Benishangul Gumuz Health Bureau

Benishangul Gumuz Health Bureau ጤንነቱ የተጠበቀ ዜጋ እናፍራ
(1)

የተቀናጀ  የብልህ ጅምር የጤና አገልግሎት  በክልሉ ተግባራዊ ማድረግ  ያለዕድሜ በመዉለድ የሚከሰቱ የጤና ችግሮች ለመከላከል የጎላ ድርሻ እንዳለዉ ተገለፀ። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ  ክልል መንግስ...
09/11/2025

የተቀናጀ የብልህ ጅምር የጤና አገልግሎት በክልሉ ተግባራዊ ማድረግ ያለዕድሜ በመዉለድ የሚከሰቱ የጤና ችግሮች ለመከላከል የጎላ ድርሻ እንዳለዉ ተገለፀ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ከኢትዮጵያ የቤተሰብ መምሪያ ጋር በመተባበር የተቀናጀ የብልህ ጅምር የጤና አገልግሎት ዙሪያ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል ።

ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና የእ/ወ/ህፃናትና ሥርዓተ ምግብ ዳይሬክቶሬት የእናቶች ወጣቶችና አፍላ ወጣቶች ኬዝ ቲም አስተባባሪ አቶ አለፎም ረዳ በስልጠና ማስጀመሪያ መድረክ ላይ እንዳሉት የዚህ ፕሮግራም በክልሉ ተግባራዊ መደረጉ የወጣቶችና አፍላ ወጣቶችን ጤና ከማሻሻሉ በተጨማሪ የክልሉን የቤተሰብ ዕቅድ ሽፋን ከፍ የሚያደረግ በመሆኑ ነው ።

ይህ ፕሮገራም በተለይ ዕድሜያቸው ከ15-24 ያሉ አድስ ተጋቢዎች የቤተሰብ ዕቅድ እየተጠቀሙ እርግዝናን ለማዘግየት እንዲችሉ ያግዛል ያሉት አቶ አለፎም ያለዕድሜ ከመዉድ ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የጤና ችግሮችን ለመቅረፍ እና ወጣቶች እና አፍላ ወጣቶች በኢኮኖሚ ራሳቸውን እስክያበቁ እርግዝናን ለማዘግየት የጎላ ድርሻ እንደአለዉ ተናግረዋል ።

በክልሉ ጤና ቢሮ የቤተሰብ ዕቅድ ባለሙያ ሲስተር መለሀሰን አጠይብ ይህ ፕሮግራም የአሶሳ ከተማን አስተዳደር ጨምሮ በክልሉ በተመረጡ 12 ወረዳዎች በሚገኙ የጤና ተቋማት ላይ ተግባራዊ እየተደረገ ስለሆነ ወጣቶች እና አፍላ ወጣቶች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ በየጤና ተቋማት የሚገኙ የጤና አመራሮችና የጤና ባለሙያዎች ለፕሮግራሙ ዉጤታማነት በትኩረት መሰራት እንደአለባቸዉ ገልፀው በቢሮ በኩልም አስፈላጊዉ እገዛ ይደረጋል ብለዋል።

ብልህ ጅምር ተግባራዊ ማድረግ ያለዕድሜ በእናቶች ላይ የሚደርሰዉን የጤና ችገሮች ከመቅረፉ በተጨማሪ ለህፃናት ጤና አስተዋጽኦ እንደአለዉ የገለፁት ደግሞ በክልሉ ጤና ቢሮ የወጣቶች እና አፍላ ወጣቶች ባለሙያ ሲስተር ፀጋነሽ በየነ ናቸው ።

የክልሉ ወጣቶች የጤና ካዉንስል ፕረዚዳንት ወ/ሮ ሀቢባ ያህያ በበኩላቸው ይህ ፕሮግራም የወጣቶች እና አፍላ ወጣቶች የቤተሰብ ዕቅድ አጠቃቀም ለማሻሻል የጎላ ድርሻ ስለአለው ለተግባራዊነቱ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን እገዛ ማድረግ እንደአለባዉ አሳስበዋል ።

በስልጠና መድረኩ ላይ ከአሶሳ ዞን ከተወጣጡ የጤና ጣቢያ ሀላፊዎች፣የጤና ኤክሰቴንሽን የትስስር ባለሙያዎች ፣የጤና ጣቢያ የወጣቶች ጤና ተጠሪና ከክልሉ ጤና ቢሮ የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል ።

ጥቅም 30/2018 ዓ.ም

ለሚመለከታችሁ ሁሉ
07/11/2025

ለሚመለከታችሁ ሁሉ

ለሚመለከታችሁ ሁሉ
07/11/2025

ለሚመለከታችሁ ሁሉ

ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የወባ በሽታ ስርጭት የመቀነስ ሁኔታዎች ቢታዩም አሁንም ክልሉ ወረርሽኝ ውስጥ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ ጠቆመ። ወቅቱ ለወባ ትንኝ መራቢያ ምች ከመሆኑ ጋ...
07/11/2025

ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የወባ በሽታ ስርጭት የመቀነስ ሁኔታዎች ቢታዩም አሁንም ክልሉ ወረርሽኝ ውስጥ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ ጠቆመ።

ወቅቱ ለወባ ትንኝ መራቢያ ምች ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ሊከሰት የሚችለውን የወባ በሽታን ለመከላከል ህብረተሰቡ የአከባቢ ቁጥጥር ስራዎች ላይ በንቃት እንዲሳተፍ ቢሮው ጥሪውን አስተላልፈዋል ።

በወቅታዊ የወባ በሽታ ስርጭት ዙሪያ ማብራሪያ የሰጡት የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ አብዱልሙኒየም አልበሽር እንዳሉት ከፍተኛ የወባ ስርጭት ካላቸው የሀገሪቱ ክልሎች መካከል ክልሉ ግንባር ቀደም መሆኑን ገልጸዋል።

የክልሉ 98 በመቶ የሚሆነው ማህበረሰብ ወባማ በሆኑ አከባቢዎች ይኖራል ያሉት ምክትል ቢሮው ሀላፊው የበሽታውን ስርጭት ለመከላከል ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑንም አብራርተዋል ።

እንደ ምክትል ቢሮ ሀላፊው ገለጻ በ2017 ዓ.ም 198,524 ቤቶች በጸረ ወባ ኬሚካል መረጨቱን፣ለከማሽ ዞን ወረዳዎች፣ማኦና ኮሞ ልዩ ወረዳን ጨምሮ በመተከል ዞን በሚገኙ ሶስት ወረዳዎች የአጎበር ስርጭት መካሄዱን ፣ከ6107 ካ.ሜ የሚሆን የአከባቢ ቁጥጥር ስራዎች ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ መከናወኑንም አብራርተዋል ።

ከዚህም በተጨማሪ በ13 ወረዳዎች ላይ የወባ በሽታ መከላከያ ክትባት በመደበኛነት በጤና ተቋማት እየተሰጠ ስለመሆኑን ጠቁመዋል።

ቢሮው የባህሪ ለውጥ ተግባቦት ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው በዚህ ሂደት የሚዲያ አካላትን ጨምሮ ለሎች ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ አስገንዝበዋል ።

በመጨረሻም ወቅቱ የክረምት መውጫ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ለወባ ትንኝ መራቢያ ምቹ ዕድል የሚፈጥር ነው ያሉት ምክትል ቢሮ ሀላፊው ህብረተሰቡ በየአከባቢው በንቂስ የአከባቢ ቁጥጥር ስራ ላይ በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪውን አስተላልፈዋል ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ!

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ ከዊንግስ ኦፍ ሂሊንግ ከተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በክልሉ የማህጸን መውጣት ወይም መንሸራተት ችግር ላለባቸው ሴቶች የህክምና አገልግሎት በክ...
06/11/2025

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ ከዊንግስ ኦፍ ሂሊንግ ከተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በክልሉ የማህጸን መውጣት ወይም መንሸራተት ችግር ላለባቸው ሴቶች የህክምና አገልግሎት በክልሉ በዘመቻ መልክ ከህዳር 4/2018 ዓም ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት በአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል ለመስጠት ዝግጅት አጠናቋል።

ህክምናው ከጎንደር ዩኒቨርስቲ በሚመጡ የማህጸንና ጽንስ ስፔሻሊስት ሀኪሞች በነጻ የሚሰጥ ሲሆን ችግሩ ያለባቸው ሴቶች በአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል በተጠቀሰው ቀን ጀምሮ በመገኘት አገልግሎት ማግኘት እንደምትችሉ እየገለጽን በርቀት ያሉ ወረዳዎች የሚገኙ እናቶች ደግሞ በአቅራቢያው ወደ ሚገኝ ጤና ተቋም በመሄድ መረጃ ማግኘት እንደምትችሉ እናሳውቃለን።

የክልሉ ጤና ጥበቃ ቢሮ!

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ  ክልል በመተከል  ዞን 3 ወረዳዎች የተከሰተውን  የኮሌራ ወረርሽኝ  ለመከላከል የሁሉም  ባለድርሻ  አካላት  ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ  መሆኑን  የቤኒሻንጉል  ጉሙዝ  ክል...
05/11/2025

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተከል ዞን 3 ወረዳዎች የተከሰተውን የኮሌራ ወረርሽኝ ለመከላከል የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ አሳሰበ ። ቢሮ በወቅታዊ የኮሌራ በሽታ ወረርሽኝ ዙሪያ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መክሯል ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል የቢሮ ሀላፊ አቶ አለም ደበሎ በክልሉ በመተከል ዞን 3 ወረዳዎች ላይ የተከሰተውን የኮሌራ ወረርሽኝ ለመከላከል በጤና ዘርፍ ላይ የሚሰሩ ባለድርሻ አካላት ጨምሮ የሁሉም አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ መሆኑን ነው ።

በክልሉ በተለያዩ ጊዜያት የሚከሰተዉን የኮሌራ ወረርሽኝ ለመከላከል ቢሮ እና በጤናው ዘርፍ ላይ የሚሰሩ ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር በአንዳንድ አከባቢዎች ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የተቻለ ቢሆንም አሁንም በአንዳንድ ወረዳዎች ወረርሽኙ እየተከሰተ በመሆኑ ወረሽኙን በአጭር ጊዜ ዉስጥ ለመቆጣጠር በጋራ መወያየት ወሳኝ በመሆኑ የዉይይት መድረኩ መዘጋጀቱን አቶ አለም ገልጸዋል ።

ይህንን ወረርሽኝ በአጭር ጊዜ ዉስጥ የመንግስት ተቋማትም ሆነ መንግስታዊ ያልሆኑ ባለድርሻ አካላት የፋይናንስ እና የቴክኒክ እገዛ በማድረግ ወረርሽኙ የከፋ ጉዳት ሳያስከትል ለመቆጣጠር በትኩረት መስራት እንደአለባቸዉ አቶ አለም አስገንዝበዋል ።

በተለይም ወረርሽኙን ለመከላከል ዋነኛው ሥራ የግልና የአከባቢ ንፅህና መጠበቅ እና የዉሃ አቀርቦትን ማሻሻል በመሆኑ በዘርፉ የሚሰሩ የመንግስት ተቋማት እና መንግታዊ ያልሆኑ አካላት ፈጣን ምላሽ መስጠት እንደአለባቸዉ አቶ አለም አሳስበዋል ።

አቶ አለም አክለውም ወረርሽኙ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ለመቆጣጠር በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት መዋቅሮች የወረርኙን ሂደት በየቀኑ እየተከታተሉ መምራት አለባቸው ብለዋል።

በዉይይቱ ላይ የተገኙ ባለድርሻ አካላት በበኩላቸው ወረርሽኙን ለመከላከል የበኩላቸውን ድርሻ እንደሚወጡ ተናግረው በየደረጃው የሚገኙ የመንግሥት መዋቅሮች ሥራዉን በበላይነት መምራት እንደአለባቸዉ ጠይቀዋል ።

የኮሌራ በሽታው በዳንጉር ወረዳ በአንድ ቀበሌ የጀመር ቢሆንም አጓራባች ወደ ሆኑ ወረዳዎች ቡለን እና ድባጤ ቀበሌዎች የተዛመተ መሆኑን ከቀረበው ሪፖርት ለማወቅ ተችሏል።

ጥቅምት 26/2018 ዓ.ም

የመተከል ዞን ከፍተኛ የጤና ዘርፍ አመራር ፣ባለሙያዎች እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በተገኙበት በቡለን ወረዳ የተከሰተዉን አኮሌራ በሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ስራዎች ሪፖርት ግምገማ ተደ...
05/11/2025

የመተከል ዞን ከፍተኛ የጤና ዘርፍ አመራር ፣ባለሙያዎች እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በተገኙበት በቡለን ወረዳ የተከሰተዉን አኮሌራ በሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ስራዎች ሪፖርት ግምገማ ተደረገ ።
*************
( ቡለን ጥቅምት 26/2018 ዓ/ም ) በሪፖርት ግምገማዉ የቡለን ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አዳሙ ታዬ በቡለን ወረዳ በኤጳር እና በአይጋሊ ቀበሌዎች የተከሰተዉን የኮሌራ በሽታ ስርጭት በመቆጣጠር ረገድ አበረታች ስራዎች የተሰሩት ሲሆኑ በቀጣይ በሽታዉን የመቆጣጠር ስራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል የመንግስታዊ ያልሆኑት ድርጅቶች ድጋፍ እንደሚያስፈል ገልጿል ።

የቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ ነመራ ማሩ በሪፖርት ግምገማዉ እንደገለጹት በወረዳችን የተከሰተዉን የኮሌራ ስርጭት ለመቆጣጠር ያለዉን የሰዉ ሐይል፣የንጹህን መጠበቅያ ቁሳቁ እና ሎጀስቲክ በመጠቀም በአጭር ጊዜ ዉስጥ ዉጤታማ ስራዎች የተሰሩት መሆናቸዉን ገልጿል ።

በወረዳችን የተጀመረዉን የኮሌራ በሽታ ስርጭት የመቆጣጠር ስራዉ አጠናክሮ ለማስቀጠል የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ስራ እና የአጋር ድርጅቶች ተሳትፎ አስፈላጊ መሆኑን የቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ ነመራ ማሩ ገልጿል ።

የቡለን ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ዳኛ አንበጌ በወረዳችን በሁለቱም ቀበሌዎች የተከሰተዉን የኮሌራ በሽታ ስርጭት በመቆጣጠር እና ማህበረሰብን ከበሽታዉ ለመታደግ ዉጤታማ ስራዎች የተጀመሩ ሲሆኑ ስራዎችን ስኬታማ ለማድረግ የተደራጀ እና የተቀናጀ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጿል ።

የመተከል ዞን ጤና ጥበቃ መምሪያ ሃላፊ ዶ/ር ታረቀኝ አርገታ የኮሌራ በሽታ ለመቆጣጠር ቅንጅታዊ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል ወሳኝ መሆኑን በመጠቆም በተለይም በአከባቢዉ ሐይጅንና ሳኒተሽን ስራዎች ላይ ትኩረት ተሰጠዉ መስራት እንዳለበት ዶ/ር ታረቀኝ አርገታ አሳስበዋል ።

በዉይይቱ የተገኙት የPUi እና የZOA ኢንተርናሽናል ድርጅት አካላት በበኩላቸዉ በመተከል ዞን በሶስቱ ወረዳዎች የተከሰተዉን የኮሌራ በሽታ ስርጭት ለመቆጣጠር የተለያዩ ድጋፎችን የማድረግ ስራዎች የተጀመሩ ሲሆን በቀጣይ የኮሌራ በሽታ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚሰሩት ስራዎች ስኬታማ ለማድረግ አጋር ድርጅቶች ድጋፋቸዉን አጠናክሮ እንደሚቀጥሉ ባለድርሻ አካላት ገልጿል ።

በዉይይቱ የመተከል ዞን ጤና ጥበቃ መምሪያ አመራርና ባለሙያዎች፣ የመተከል ዞን ትምህርት መምሪያና ግብርና መምሪያ ባለድርሻ አካላት ፣ የመተከል ዞን የሚሰሩት አጋር ድርጅቶች ፣የቡለን ወረዳ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ፣የቡለን ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት እና የቡለን ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት አመራሮች ፣ ባለሙያዎች እንዲሁም በቡለን ወረዳ የሚሰሩት አጋር ድርጅቶች ጭምር ዉይይቱን ተሳትፏል ።

መረጃው የወረዳው መንግሥት ኮሚኒኬሽን ነው

በክልሉ በመተከል ዞን የተከሰተው የኮሌራ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት የዘርፉ ባለሙያዎች በቁርጠኝነት እንዲሰሩ የክልሉ ጤና ቢሮ ገለጸ። በሽታውን ለመከላከል ውጤታማ የሆነ...
04/11/2025

በክልሉ በመተከል ዞን የተከሰተው የኮሌራ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት የዘርፉ ባለሙያዎች በቁርጠኝነት እንዲሰሩ የክልሉ ጤና ቢሮ ገለጸ።

በሽታውን ለመከላከል ውጤታማ የሆነ የተግባቦትና ግንዛቤ ፈጠራ ስራዎችን ማጠናከር እንደሚገባም ቢሮው አስታውቋል ።

የክልሉ ጤና ቢሮ ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና እንስትቲዩት ጋር በመተባበር በከማሽና በመተከል ዞኖች ለተወጣጡ የህብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት በአሶሳ ከተማ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል።

በማጠቃላያ መድረኩ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ አብዱልሙኒየም አልበሽር እንዳሉት በመተከል ዞን በአራት ወረዳዎች የተከሰተውን የኮሌራ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ቢሮው በትኩረት እየሰራ ስለመሆኑን አነስተዋል።

ለበሽታው ምላሽ ለመስጠት ተቋማት አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶችን እንዲያገኙ እየተደረገ ነው ያሉት ምክትል ቢሮ ሀላፊው በየደረጃው የተቋቋመው ግብረ ሀይል ስራ ውስጥ እንዲገባ፣የበሽታ አሰሳና ቅኝት ስራዎችን ማጠናከር እንዲሁም የልየታና ህክምና አገልግሎትን ማጠናከር ላይ በትኩረት እንዲሰራም አስገንዝበዋል ።

በክልሉ ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥርና ምላሽ አሰጣጥ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መብራቱ በጉኖ በበኩላቸው የኮሌራ በሽታን ለመከላከል በቅንጅት መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።

የልየታና የህክምና ስራዎችን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲሰሩም አቶ መብራቱ አክለውም ጥሪ አስተላልፏል ።

የኮሌራ በሽታ በመተከል ዞን ድባጢ፣ቡለን፣ማንዱራና ዳንጉር ወረዳዎች ላይ የተከሰተ ሲሆን 127 ሰዎች በበሽታው ተይዞ አስፈላጊ ህክምና አግኝተዋል ።

የክልሉ ጤና ቢሮ!

PUi ኢንተርናሽናል መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በቡለን ወረዳ ለባኩጅ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የ9 መቶ ሽህ ብር በላይ ወጪ የሆነ የስራ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።************( ቡለን ጥቅምት...
04/11/2025

PUi ኢንተርናሽናል መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በቡለን ወረዳ ለባኩጅ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የ9 መቶ ሽህ ብር በላይ ወጪ የሆነ የስራ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
************
( ቡለን ጥቅምት 25/2018 ዓ/ም )PUi ኢንተርናሽናል መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በቡለን ወረዳ ለባኩጅ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ 9 መቶ ሽህ ብር በላይ ወጪ የሆነ የስራ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

የቡለን ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አዳሙ ታዬ PUi ኢንተርናሽናል መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በቡለን ወረዳ በተለይም ለባኩጅ ጤና ጣቢያ በርካታ የህክምና ቁሳቁስ፣ መዳሃኒት ፣ የንጹህና መጠበቅያ፣ የቢሮ ዕቃዎች እና ሌሎች ድጋፎችን ከማድረግ በተጨማሪ በተለያዪ በሽታ መከላከያ ስራዎች ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ፈጠራ ስልጠና በመስጠት ፕሮጀክቱ በወረዳዉ ስኬታማ ስራዎችን መስራቱን አቶ አዳሙ ታዬ ገልጿል ።

አቶ አደሙ ታዬ አክለዉም ፕሮጀክቱ በዚህ ዙር የጤና ስራዎችን ለማሳለጥ ለባኩጅ ጤና ጣቢያ ኮምፕተር ፣ ፕርንተር፣ሸልፍ፣ወንበር፣ወረቀት እናሌሎች ቁሳቁስ ጭምር በአጠቃላይ 981,163,65 ብር የሚያወጣ ቁሳቁስ ፕሮጀክቱ ድጋፍ በማድረጉ አቶ አዳሙ ታዬ ለፕሮጀክቱን ምስጋና በማቅረብ የፕሮጀክቱ ድጋፍ በባኩጅ ክላስተር የጤና ስራዎችን ስኬታማ በማድረግ በአከባቢዉ ጤናማ እና አምራች ዜጋ ለማፍራት ከፍተኛ አስተዋጾ መኖሩን የቡለን ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ሃላፊዉ አቶ አዳሙ ታዬ ገልጿል ።

PUi ኢንተርናሽናል መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት የቡለን ወረዳ አስተባባሪ ዶ/ር ያረጋል ታደሰ በርክክቡ ፕሮግራም እንደገለጹት ፕሮጀክቱ በቡለን ወረዳ ለቡለን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ፣ ለቡለን ጤና አጠባበቅ ጣቢያ እና ለባኩጅ ጤና ጣቢያ ክላስተር ከዚህ በፊት የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ስኬታማ ስራዎችን የሰራ ሲሆን በዛሬ እለት ለባኩጅ ጤና ጣቢያ የተደረገ የቁሳቁስ ድጋፍ የተቋሙ ባለሙያዎች የተሻለ የጤና አገልግሎት ለማህበረሰብ በመስጠት ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር የተደረገ መሆኑን ዶ/ር ያረጋል ታደሰ ገልጿል ።

PUi ኢንተርናሽናል መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ኦፊሰር አቶ አለምነዉ አሻግሬ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ በቡለን ወረዳ ጤናማ ማህበረሰብ ለማፍራት የጀመረዉን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿልጰ።

የቡለን ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ ነመራ ማሩ በፕሮግራሙ እንደገለጹት PUi ኢንተርናሽናል መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ከዚህ በፊት በቡለን ወረዳ ለጤናዉ ዘርፍ ተቋማት የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ አበረታች ስራዎች የሰራ ሲሆን የጤና ባለሙያዎች በተሰጠዉ ድጋፍ ምቹ ሁኔታ በመጠቀምና ለማህበረሰቡ የተሻለ የጤና አገልግሎት በመስጠት በአከባቢዉ አምራችና ጤናማ ዜጋ ለማፍራት የበኩላቸዉን ድርሻ መወጣት እንዳለባቸዉ አቶ ነመራ ማሩ አሳስበዋል ሲል የወረዳው ኮሚኒኬሽን መረጃ ያመላክታል።

የማህበረሰብ እና ሁኔታዎች  ላይ የተመሠረተ የህብረተሰብ  ጤና አደጋዎች  ቅኝት ሥርዓት ማጠናከር በተለያዩ  ጊዜያት የሚከሰቱ ወረርሽኞችን ለመከላከል የጎላ  ድርሻ  እንደአለዉ ተገለፀ ።የቤ...
04/11/2025

የማህበረሰብ እና ሁኔታዎች ላይ የተመሠረተ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝት ሥርዓት ማጠናከር በተለያዩ ጊዜያት የሚከሰቱ ወረርሽኞችን ለመከላከል የጎላ ድርሻ እንደአለዉ ተገለፀ ።የቤ/ጉ/ክ/መ/ጤና ቢሮ ለጤና ኤክስቴንሽንና ለጤና ኤክስቴንሽን ሱፐርቫይዘሮች በማህበረሰብ እና ሁኔታዎች ላይ የተመሠረተ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝት ላይ ያተኮረ ስልጠና ሰጥቷል።

በክልሉ በተለያዩ ጊዜያት የሚከሰቱ ወረርሽኞችን ለመከላከል የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች እያበረከቱት ያለዉ እገዛ የጎላ ድርሻ እንደነበረው ይታወቃል ።

እነዚህን የተጀመሩ ሥራዎች አጠናክሮ ለማስቀጠል የጤና ኤክስቴሽን ባለሙያዎች እና የጤና ኤክስቴሽን ሱፐርቫይዘሮች በዕውቀት ላይ የተመሠረተ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ የስልጠና መድረኩ መዘጋጀቱን በክልሉ ጤና ቢሮ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቁጥጥር እና ምላሽ አሰጣጥ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ሰኚ መኮንን ተናግረዋል ።

ስልጠናዉ የማህበረሰብ እና በሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝት ስርዓትን ለማጠናከር የሚያግዝ የአተገባበር ማንዋል ላይ አተኩሮ የተሰጠ መሆኑን አቶ ሰኚ ገልጸዋል ።

የበሽታዎች አሰሳና ቅኝት ስርዓትን ለማጠናከር የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች በትኩረት እንዲሰሩ ያሳሰቡት አቶ ሰኚ በተለይ በወሰዱት ግንዛቤ ልክ ለተግባራዊነቱ በቁርጠኝነት እንዲሰሩ እና የተሰሩ ሥራዎችን ለሚመለከተዉ አካል በወቅቱ ማቅረብ እንደአለባቸዉ አስገንዝበዋል ።

አቶ ሰኚ አክለውም የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ወደ ወረዳቸው ሲመለሱ በቀበሌ ደረጃ የሚገኙ የልማት ቡድኖችን በማሰልጠን በወረርሽኝ መከላከል ሥራዎች ዉስጥ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲያበረክቱ ማድረግ እንደአለባቸዉ ብለዋል ።

የማህበረሰብ እና በሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች ቅኝት ስራዎች በዋናነት የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ሥራ በመሆኑ በየደረጃው የሚገኙ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች በሙሉ አቅማቸው ስራዎችን እንዲያከናውኑ በቢሮው በኩል አስፈላጊው ሁሉ ድጋፍና እገዛ እንደሚያደረግ የመሠረታዊ ጤናና የጤና ኤክስቴሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ግሩም ባዩ ገልጸዋል ።

የስልጠና ተሳታፊዎች በበኩላቸው ወደ ቀበሌያቸው ሲመለሱ በቀበሌ ደረጃ ኮሚቴ በማቋቋም የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በመስጠት ወደ ሥራ እንደሚገቡና ወቅታዊ የሆነ ሪፖርት በወቅቱ እንደሚያቀርቡ ተናግረዋል ።

በስልጠናው መድረክ ላይ ከጤና ቢሮ፣ከዞን የሚመለከታቸው አካላት፣ከማኦና ኮሞ ልዩ ወረዳ፣ከባምባሲና ከአቡራሃሞ ወረዳ የተወጣጡ የጤና ኤክሰቴንሽን ባለሙያዎች እና የጤና ኤክስቴንሽን ሱፐርቫይዘሮች ተሳትፈዋል ።

ጥቅምት 25/2018ዓ.ም
የክልሉ ጤና ቢሮ

በፓይለት ደረጃ በአሶሳ ከተማ የተጀመረው በራስ የሚወሰድ የቤተሰብ ዕቅድ ዜዴ (Self injection Dipo) ትግበራ የከተማ  የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችና ጤና ባለሙያዎች የጎላ ድርሻ ...
04/11/2025

በፓይለት ደረጃ በአሶሳ ከተማ የተጀመረው በራስ የሚወሰድ የቤተሰብ ዕቅድ ዜዴ (Self injection Dipo) ትግበራ የከተማ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችና ጤና ባለሙያዎች የጎላ ድርሻ እንዳላቸው የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ጤና ቢሮ በራስ የሚወሰድ የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎትን ለማጠናከር ለከተማ ጤና ኤክስቴንሽንና ጤና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥዋል።
በክልሉ ጤና ቢሮ የእናቶች ወጣቶችና አፍላ ወጣቶች ጤና አገልግሎት አስተባባሪ አቶ ሀለፎም ረዳ በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ እናቶች የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

የቤተሰብ ዕቅድ ከወሊድ ጋር በተያያዘ ሊከሰት የሚችለውን የእናቶችና የህጻናት ሞት ከመከላከል አኳያ ትልቅ ድርሻ አለው ያሉት አቶ ሀለፎም በተለይ በክልሉ በተመረጡ ጤና ተቋማት የተጀመረው ይህ አዲስ በራስ የሚወሰድ የቤተሰብ ዕቅድ ዜዴ(self injection dipo) ወጪ ቆጣቢ ቀላል ዜዴና ተደራሽነትን የሚያሻሽል ነው ተብለዋል።

ይህ ዜዴ ቀላል፣ምቹ ከመሆኑ ባሻገር ሴቶችን ከማብቃት አንጻርም ትልቅ አበርክቶ እንዳለው ጠቁመው በተለይ ለተግባራዊነቱ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችና ጤና ባለሙያዎች በቁርጠኝነት እንዲሰሩም ጥሪ አስተላልፈዋል ።

እንደ ሀገር በተመረጡ 10 ከተሞች በፓይለት ደረጃ የተጀመረው ይህ ዜዴ አንዱ የአሶሳ ከተማ መሆኑንም ተገልጸዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ!

የፓዌ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የወረዳው የትራንስፎርሜሽን አጀንዳ ቴክኒክ ኮሚቴ የስራ ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን ገመገመ።(ፓዊ፥ ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም) የፓዊ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት የ2018...
03/11/2025

የፓዌ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት የወረዳው የትራንስፎርሜሽን አጀንዳ ቴክኒክ ኮሚቴ የስራ ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን ገመገመ።

(ፓዊ፥ ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም) የፓዊ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት የወረዳ ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በቴክኒክ ኮሚቴው ገምግሟል።

ሪፖርቱ በጽ/ቤቱ የጤና ኤክስቴንሽን ኦፊሰርና የወረዳው ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ ፎካል በሆኑት አቶ ሙሉቀን አዋሮ የቀረበ ሲሆን፥ በበጀት ዓመቱ የወረዳ ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ከሚሰራባቸው 19 ቀበሌዎች መካከል የተመረጡ ሰባት ቀበሌዎች ሞዴል ለማድረግ አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ላሎቶ፥ የወረዳ ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ በዕቅድ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው፥ በወረዳው ውስጥ የሚገኙ ሁሉም ጤና ጣቢያዎችና ጤና ኬላዎች ለጉዳዩ ተገቢውን ትኩረት በመስጠት እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

በሩብ ዓመቱ ግምገማ የተሻለ አፈፃፀም ተመዝግቧል ያሉት አቶ ግዛቸው፥ በግምገማው የመረጃ አያያዝ፣ ደረጃውን የተጠበቀ የመፀዳጃ ቤት አገልግሎት እና የግብዓት አቅስቦት ውስንነት በአንደኛው ሩብ ዓመት የታዩ ክፍተቶች መሆናቸውን ጠቅሰው፥ ባለድርሻ አካላት ችግሩን ለመቅረፍ ርብርብ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል።

አፈፃፀሙ በቀጣይም በወረዳው ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ ግብረ-ኃይልና በጤና ጣቢያ ትስስር ደረጃ የሚገመገም መሆኑ ተገልጿል ሲል የወረዳው መንግስት ኮሚኒኬሽን ዘገባ ያመላክታል።

Address

Asosa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Benishangul Gumuz Health Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Benishangul Gumuz Health Bureau:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram