና ለታካሚዎች ደህንነት ሌሊትና ቀን ያበረከቱት የላቀ ጥረት ውጤት መሆኑን ገልፀዋል።

‎በሀገር አቀፍ ደረጃ በ90 ሆስፒታሎች መካከል በተደረገው ውድድር ሆስፒታሉ 3ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ የሁሉም ባለድርሻ የነቃ ተሳትፎ መሆኑን ገልፀው ለተገኘው ውጤት አስተዋጽኦ ላደረጉ የክልልና የዞን ጤና መዋቅሮች፣ የቦርድ አባላትና ለመላው የሆስፒታሉ ባለሙያዎች ምስጋና አቅርበዋል።

‎አክለው ሆስፒታሉ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደግሞ የ1ኛ ደረጃን በመያዝ የክልሉና የዞኑ የኩራት ምንጭ መሆኑም ነው ዶ/ር አምባቸው የጠቆሙት።

‎​ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰይፉ ዋናቃ በበኩላቸው ይህ ውጤት ሆስፒታሉ በቀጣይ የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጥ ለአመራሩና ሠራተኛው ትልቅ መነቃቃትን የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።

‎ሆስፒታሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ አዳዲስ አሰራሮችን ወደ ተግባር በመቀየር ለህብረተሰቡ ተደራሽ እየሆነ መምጣቱን ገልፀው ውጤቱ የመተባበር፣ የአንድነትና የላቀ ትጋት ምልክት መሆኑን ተናግረዋል።
‎​
‎​የሆስፒታሉ ምክትል ዳይሬክተር ዶ/ር አዲሱ ተስፋዬ ሆስፒታሉ ቀደም ሲልም በተለያዩ ጊዜያት ተሸላሚ መሆኑን አስታውሰው፣ አሁን የተገኘውን ውጤት ለተሻለ ስራ የሚያነሳሳ ከመሆኑም በላይ ሆስፒታሉ በቀጣይ ይህንን ጥረቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል።


‎ በመድረኩ የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር አምባቸው ዱማ፣የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰይፉ ዋናቃን ጨምሮ የሆስፒታሉ ሠራተኞች እንድሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል

በሀገር አቀፍ ደረጃ የላቀ ውጤት በማስመዝገብ የ2 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ የሆነ አርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ልዑካን ወደ አርባምንጭ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።‎‎አርባምንጭ፡ ...
08/03/2026

በሀገር አቀፍ ደረጃ የላቀ ውጤት በማስመዝገብ የ2 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ የሆነ አርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ልዑካን ወደ አርባምንጭ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

‎አርባምንጭ፡ የካቲት 29/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎ሆስፒታሉ በክልል 1ኛ እንድሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ 3ኛ በመውጣት ነው የተሸለመው

‎በአቀባበል ስነ ስርዓቱ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ሰራተኞች እንድሁም የአርባምንጭ ከተማ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የካምባ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የዓለም ምግብ ፕሮግራም የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወር ስርዓተ-ምግብ ተኮር ተግባራት ግምገማ መድረክ እያካሄደ። ‎አርባ ምንጭ፡ የካቲት 28/2018 ዓ.ም (...
07/03/2026

የካምባ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የዓለም ምግብ ፕሮግራም የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወር ስርዓተ-ምግብ ተኮር ተግባራት ግምገማ መድረክ እያካሄደ።

‎አርባ ምንጭ፡ የካቲት 28/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

በመርሃ ግብሩ ተገኝተው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የወረዳው ዋና አስተዳደርና የስርዓተ-ምግብ ስትርንግ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ አዴ አለሙ እንዳሉት ጤናማ ምግብ ጤናማ ህይወት በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ዉይይት መድረክ ከቃል አልፎ በተግባር ያየንበት ነው ብለዋል።

የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሐንዲሱ በይና በበኩላቸው ፕሮግራሙ በወረዳችን የእናቶችና ህፃናት ስርዓተ-ምግብ ከፍተኛ ትኩረት እየተሰጠ መኖሩን በማሳሰብ ከአምና አፈጻጸም አኳያ ስታይ የስርዓተ-ምግብ ልየታ ሽፋን ለሴቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት በአግባቡ እየተካሄደ መሆኑን አሳስበዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ በሽታ መከላከልና ጤና ማበልጸግ ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ በአቶ ቻለው ንጋቱ በኩል የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም ፍኖተ ካርታ አተገባበር ያለበት ደረጃ እና የትራንስፎርሜሽን አጀንዳዎች አተገባበር ላይ ሠነድ ያቀረቡ ሲሆን በቀረበው ሰነድ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡

በመጨረሻም በፕሮግራሙ አፈጻጸም ከፍተኛ አስተዋዕፆ ላበረከቱ ባለድርሻ አካለት ማለትም ለቀበሌ የሴቶች ልማት ቡድን መርዎች፣ለቀበሌ በጎ መልዕክተኞች፣ ለቀበሌ ሊቀነመናብርቶች፣ ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሞያዎች፣ ለጤና ጣቢያ ሥርዓተ-ምግብ ባለሞያዎች፣ ለጤና ጣቢያ ኃላፍዎች፣ ለዓለም ምግብ ፕሮግራም ባለሞያዎችና ለከምባ ዙርያ ወረዳ አስተዳደር የተከበሩ አቶ አዴ አለሙ ጭምር የሥርዓተ-ምግብ ስራን አቀናጅተው በመምራት ከፍተኛ ውጤት እንድመዘገብ ጉልህ ሚና የተጫወቱ በመሆኑ ሽልማትና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል ።

‎በቦረዳ ወረዳ ለደንገለ ጤና ጣቢያ  ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የመድኃኒትና እና ህክምና መገልገያ መሳርያዎች ግዥ ተፈጽሟል ።‎‎አርባምንጭ፡ የካቲት 28/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መም...
07/03/2026

‎በቦረዳ ወረዳ ለደንገለ ጤና ጣቢያ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የመድኃኒትና እና ህክምና መገልገያ መሳርያዎች ግዥ ተፈጽሟል ።

‎አርባምንጭ፡ የካቲት 28/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎የደንገለ ጤና ጣቢያ ለማህበረሰቡ የሚሰጠውን አግልግሎት ለማሳለጥ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የመድኃኒትና እና ህክምና መገልገያ መሳርያዎች ግዥ ተፈጽሟል ።

‎ላለፍት በርካቲ ዓመታት በክላስተር ጤና ኬላ በመባል በዘፍኔ ጤና ጣቢያ ስር ሲተዳደር የቆዬው የደንገለ ጤና ጣቢያ የጤና ፍትሃዊነትን እና ተደራሽነትን ለማህበረሰቡ ተደራሽ ለማድረግ የተያዘውን ዕቅድ ለማስፈጸም የወረዳው መንግስት በወሰነው ውሳኔ መሠረት ወደ ጤና ጣቢያ አድጓል ።

‎በዝህ መሰረት የጤና ጣቢያውን የውስጥ አቅም ለማሳደግ በተሰጠው ድጎማ በጀት ለጤና ጣቢያ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የመድኃኒትና እና ህክምና መገልገያ መሳርያዎች ግዥ ተፈጽሟል ።

‎ምንጭ፡-የቦረዳ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት

በአርባምንጭ ከተማ ሼቻ ጤና  ጣቢያ ከየካቲት  29/2018 ዓ.ም  ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት  ነፃ የህክምና አገልግሎት  እንደሚሰጥ ተገለፀ‎‎አርባምንጭ፡ የካቲት 28/2018 ዓ.ም (የ...
07/03/2026

በአርባምንጭ ከተማ ሼቻ ጤና ጣቢያ ከየካቲት 29/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት ነፃ የህክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገለፀ

‎አርባምንጭ፡ የካቲት 28/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ): )

‎"ጀውሽ ቮይስ ሚኒስትሪስ ኢንተርናሽናል" የተሰኘ አለም ዓቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅት ልዑክ አርባምንጭ ከተማ ተገኝቷል።

‎ልዑኩ በሼቻ ጤና ጣቢያ ከየካቲት 29 ቀን ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት በአርበምንጭ ከተማ ጤና መምሪያ አስተባባሪነት ነፃ የህክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ ተመላክቷል።

‎የሼቻ ጤና ጣቢያ ኃላፊ ዶ/ር በረከት ባሻ በድርጅቱ የህክምና አገልግሎት የሚሰጡ ከ100 በላይ የውጪ ሀገር እና የሀገር ውስጥ የህክምና ባለሙያዎች ነፃ አገልግሎት ለመስጠት መገኘታቸውን ተናግረዋል።

