Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ

Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ Disease prevention and control
Maternal and child health
Nutrition
Health care financing

 #የሥራ ማስታወቂያ
04/05/2026

#የሥራ ማስታወቂያ

 #ማስታወቂያ
04/05/2026

#ማስታወቂያ

በዞኑ ከ 290 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ህፃናት የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት መሠጠት መቻሉ ተነገረ፤‎‎አርባ ምንጭ፡- ሚያዝያ 26/2018 ዓ/ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)‎‎የጋሞ ዞን ጤና መም...
04/05/2026

በዞኑ ከ 290 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ህፃናት የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት መሠጠት መቻሉ ተነገረ፤

‎አርባ ምንጭ፡- ሚያዝያ 26/2018 ዓ/ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የ5ኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ የሶስተኛ ቀን አፈጻጸምን ገምግሟል፡፡ በዘመቻው በሶስት ቀናት ውስጥ በአጠቃላይ ለ 293 ሺህ 885 ህጻናት የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት መስጠት ተችሏል ይህም አንደ ዞን በሽፋን ደረጃ 88 በመቶ ያህል መፈጸሙን ከቀረበው ሪፖርት መረዳት ተችሏል፡፡ በአጠቃላይ ክትባት ያልጀመሩ ህጻናት ዜሮ ዶዝ (ፔንታ 1) 1 መቶ 11 ህጻናትን እንዲከተቡ ተደርጓል፡፡

‎ከስርዓተ ምግብ አገልግሎት ጋር በተያያዘ ከ 5 ዓመት በታች ለሆናቸው ህጻናት የሥርዓተ-ምግብ ልዬታ አገልግሎት ለ 235 ሺህ 714 ሕጻናት ልዩታ ተካሂዶ በክፍተኛ የምግብ እጥት 2 መቶ 13 ሕጻናት ተለይተው ተገቢውን ሕክምና እንዲያገኙ ወደ ጤና ተቋም ሪፈር ተደርገዋል፡፡ አጥቢና ነፍሰጡር እናቶች የስርዓተ-ምግብ ልዬታ ለ 40 ሺህ 875 ለሚሆኑ አጥቢና ነፍሰጡር እናቶች ልየታ ተካሂዷል፡፡

‎የፌስቱላ ችግር ያለባቸው ሴቶች ከ ጨንቻ ዙሪያ ወረዳ 3፣ ከ ጋጮ ባባ ወረዳ 4፣ ከ ገረሴ ዙሪያ 2፣ ከቆጎታ ወረዳ 1 እና ከቁጫ አልፋ ወረዳ 1 በአጠቃላይ 11 እናቶች ተለይዋል፡፡ ቆልማማ የእግር ችግር ያለባቸው ህጻናት ከ ብርብር ከተማ ወረዳ 1፣ ከዲታ ወረዳ 3፣ ከቆጎታ ወረዳ 1፣ ከቁጫ ወረዳ 2 እንዲሁም ከቁጫ አልፋባ ወረዳ 1 በአጠቃላይ 9 ሕጻናት ተለይተዋል፡፡

‎በቀጣይ የዘመቻው ቀናት የቆልማማ እግር ችግር ያለባቸውን፣ የከንፈር እና የላንቃ ስንጥቅ ያለባቸውን ሕጻናት የመለዬት ስራ በሁሉም መዋቅሮች በተደራጀ መልኩ ከዘመቻው ጋር አቀናጅቶ ሊተገበር ይገባል ተብሏል፡፡ የዜሮ ዶዝ ክትባት ተደራሽ ከማድረግ ጋር በተያያዘ በሁሉም መዋቅሮች በዘመቻው ሶስት ቀናት ውስጥ ውስን መዋቅሮች ቢቻ ሪፖርት ያደረጉ ሲሆን በሁሉም መዋቅሮች ተግባራቱ በተጠናከረ መልኩ ሊቀጥሉ የሚገባ እና የአፈጻጸም መረጃ በቀበሌ ደረጃ በማደራጀት ለዞን ሪፖርት ማድረግ አንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡

‎የክትባት አሰጣጡን ጥራት ለማስጠበቅ ሁሉም ባለሙያዎች ለድጋፍ በሄዱበት አከባቢ ላይ በODK መረጃ ዙሪያ ትኩረት መስጠት፣ የቤት ምልክት ኮድ ማድረግ እንዲሁም ክትባት የወሰዱ ሕጻናት ጣት ላይ የሚደረገው ምልክት በሚፈለገው መልኩ በየደረጃው ተግባራዊ ሊደረግ ይገባል፡፡ የልጅነት ልምሻ በሽታ አሰሣ ከዘመቻው ጋር ከመቸውም ጊዜ በላይ ተቀናጅቶ ሊተገበር ይገባል ተብሏል፡፡

‎የወባ በሽታ የመከላከልና የመቆጣጠር ተግባራት በተለይ የመኝታ አጎበር አጠቃቀም፣ ትኩሳት ያለባቸውን ግለሰቦች የመለየት የመመርመር እና የማከም ተግባራት ከክትባት ዘመቻው ጋር ተቀናጅተው ሊተገበሩ ይገባል ተብሏል።

‎በናዳ ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚሰጠው ሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት በተደራጀ መልኩ እየተሰ ጠመሆኑ ተመላክቷል።

‎በዘመቻው የጋራ ግብረ-ሃይል ግምገማ መድረክ ላይ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሴይፉ ዋናቃ፣ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ባንጌ ባንጃ ጨምሮ የመምሪያዉ የዘመቻዉ ግብረ-ሃይል አባላት፣ ከክልሉ ጤና ቢሮ እና ከአጋር ድርጅቶች ለድጋፍ የተመደቡ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

በጋሞ ዞን 5ኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተነገረ፤‎‎አርባ ምንጭ፡- ሚያዝያ 25/2018 ዓ/ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)‎‎የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ...
03/05/2026

በጋሞ ዞን 5ኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተነገረ፤

‎አርባ ምንጭ፡- ሚያዝያ 25/2018 ዓ/ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የ5ኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ የሁለተኛ ቀን አፈጻጸምን ገምግሟል፡፡ በዘመቻው በሁለት ቀናት ውስጥ በአጠቃላይ ለ 197 ሺህ 606 ህጻናት የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት መስጠት ተችሏል ይህም አንደ ዞን በሽፋን ደረጃ 59 በመቶ ያህል መፈጸሙን ከቀረበው ሪፖርት መረዳት ተችሏል፡፡ በአጠቃላይ ክትባት ያልጀመሩ ህጻናት ዜሮ ዶዝ (ፔንታ 1) 94 ህጻናትን እንዲከተቡ ተደርጓል፡፡

‎ከስርዓተ ምግብ አገልግሎት ጋር በተያያዘ ከ 5 ዓመት በታች ለሆናቸው ህጻናት የሥርዓተ-ምግብ ልዬታ አገልግሎት ለ 178 ሺህ 856 ሕጻናት ልዩታ ተካሂዶ በክፍተኛ የምግብ እጥት 141 ሕጻናት ተለይተው ተገቢውን ሕክምና እንዲያገኙ ወደ ጤና ተቋም ሪፈር ተደርገዋል፡፡ አጥቢና ነፍሰጡር እናቶች የስርዓተ-ምግብ ልዬታ ለ 23 ሺህ 825 ለሚሆኑ አጥቢና ነፍሰጡር እናቶች ልየታ ተካሂዷል፡፡ ቆልማማ የእግር ችግር ያለባቸው ህጻናት ከ ዲታ ወረዳ 2፣ ከቆጎታ ወረዳ 1፣ ከቁጫ አልፋ ወረዳ 1 በአጠቃላይ 4 ሕጻናት ተለይተዋል፡፡

‎በቀጣይ የዘመቻው ቀናት የቆልማማ እግር ችግር ያለባቸውን፣ የከንፈር እና የላንቃ ስንጥቅ ያለባቸውን ሕጻናት የመለዬት ስራ በሁሉም መዋቅሮች በተደራጀ መልኩ ከዘመቻው ጋር አቀናጅቶ ሊተገበር ይገባል ተብሏል፡፡ የዜሮ ዶዝ ክትባት ተደራሽ ከማድረግ ጋር በተያያዘ በሁሉም መዋቅሮች በዘመቻው ሁለት ቀናት ውስጥ ውስን መዋቅሮች ቢቻ ሪፖርት ያደረጉ ሲሆን በሁሉም መዋቅሮች ተግባራቱ በተጠናከረ መልኩ ሊቀጥሉ የሚገባ እና የአፈጻጸም መረጃ በቀበሌ ደረጃ በማደራጀት ለዞን ሪፖርት ማድረግ አንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡

‎የክትባት አሰጣጡን ጥራት ለማስጠበቅ ሁሉም ባለሙያዎች ለድጋፍ በሄዱበት አከባቢ ላይ በODK መረጃ ዙሪያ ትኩረት መስጠት፣ የቤት ምልክት ኮድ ማድረግ እንዲሁም ክትባት የወሰዱ ሕጻናት ጣት ላይ የሚደረገው ምልክት በሚፈለገው መልኩ በየደረጃው ተግባራዊ ሊደረግ ይገባል፡፡ የልጅነት ልምሻ በሽታ አሰሣ ከዘመቻው ጋር ከመቸውም ጊዜ በላይ ተቀናጅቶ ሊተገበር ይገባል ተብሏል፡፡ ሁሉም ዓይነት ሪፖርት ተገምግሞ በተቀመጠው ጊዜ ገደብ ውስጥ ለዞን ሊደርስ ይገባል ተብሏል።

‎የወባ በሽታ የመከላከልና የመቆጣጠር ተግባራት በተለይ የመኝታ አጎበር አጠቃቀም፣ ትኩሳት ያለባቸውን ግለሰቦች የመለየት የመመርመር እና የማከም ተግባራት ከክትባት ዘመቻው ጋር ተቀናጅተው ሊተገበሩ ይገባል ተብሏል።

‎በዘመቻው የጋራ ግብረ-ሃይል ግምገማ መድረክ ላይ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሴይፉ ዋናቃ፣ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ባንጌ ባንጃ ጨምሮ የመምሪያዉ የዘመቻዉ ግብረ-ሃይል አባላት፣ ከክልሉ ጤና ቢሮ እና ከአጋር ድርጅቶች ለድጋፍ የተመደቡ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ በዞኑ እየተካሄደ የሚገኘውን 5ኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ዘመቻ የመጀመሪያ ቀን ውሎ አፈጻጸምን ገመገመ፣‎‎አርባ ምንጭ፡- ሚያዝያ  24/2018 ዓ/ም (...
02/05/2026

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ በዞኑ እየተካሄደ የሚገኘውን 5ኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ዘመቻ የመጀመሪያ ቀን ውሎ አፈጻጸምን ገመገመ፣

‎አርባ ምንጭ፡- ሚያዝያ 24/2018 ዓ/ም (የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ)

‎የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ የ5ኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ የመጀመሪያ ቀን አፈጻጸምን ገምግሟል፡፡ በመጀመሪያ የዘመቻ ማስጀመሪያ ቀን ዘመቻው በሁሉም የዞኑ መዋቅሮች መጀመሩ ታውቋል። በዘመቻው የመጀመሪያ ቀን በአጠቃላይ ለ 85 ሺህ 269 ህጻናት የፖሊዮ በሽታ መከላከያ ክትባት መስጠት ተችሏል ይህም አንድ ዞን በሽፋን ደረጃ 26 በመቶ ያህል መፈጸሙን የቀረበው ሪፖርት አመላክቷል፡፡ በአጠቃላይ ክትባት ያልጀመሩ ህጻናት ዜሮ ዶዝ (ፔንታ 1) ለ 47 ህጻናትን ተደራሽ ማድረግ ተችሏል፡፡

‎ከስርዓተ ምግብ አገልግሎት ጋር በተያያዘ ከ 5 ዓመት በታች ለሆናቸው ህጻናት የሥርዓተ-ምግብ ልዬታ አገልግሎት ለ 71 ሺህ 316 ሕጻናት ልዩታ ተካሂዶ በክፍተኛ የምግብ እጥት 82 ሕጻናት ተለይተው ተገቢውን ሕክምና እንዲያገኙ ወደ ጤና ተቋም ሪፈር ተደርገዋል፡፡ አጥቢና ነፍሰጡር እናቶች የስርዓተ-ምግብ ልዬታ ለ 10 ሺህ 783 ልየታ ተካሂዷል፡፡

‎በቀጣይ የዘመቻው ቀናት የቆልማማ እግር ችግር ያለባቸውን፣ የከንፈር እና የላንቃ ስንጥቅ ያለባቸውን ሕጻናት የመለዬት ስራ በሁሉም መዋቅሮች በተደራጀ መልኩ ከዘመቻው ጋር አቀናጅቶ ሊተገበር ይገባል ተብሏል፡፡ የዜሮ ዶዝ ክትባት ተደራሽ ከማድረግ ጋር በተያያዘ በሁሉም መዋቅሮች በዘመቻው የመጀመሪያ ቀን ዝቅተኛ አፈፃፀም የተመዘገበበት በመሆኑ በየደረጃው በትኩረት ሊተገበር ይገባል፡፡

‎የክትባት አሰጣጡን ጥራት ለማስጠበቅ ሁሉም ባለሙያዎች ለድጋፍ በሄዱበት አከባቢ ላይ በODK መረጃ ዙሪያ ትኩረት መስጠት፣ የቤት ምልክት ኮድ ማድረግ እንዲሁም ክትባት የወሰዱ ሕጻናት ጣት ላይ የሚደረገው ምልክት በሚፈለገው መልኩ በየደረጃው ተግባራዊ ሊደረግ ይገባል፡፡ የልጅነት ልምሻ በሽታ አሰሣ ከዘመቻው ጋር ተቀናጅቶ ሊተገበር ይገባል ተብሏል፡፡

‎የወባ በሽታ የመከላከልና የመቆጣጠር ተግባራት በተለይ የመኝታ አጎበር አጠቃቀም፣ ትኩሳት ያለባቸውን ግለሰቦች የመለየት የመመርመር እና የማከም ተግባራት ከክትባት ዘመቻው ጋር ተቀናጅተው ሊተገበሩ ይገባል ተብሏል።

‎በመጨራሻም የሪፖርት ጥራት እና ወቅታዊነት፣ አገልግሎት ላይ የዋሉ ብልቃጦችን በሙሉ ወደ ጤና ተቋም የመመለስ ተግባር፣ የቀን ውሎ አፈጻጸሞችን ወደ Google Sheet የማስገባት ተግባር እንዲሁም በየደረጃው የሚደረገው የቀን ውሎ አፈጻጸም ተግባር ትኩረት ሊቸረው ይገባል ተብሏል፡፡

‎በዘመቻው የጋራ ግብረ-ሃይል ግምገማ መድረክ ላይ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሴይፉ ዋናቃ፣ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ባንጌ ባንጃ ጨምሮ የመምሪያዉ የዘመቻዉ ግብረ-ሃይል አባላት፣ ከክልሉ ጤና ቢሮ እና ከአጋር ድርጅቶች ለድጋፍ የተመደቡ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

በጋሞ ዞን አምስተኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት መሰጠት ተጀመረ‎‎አርባ ምንጭ፡- ሚያዝያ 23/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምርያ ) ‎‎ዞናዊ የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ማስጀመሪያ...
01/05/2026

በጋሞ ዞን አምስተኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት መሰጠት ተጀመረ

‎አርባ ምንጭ፡- ሚያዝያ 23/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምርያ )

‎ዞናዊ የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር የተካሄደው በገረሴ ከተማ አስተዳደር ዛዚኤ ቀበሌ የተፈጥሮ አደጋ ተፈናቃዮች በሚገኙበት ስፍራ ነው።

‎የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ እና የአስተዳዳሪው ልዩ አማካሪ አቶ ተስፋጽዮን ዘነበ በስፍራው ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት መንግስት የህፃናትን ህመምና ሞት ለመቀነስ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

‎ፖሊዮ ህፃናትን ለህመምና ለሞት ከመዳረጉም ባሻገር የሚያስከትለው ማትበራዊ ቀውስ ከፍተኛ መሆኑንም አቶ ተስፋጽዮን ገልፀዋል።

‎ክትባቱ ህፃናትን ከተለያዩ በሽታዎች እንደሚከላከል የገለፁት አማካሪው እድሚያቸው ለክትባት የደረሱ ህፃናት እንዲከተቡ ወላጆችና አሳዳጊዎች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡም አሳስበዋል።

‎የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰይፉ ዋናቃ በበኩላቸው በዘመቻው ዕድሜያቸው ለክትባት የደረሱ ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ከ251 ሺህ በላይ ህጻናትን ለመከተብ መታቀዱን አብራርተዋል።

‎በዘመቻው ክትባት ጀምረው ያቋረጡትና ያልጀመሩ ህፃናት የሚያካትቱ መሆኑን ያሳወቁት አቶ ሰይፉ ጥራቱንና ተደራሽነቱን በጠበቀ መልኩ ለመፈፀም መትጋት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

‎በዘመቻው ከክትባቱ ባሻገር የማህፀን ውልቃት ችግር ያጋጠማቸውን እናቶች እንዲሁም የከንፈርና የላንቃ መሰንጠቅ፣ የስርዓተ ምግብ ችግር ያለባቸውን እና መሰል የጤና ችግር የመለየት ስራዎች በትኩረት እንደሚከናወኑ ኃላፊው አብራርተዋል።

‎የገረሴ ከተማ አስተዳደር ም/ ከንቲባና የማዘጋጃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉነት ሙዳ እንደተናገሩት በከተማ አስተዳደሩ 7ሺህ 414 እድሜያቸው ለክትባት የደረሱ ህፃናትን ለማስከተብ እቅድ መያዛቸውንና ቅድመ ዝግጅት ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።

‎አመራሮቹ በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ዛዚኤ ቀበሌ ተጠልለው የሚገኘኙ የህብረተሰብ ክፍሎችንም ጎብኝተዋል።

‎በዞኑ በሚገኙ በሁሉም መዋቅሮች ድዕድሜያቸው ለክትባት የደረሱ ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት ለሚቀጥሉ 4 ተከታታይ ቀናት ክትባቱ እንደሚሰጥ ተመላክቷል።

‎በመርሃ -ግብሩ የዞን እና የገረሴ ከተማ አስተዳደር አመራሮችን ጨምሮ የአከባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

01/05/2026
የአደጋ ተጎጅዎችን ጤና በዘላቂነት ለመጠበቅ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ‎‎አርባ ምንጭ፡- ሚያዝያ 23/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምርያ ) ‎  ‎በናዳ ምክንያት ለተፈናቀሉ ...
01/05/2026

የአደጋ ተጎጅዎችን ጤና በዘላቂነት ለመጠበቅ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ

‎አርባ ምንጭ፡- ሚያዝያ 23/2018 ዓ.ም (የጋሞ ዞን ጤና መምርያ )

‎በናዳ ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚሰጠው ሁሉ አቀፍ የጤና አገልግሎት ተጠናክሮ መቀጠሉ ተነግፘል።

‎በጊዚያዊ መጠለያ ለተጠለሉ ወገኖች በተቋቋመው ጊዚያዊ ክሊኒክ የሚሰጠው አገልግሎት በተጠናከረ መልኩ መቀጠሉ በሪፖርት ተመላክቷል። በዚህም 1 ሺህ 576 ሰዎች የህክምና አገልግሎት፣ 10 ሰዎች የቲቢ በሽታ ምልክት አሳይተው የአክታ ምርመራ ተደርጎላቸው በ 5 ሰዎች ላይ በሽታው ተገኝቶ ህክምና እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል።

‎ከስርዓተ-ምግብ ጋር በተያያዘ ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች የሆናቸው 1 ሺህ 010 ህፃናት ልየታ ተደርጎላቸው 16 ህፃናት ከፍተኛ የምግብ አለመመጣጠን ችግር ገጥሟቸው ከነዚሁ ህፃናት መካከል 7 ሕፃናት በተኝቶ ህክምና እንዲሁም 9 ሕፃናት በውሎ ገብ የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ተጠቁሟል።

‎ከወባ በሽታ ጋር በተያያዘ እየጣለ ካለው ዝናብ ጋር ተያይዞ በወባማ ወረዳዎች የበሽታው ስርጭት ከመጨመሩ ጋር በተገናኘ በዜጎች ላይ የከፋ ጉዳት ከማስከተሉ በፊት በሽታውን ለመከላከል የሚደረገው ጥረት ማህበረሰቡን በስፋት በማሳተፍ ከ 5ኛ ዙር የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ጋር በማቀናጀት ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ተብሏል።

‎ይህ በእንዲህ እንዳለ ለተጎጂ ወገኖች የህክምና አገልግሎትን ለማሳለጥ ይረዳ ዘንድ የመድሃኒት እና የህክምና መገልገያ ቁሳቁሶች የማቅረብ ሂደቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

‎በመጨረሻም በግብረ-ሃይሉ ስብሰባ ወቅት የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሴይፉ ዋናቃ፣ የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ባንጌ ባንጃ እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተውበታል።

ቤት ለቤት የሚሰጠዉን የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በጥራት ተደራሽ ለማድረግ በቅንጅት እየተሰራ ነው፡፡በክልሉ ባሉት ዞኖች የተመደቡ ከፍተኛ ባለሙያዎችና ለጤና አጋር ድርጅቶች በበይነ መረብ...
30/04/2026

ቤት ለቤት የሚሰጠዉን የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ በጥራት ተደራሽ ለማድረግ በቅንጅት እየተሰራ ነው፡፡

በክልሉ ባሉት ዞኖች የተመደቡ ከፍተኛ ባለሙያዎችና ለጤና አጋር ድርጅቶች በበይነ መረብ ኦሬንተሽን መስጠቱን ህብረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት አስታውቋል።

የክልሉ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አጉኔ አሾሌ እንዳስታወቁት ከሚያዝያ 23-26/2018 ዓ.ም ድረስ የሚሰጠው የተቀናጀ የፖሊዮ ክትባት በጥራት ተደራሽ እንዲሆን ክትትልና ድጋፍ መጠናከር እንዳለበት አሳስበዋል።

በክልሉ 1.3 ሚሊየን በላይ ህፃናት ክትባቱን እንዲያገኙ ይደረጋል ያሉት አቶ አጉኔ፤ ክትባቱ በስኬት እንዲጠናቀቅ የተመደቡ ባለሙያዎች ሁሉ ሚናቸዉን እንዲወጡ ጠይቀዋል፡፡

መደበኛ ክትባት ያልተከተቡ፣ ክትባቱን ጀምረዉ ያቋረጡ ህፃናትን ማስከተብ እንደሚገባም በመጠቆም፡፡

ቆልማማ እግር፣የከንፈር እና ላንቃ መሰንጠቅ ችግር ያለባቸዉን ልየታ እና የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙም ይደረጋል ተብሏል፡፡

ወባ በሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ተግባራት እንዲሁም የተወሳሰበ ምግብ እጥረት ያለባቸዉ ሕፃናት ልየታ ከዘመቻዉ ጎን ለጎን እንደሚሰራ በውይይቱ ዳብሯል።

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ቻለው ንጋቱ ለዘፍኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ገቢ አሰባሰብ 1000 ሺህ ብር ገቢ በማድረግ ቻሌንጁን ተቀላቅለዋል።‎‎ለቦረዳ ህዝብ ታሪካ...
30/04/2026

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ቻለው ንጋቱ ለዘፍኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ገቢ አሰባሰብ 1000 ሺህ ብር ገቢ በማድረግ ቻሌንጁን ተቀላቅለዋል።

‎ለቦረዳ ህዝብ ታሪካዊ የሆነውን የዘፍኔ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግብዓት ማሟያና ሥራ ማስጀመሪያ የድጋፍ ቻሌንጁን ይቀላቀላሉ !!

‎የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት

‎1000763508416

‎Zefine Yemejemeriya dereja hospital

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ም/ሃላፊ ክቡር ወ/ሮ ባንጌ ባንጃ ለዘፍኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ገቢ አሰባሰብ 3000 ሺህ ብር ገቢ በማድረግ ቻሌንጁን ተቀላቅለዋል።‎‎ክቡር ወ/ሮ ባንጌ ባንጃ ...
30/04/2026

የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ም/ሃላፊ ክቡር ወ/ሮ ባንጌ ባንጃ ለዘፍኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ገቢ አሰባሰብ 3000 ሺህ ብር ገቢ በማድረግ ቻሌንጁን ተቀላቅለዋል።

‎ክቡር ወ/ሮ ባንጌ ባንጃ ለሆስፒታሉ ምረቃ ቻሌንጅ በመቀላቀል ላደረጉት ድጋፍ በህዝብ ስም እናመሰግናለን!

‎ለቦረዳ ህዝብ ታሪካዊ የሆነውን የዘፍኔ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግብዓት ማሟያና ሥራ ማስጀመሪያ የድጋፍ ቻሌንጁን ይቀላቀላሉ !!

‎የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት

‎1000763508416

‎Zefine Yemejemeriya dereja hospital

አቶ ሴይፉ ዋናቃ ለዘፍኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ገቢ አሰባሰብ 5000 ሺህ ብር  ገቢ በማድረግ ቻሌንጁን ተቀላቅለዋል።‎‎ለቦሮዳ ህዝብ ታሪካዊ የሆነውን የዘፍኔ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ...
30/04/2026

አቶ ሴይፉ ዋናቃ ለዘፍኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ገቢ አሰባሰብ 5000 ሺህ ብር ገቢ በማድረግ ቻሌንጁን ተቀላቅለዋል።

‎ለቦሮዳ ህዝብ ታሪካዊ የሆነውን የዘፍኔ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግብዓት ማሟያና ሥራ ማስጀመሪያ የድጋፍ ቻሌንጁን ተቀላቀሉ!!

‎የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት

‎1000763508416

‎Zefine Yemejemeriya dereja hospital

Address

Shecha Sub City, Beside Zone Administration
Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone Health Department ጋሞ ዞን ጤና መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share