‎አገልግሎቱ በሼቻ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ከየካቲት 29/2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 2/2018ዓ.ም የሚሰጥ እንደሆነም ዶ/ር በረከት ተናግረዋል።

‎የአርባምንጭ ከተማ ጤና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር አንተነህ ካሳዬ በአገልግሎቱ ከ10ሺህ በላይ ህብረተሰብ ተጠቃሚ ይሆናል ብለዋል።

‎ ማህበረሰቡ በተቀመጠው ጊዜ እና ቦታ በመገኘ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ጥሪ አስተላልፈዋል።

‎አገልግሎቱን ለመስጠት በስፍራው ለተገኘው ልዑክ ዶ/ር አንተነህ ምስጋናም አቅርበዋል።

‎ነፃ አገልግሎቱ የጥርስ፣የአይን፣የውስጥ ደዌ አገልግሎቶችን ጨምሮ ሌሎችን የህክምና አገልግሎቶችም ማካተቱ ተመላክቷል።

የገረሴ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቦርድ  የ2018 ዓ/ም  ስድስት ወር የስራ  አፈጻጸም ግምገማ መድረክ አካሄደ።‎‎አርባምንጭ፡ የካቲት 28/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ): )‎‎በ...
07/03/2026

የገረሴ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቦርድ የ2018 ዓ/ም ስድስት ወር የስራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ አካሄደ።

‎አርባምንጭ፡ የካቲት 28/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ): )

‎በጋሞ ዞን የገረሴ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቦርድ የ2018 ዓ/ም ስድስት ወር የስራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ዛሬ ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሄደ።

‎በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጋሞ ዞን ሲቪል ሴርቪስ መምሪያ ኋላፊና የገረሴ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቦርድ ዋና ሰብሳቢ አቶ መኮንን ቶንቼ በስድስት ወር ውስጥ የሚታይና የምያረካ ስራ በሆስፒታሉ እንደተሰራ ጠቁመው ቦርዱ በቀጣይነት ይህን ሆስፒታል በበቂ ሁኔታና በዘላቂነት አገልግሎት እንዲሰጥ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

‎በሆስፒታሉ በስድስት ወራት የተሰሩ ስራዎችንና አገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱን ቦርዱ ምልከታ ያደረገ ሲሆን የምርመራ ክፍሎችና ሌሎች አገልግሎቶች በተሟላ መልኩ አገልግሎት እንድሰጡ እየተደረገ ያለው ጥረት አበረታች መሆኑን የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኋላፊ አቶ ሰይፋ ዋናቃ ገልጸዋል።

‎አክለውም የጋልማ ፋርማሲ አገልግሎትን ከማዐጠሜ ጋር በማስተሳሰር በሆስፒታሉ የመድሃኒት እጥረት በምያጋጥም ወቅት ህብረተሰቡ ለችግር ሳይጋለጥ በማዐጠመ ከጋልማ ገረሴ ቅርንጫፍ ማህበረሰብ ፓርማሲ አገልግሎት ማግኘት እንዲችል በቀጣል ሊሰራ ይገባል ብለዋል።

‎በምልከታውም የገረሴ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ወንድወሰን ወርቁ እንደገለጹት፦ ሆስፒታሉ ለህብረተሰቡ መደበኛ አገልግሎት እንዲሰጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየሰራን የቆየን ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚታይ ለውጥም ተሰርቷል ብለዋል።

‎የሆስፒታሉን የውስጥ ገቢን በማሳደግና የማህበረሰቡን የጤና አገልግሎት ችግር እየፈታ ይገኛል ያሉት ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ወንድወሰን በዚህ ስድስት ወር 3.6 ሚሊዮን ብር በላይ መድኋኒት ግዢ መፈጸሙን ገልጸዋል።

‎አሁንም በሆስፒታሉ የሚታዩ ጉድለቶችን ለማሟላት የባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደምያስፈልግ የጠቆሙት ስራ አስኪያጁ የትርፍ ሰዓት ክፍያና የቴክኖሎጂ ውጤቶች እጥረት ትኩረት ሊሰጥ ይገባልም ብለዋል።

‎የገረሴ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር አወቀ አለሙ በበኩላቸው አሁን ላይ ሆስፒታሉ በበቂ ሁኔታ በሚል ደረጃ ላይ ባይገኝም የተሻለ ደረጃ ላይ ነው በምያሰኝ ለማህበረሰቡ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ገልጸው ሆስፒታሉ ካለበት ደረጃ እንዲሻሻል የበኩላቸውን ለተወጡ ባለድርሻ አካላትን አመስግነዋል።

‎በመድረኩ የጋሞ ዞን ሲቪል ሴርቪስ መምሪያ ኋላፊና የገረሴ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቦርድ ዋና ሰብሳቢ አቶ መኮንን ቶንቼ፣ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኋላፊ አቶ ሰይፋ ዋናቃ የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ቦርሴ ቦታና የገረሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ኤርሚያስ እሸቱን ጨምሮ ሌሎች የቦርድ አባላትና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል።

በጋሞ ዞን ቁጫ አልፋ ወረዳ ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ‎‎አርባምንጭ፡ የካቲት 27/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ): )‎‎በጋሞ ዞን ቁጫ አልፋ ወረዳ በመንግ...
06/03/2026

በጋሞ ዞን ቁጫ አልፋ ወረዳ ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ

‎አርባምንጭ፡ የካቲት 27/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ): )

‎በጋሞ ዞን ቁጫ አልፋ ወረዳ በመንግስትና በህብረተሰበ ተሳትፎ ከ3.5 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ የተደርጎበት ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ።

‎ለምረቃ የበቃው ሁሉ አቀፍ ጤና ኬላ ከ3.5 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ የተደረገበትና 5 ሺህ ለሚሆኑ የአከባቢ ነዋሪዎች አገልግሎት የሚሰጥ እንደሆነም ተጠቁሟል።


‎በምረቃው የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ ፣ የዞኑ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ገዛሀኝ ጋሞ፣ የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሴይፉ ዋናቃን ጨምሮ እንዲሁም የዞን እና የወረዳው ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

እንኳን ደስ አለን! አርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል በሀገር አቀፍ ደረጃ የላቀ ውጤት በማስመዝገብ የ2 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ ሆነ​በአራተኛው ዙር የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ጥምረት ለጥራት (EHAQ)...
06/03/2026

እንኳን ደስ አለን! አርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል በሀገር አቀፍ ደረጃ የላቀ ውጤት በማስመዝገብ የ2 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ ሆነ

​በአራተኛው ዙር የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች ጥምረት ለጥራት (EHAQ) ግምገማ የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የላቀ የሥራ አፈፃፀም በማስመዝገብ በሀገር አቀፍ ደረጃ የ3ኛ ደረጃን በመያዝ ታሪካዊ ስኬት ተቀዳጅቷል።

​ይህ ስኬት ሆስፒታላችንን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብቸኛው ተሸላሚ በማድረግ በግንባር ቀደምትነት አቁሞታል።

​ለጤና ሥርዓቱ መሻሻል ላበረከተው ከፍተኛ አስተዋጽኦ
​የድል ዋንጫ፣የዕውቅና የምስክር ወረቀትእና​2,000,000 (ሁለት ሚሊዮን) ብር የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶለታል ።

የተቋሙ ዋና ሥራ አስኪያጅ​ ዶክተር አምባቸው ዱማ በድሉ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው፤ "ይህ ስኬት የሁላችንም የጋራ ጥረትና የቆራጥ አመራር ውጤት መሆኑን ገልፀው ለመላው የሆስፒታሉ ማህበረሰብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

አክለውም ይህ ሽልማት ለቀጣይ የተሻለ አገልግሎትና ለላቀ የጥራት ደረጃ ይበልጥ እንድንተጋ ትልቅ ብርታት እንደሚሆን ገልጸዋል።

ለዚህ ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከታችሁ የጤና ባለሙያዎች፣ የአመራር አካላትና ደጋፊ ሰራተኞች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በጋሞ ዞን ሲያካሂድ የነበረውን ድጋፋዊ ክትትል አጠናቀቀ‎‎አርባምንጭ፡ የካቲት 27/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ): ‎‎የክለሉ ...
06/03/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በጋሞ ዞን ሲያካሂድ የነበረውን ድጋፋዊ ክትትል አጠናቀቀ

‎አርባምንጭ፡ የካቲት 27/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ):

‎የክለሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የበጀት አመቱን የግማሽ ዓመት ድጋፋዊ ክትትል በጋሞ ዞን እያካሄደ ቆይቷል።

‎በድጋፋዊ ክትትሉ ሁለት ወረዳዎች አራት ጤና ጣቢያዎች፣ ስምንት ጤና ኬላዎች፣ እንዲሁም ከአርባ በላይ ቤተሰቦች ጉብኝት ተደርጎባቸዋል።

‎የድጋፋዊ ክትትሉ ግብረ-መልስ በሚሰጥበት ወቅት የመምሪያው ም/ኃላፊ ወ/ር ባንጌ ባንጃ እንዲሁም የመምሪያው ክፍተኛ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

‎በመጨረሻም በግብረ መልሱ የተሰጡ ጠንካራ ጎኖች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ እና በድክመት የተገመገሙ ጉዳዮች ይጠናከራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ጤና ሚኒስቴር በመላው ኢትዮጵያ የጤና አገልግሎት አቅርቦትን እና የቀዝቃዛ ሰንሰለት ስርዓቶችን ለማጠናከር የፀሐይ ኤሌክትሪክ መሳሪያዎችን እና ሞተር ሳይክሎችን ለክልል የጤና ቢሮዎች አስረክቧ...
06/03/2026

ጤና ሚኒስቴር በመላው ኢትዮጵያ የጤና አገልግሎት አቅርቦትን እና የቀዝቃዛ ሰንሰለት ስርዓቶችን ለማጠናከር የፀሐይ ኤሌክትሪክ መሳሪያዎችን እና ሞተር ሳይክሎችን ለክልል የጤና ቢሮዎች አስረክቧል።

‎አርባምንጭ፡ የካቲት 27/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ):

‎በርክክብ መርሃ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ይህ ተነሳሽነት በጤና ተቋማት ውስጥ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያሰፋ ተናግረዋል። 380 የጤና ተቋማት የፀሐይ ኤሌክትሪክ ሃይል አገልግሎት ያገኛሉ፤ ይህም ያልተቋረጡ አገልግሎቶችን ለማረጋገጥ ይረዳቸዋል ብለዋል። ሚኒስትሯ በተጨማሪም 1,183 በሃገር ውስጥ የተገጣጠሙ ሞተር ሳይክሎች ለመድረስ አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ክትባቶችን እና መድሃኒቶችን ለማድረስ እንደሚደግፉ አፅንኦት ሰጥተዋል።

‎ዶ/ር መቅደስ መንግስት ለአየር ንብረት ተፅዕኖ የማይበገር የጤና ተቋማትን ለመገንባት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፤ እንዲሁም ሚኒስቴሩ የኢትዮጵያን የጤና ስርዓት ለማጠናከር ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር መስራቱን እንደሚቀጥል ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠው፤ ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

‎የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ ፕሮጀክቱ በተለይም በገጠር አካባቢዎች በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያሉ የፍትሃዊነት ክፍተቶችን ለመፍታት ይረዳል ብለዋል። ታዳሽ እና ዘላቂ የኃይል መፍትሄዎችን መጠቀም የጤና ዘርፉን ለማጠናከር እና የእናቶች እና የህፃናት ጤና አገልግሎቶችን ለማሻሻል አስፈላጊ መሆኑን አክለዋል። የክልል የጤና ቢሮዎች የተበረከቱትን መሳሪያዎች በአግባቡ እንዲጠቀሙ እና እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርበዋል።

‎የዩኒሴፍ የኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ ተወካይ ዶ/ር አቡባካር ካምፖ ርክክቡ አገሪቱ የጤና አገልግሎቶችን ለማሻሻል እና በጤና ተቋማት ውስጥ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ለማስፋፋት ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል። ኢትዮጵያ በጤና ዘርፉ ውስጥ የታዳሽ የኃይል መፍትሄዎችን በመተግበር ረገድ አስፈላጊ እርምጃዎችን እየወሰደች መሆኑን ተናግረዋል።

‎የውሃ እና የኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ዋሊ የአገሪቱን ሰፊ የታዳሽ የኃይል አቅም አጉልተው ገልጸው፤ መንግስት ከኃይል ማመንጫ ውጭ በሚታደሱ የኃይል ስርዓቶች አማካኝነት የሀገር ውስጥ የኃይል ፍላጎትን ለማሟላት አቅዷል ብለዋል። የጤና ተቋማት የፀሐይ ኃይል ኤሌክትሪክ ፕሮጀክት ከኢትዮጵያ ሰፊ የልማት አጀንዳ ጋር የሚጣጣም መሆኑን አክለዋል።

‎የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የማህበራዊ፣ የባህልና የስፖርት ቋሚ ኮሚቴ ሊቀመንበር ወርቅሰሙ ማሞ ጤና ሚኒስቴር የእናቶችና የህፃናት ጤና አገልግሎቶችን ለማሻሻል ላሳየው ቁርጠኝነት ምስጋና አቅርበዋል። ሚኒስቴሩ የእናቶችና የህፃናት ሞትን በመቀነስ ረገድ ላከናወናቸው ስኬቶች እውቅና ሰጥተዋል።

‎በሥነ ሥርዓቱ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የፀሐይ ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫዎችን እና ሞተር ሳይክሎችን ለክልል ጤና ቢሮዎች በይፋ አስረክበዋል።

‎ምንጭ፡-ጤና ሚኒስቴር

በድቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2018 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የጤና ፕሮግራሞችና ኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ የተግባር አፈጻጸም ግምገማ በአሪ ዞን ጂንካ ከተማ ማካሄድ ጀመረ።...
05/03/2026

በድቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ2018 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የጤና ፕሮግራሞችና ኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ የተግባር አፈጻጸም ግምገማ በአሪ ዞን ጂንካ ከተማ ማካሄድ ጀመረ።

የአኗኗር ዘይቤያችንን በማዘመን ተላላፈና ተላለፊ ያልሆኑ በሽታዎችን መከላከል እንደሚገባም የክልሉ ጤና ቢሮ አስታውቋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ መና መኩሪያ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደተደመጡት የእናቶች ጤና፣ የህፃናት ክትባ፣ ሥርዓተ ምግብና አጠቃላይ በሽታ መከላከል ዘርፎች ዙሪያ የታዮ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል ውስንነቶችን በማረን የዜጎችን ጤና ልንጠብ ይገባል ብለዋል።

የጤና ኤክስተንሽን ፕሮግራሞችን በሁሉም የክልላችን አካባቢዎች በመተግበር ህዝባችንን የጤና ተጠቃሚ ለማድረግም ሁሉም ዞንና ሪጂኦ ፖሊሲ ከተሞች በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ተብራርቷል።

የኤች አይ ቪ በሽታ ቁጥጥር በበለጠ ትኩረት በመስራትና በወገኖች ላይ የሚደረግ ማግለልና መድሎን በጋራ መከላከል ይገባል ብለዋል።

የህጻናት የምግብ እጥረት ልየታ በማድረግ በምግብ እጥረት የተጎዱ ህጻናትን ወዲያዉኑ ህክምና ተቋም በመውሰድ ቨመጤናቸው እንዲጠበቅ ማድረግ እንደሚገባ አቶ መና አሳስበዋል።

ፅዱ አከባቢ፣ ፅዱ ከተማ፣ ፅዱ ክልልና ፅዱ ኢትዮጵያን ለጤናችን! ሁሉም በባለቤትነት መስራት እንደሚገባ አቶ መና በመክፈቻ ንግግራቸው ተደምጠዋል።

ምንጭ፡-ጤና ቢሮ ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

 #የስራ   #የዝውውር  #ማስታወቂያየኢትዮጵያ ምግብ መድኃኒት ባለስልጣን ከዚህ በታች በተገለጸው ክፍት የስራ መደብ ላይ መስፈርቱን የምታሟሉ ሰራተኞችን አዛውሮ በቋሚነት ማሰራት ይፈልጋል
03/03/2026

#የስራ #የዝውውር #ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ምግብ መድኃኒት ባለስልጣን ከዚህ በታች በተገለጸው ክፍት የስራ መደብ ላይ መስፈርቱን የምታሟሉ ሰራተኞችን አዛውሮ በቋሚነት ማሰራት ይፈልጋል

Address

Shecha Sub City, Beside Zone Administration
Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram