Benishangul Gumuz Health Bureau

Benishangul Gumuz Health Bureau ጤንነቱ የተጠበቀ ዜጋ እናፍራ
(1)

በማህጸን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት ዙሪያ ለትምህርት ተቋማት አካላት የተዘጋጀ የውይይት መድረክ በምስል!
22/01/2026

በማህጸን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት ዙሪያ ለትምህርት ተቋማት አካላት የተዘጋጀ የውይይት መድረክ በምስል!

ጤናማ እናትነት ፈጠራና ዘላቂ ፋይናንሰ ለጤናማ እናትነት!” Innovation and Sustainable Financing for Safe Delivery በሚል መሪ ቃል ጤናማ እናትነት ወር በክልል...
21/01/2026

ጤናማ እናትነት ፈጠራና ዘላቂ ፋይናንሰ ለጤናማ እናትነት!” Innovation and Sustainable Financing for Safe Delivery በሚል መሪ ቃል ጤናማ እናትነት ወር በክልል ደረጃ ለ20ኛ ጊዜ በክልሉ ስራ አመራር ተቋም ተከበረ።

የቤ/ጉ/ክ/ መንግስት ጤና ቢሮ ፕሮግራም ዘርፍ ም/ኃላፊ አቶ አብዱልሙኒየም አልበሽር የጤናማ እናትነት ወር አከባበርን በማስመልከት መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን ጤናማ እናትነት ወር ሁሉም እናቶች ጤናማ የእርግዝና፤ የወሊድና የድህረ-ወሊድ ጊዜ እንዲኖራቸውና አስፈላጊውን የጤና መረጃ እና አገልግሎት ተደራሽነት ለማረጋገጥ የተገባውን ቃል ለማደስ በየዓመቱ ጥር ወር የሚዘከርበት ነው ሲሉ ገልፀዋል።

እንደ ኃላፊው አገላለፅ የፕሮግራሙ ዋና አላማ ማህበረሰባችንን ግንዛቤ በማስጨበጥ ልንከላከላቸው በምንችላቸው ምክንያት የሚከሰት የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናት ሞትን ለመቀነስ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ለማድረግ ነው በማለት በየአመቱ 14ሺ በየቀኑ ደግሞ 39 እናቶች ከእርግዝናና ከወሊድ ጋር በተያያዘ ህይወታቸው እንደሚያልፍ ይህም እንደ ወረርሽን ነው ብለዋል።

አብዱልፈታ አብደራሂም የእናቶች ህፃናት ወጣቶች ስርአተ ምጎግብ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በበኩላቸው ጤናማ እናትነት ማለት አንዲት ሴት በእርግዝና ፤ በወሊድ እንዲሁም በድህረ ወሊድ ወይም (ከወለደች በ 42 ቀናት) የሚኖራት የአካል፡ የአእምሮ እና ማህበራዊ ጤንነት መሆኑን በመግለፅ የእናቶች የጤና ለመጠበቅና ጤናማ ትውልድ ለማፍራት በጥር ወር ብቻ ሳይሆን ከአመት እስከ አመት በተገቢው ልክ አገልግሎት መስጠት ስንችል መሆኑን ገልፀዋል ።

የእናቶችህፃናት ጤና ጤና ቡድን መሪ ሀለፎም ረዳ የክልላችን ተጨባጭ ሁኔታን ስንመለከት ለእናቶች ሞት ምክንያት ከሆኑት የተራዘመ ምጥ: የጤና መመረዝ :ከወሊድ በኃላ የሚከሰት ከፍተኛ የደም መፍሰስ: ዋነኛዎቹ ሲሆኑ እናቶች ወደ ጤና ተቋም ሳይሄዱ በቤት ውስጥ መዘግየት በትራንስፖርት ችግር የአንቡላንስ አጠቃቀም ችግር በቂ የሆነ የሰለጠነ ባለሞያ አለመኖር እንዲሁም በባለሞያዎች የሚገለፅ ቸልተኝነት ዋና ምክንያቶች ናቸው ብለዋል።

ቡድን መሪው አያይዘውም ቀኑን አስመልክቶ እንደተናገሩት በቀጣይ ቀናት ወሩን አስመልክቶ በዞኖች እና በወረዳዎች የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን በማከናወን፣ የእናቶች ጤና አገልግሎት ተጠቃሚነትና ተደራሽነትን እንዲሁም የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት ተደራሽነትና ተጠቃሚነትን ለማሻሻል እየተሰሩ ያሉ ተግባራት በመቃኘት እንደሚከበር አስታውቀዋል።

ተሳታፊዎች በበኩላቸው ጤናማ እናትነት ወርን ስናከብር ያሉት ችግሮች ዘርፈ ብዙ በመሆናቸው የሴቶች ክንፍና የሴቶች ፎረም በጋራ በመሆን ከቢሮው ጋር በመተባቡር የግንዛቤ ስራዎችን በመስራት የእናቶችን ሞት ለማስቀረት የድርሻቸውን እንደሚሰሩ ተናግረዋል

በእለቱ ሰነዶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸው ፕሮግራሙ ተጠናቋል።

የቤኒሻጉል ጉሙዝ  ክልል ጤና ቢሮ  ከክልሉ ህብረተሰብ ጤና  ላብራቶሪ  ምርምር ማዕከል  ጋር በመተባበር  መድሀኒት  የተላመደ  ተወሲያን (AntiMicro durg resistance) ዙሪያ ...
18/01/2026

የቤኒሻጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ ከክልሉ ህብረተሰብ ጤና ላብራቶሪ ምርምር ማዕከል ጋር በመተባበር መድሀኒት የተላመደ ተወሲያን (AntiMicro durg resistance) ዙሪያ በክልሉ ስራ አመራር ተቋም ስልጠና ተሰጥቷል ።

እንደ ሀገር ብሎም እንደ ክልላችን በጤና ተቋሟት የናሙና አወሳሰድ ቁጥሩ ዝቅተኛ በመሆኑ በቀጣይ የግሉንና የመንግስት ጤና ተቋማትን በማሳተፍ ና ሙያዊ ስልጠናዎችን በመስጠት እንደሚሰራም በመድረኩ ላይ ተጠቁሟል ።

የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው ስልጠናው ሙያዊ በመሆኑ ቀጣይ ስራዎችን በአግባቡና በጥራት ለመስራት እንደሚያግዝም ተናግረዋል ።

የማጠቃለያ መድረኩ ላይ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ጤና ቢሮ ም/ ሀላፊዎች የተገኙ ሲሆን የተሰጠው ስልጠና ሙያቸውን የሚያዳብር በመሆኑ በክልላችን በመንግስትና በግል ጤና ተቋም ላይ የናሙና አወሳሰድ ዝቅተኛ በመሆኑ ከስልጠናው መልስ ክፍተቶችን በመፍተሽ የተሻለ ስራ ለመስራት መዘጋጀት እንዳለባቸው ሀላፊዎቹ አሳስበዋል ።

በስልጠናው መድረክ ላይ የአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል የጤና ባለሙያዎች ፣ ከግል ጤና ተቋማት የተወጣጡ ተሳታፊዎች ፣የጤና ጣቢያ ባለሙያዎች ፣ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ጤና ባለሙያዎች ፣ የክልሉ ጤና ቢሮ ባለሙያዎችና ሀላፊዎች ፣ የክልሉ ላብራቶሪ ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የክልሉ ጤና ቢሮ!

የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ክትባት እንዲሁም ለሎች በክትባት ልንከላከል የምንችላቸው በሽታዎች ለመከላከል በሚደረገው ጥረት የትምህርት ዘርፉ የጎላ ድርሻ እንዳለው የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ። ...
18/01/2026

የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ክትባት እንዲሁም ለሎች በክትባት ልንከላከል የምንችላቸው በሽታዎች ለመከላከል በሚደረገው ጥረት የትምህርት ዘርፉ የጎላ ድርሻ እንዳለው የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር በማህጸን በር ካንሰር መከላከያ ክትባትና ሌሎች በክትባት የምንከላከላቸው በሽታዎች ዙሪያ ከትምህርት ተቋሟት ከተወጣጡ መምህራኖች እና የስራ ሀላፊዎች ጋር በክልሉ ስራ ዓመራር ተቋም ውይይት አካሂደዋል ።

በመድረኩ የተገኙት በክልሉ ጤና የእናቶች ፣ ህጻናትና ስርዓት ምግብ ኬዝ ቲም አስተባባሪ አቶ ማህጁብ ካሊፋ የማህጸን በር ካንሰር በሸታን ለመከላከል መምህራን በትምህርት ተቋማትና ከትምህርት ተቋማት ዉጭ ግንዛቤን በመፍጠር እና ግንባር ቀደም በመሆን ልጆችን በማስከተብ ሌሎችም እንዲከተቡ ማስተማር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል ።

ስለሆነም በየደረጃው የሚገኙ የትምህርት ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ በመፍጠር ረገድ ከጤናው ዘርፍ ጋር በቅርበት ሊሰሩ እንደሚገባም ነው የጠቆሙት።

በመድረኩ ላይ ስለ ማህጸን በር ካንሰር መከላከያ መንገዶች እና የእናቶች ፣ አፍላ ወጣቶች ጤና አገልግሎት ለመድረኩ ተሳታፊዎች ስፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት በክልል ጤና ቢሮ ከፍተኛ ባለሙያዎች ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ።

በመድረኩ ላይ የአሶሳ ዞን የ9ኙ ወረዳ የትምህርት ጽ/ቤት የስራ ሀላፊዎች ፣ የትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን እንዲሁ። የትምህርት እና የጤና ሴክተር ባለሙያዎች ተገኙተዋል ።

የክልሉ ጤና ቢሮ!

የክልሉ ጤና ቢሮ በተለያዩ የጤና ፕሮግራሞች ዙሪያ በተለይ በግልና በአከባቢ ንጽህና ጉድለት የሚመጡ በሽታዎችን ለመከላከል በመተከል ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ላይ እያካሄደ ያለው የግንዛቤ ፈጠራ...
17/01/2026

የክልሉ ጤና ቢሮ በተለያዩ የጤና ፕሮግራሞች ዙሪያ በተለይ በግልና በአከባቢ ንጽህና ጉድለት የሚመጡ በሽታዎችን ለመከላከል በመተከል ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ላይ እያካሄደ ያለው የግንዛቤ ፈጠራና የማህበረሰብ ቅስቀሳ ስራዎች ተጠናክሮ ቀጥለዋል።

በመሆኑ በግልና በአካባቢ ንጽህና ጉድለት የሚመጡ የጤና ችግሮች ምን ያህል ያዉቃሉ ?

የግል ንጽህናና የአካባቢ ጤና በመጠበቅ በቆሻሻ ምክንያት ቤተሰብዎ ላይ የሚደርሱ የጤና ችግሮች እንደ ተቅማጥ፣ የአንጀት ተስቦ፣ትራኮማ እና የመተንፈሻ አካላት ካሉ በሽታዎች ለመከላከል ደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻዎችን ለያይቶ በማስቀመጥና በማስወገድ ይከላከሉ፡፡

የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ጉድጓድ በግቢ ውስጥ በአካባቢዎ በሚገኝ ቁሳቁስ አዘጋጅቶና ከላይ ወንፊት ወይም ማጣሪያ አድርጎ በመጠቀም በንፅህና ጉድለት የሚከሰቱ ጉንፋንና መሰል የመተንፈሻ አካላት በሽታዎችን ይከላከሉ፡፡

ፍሳሽ ቆሻሻን ለፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ባዘጋጁት ጉድጓድ ውስጥ በመጨመር፣ አላስፈላጊ ሽታና ዝንብን በመከላከል ቤተሰብዎን ከሆድ ጥገኛ ትላትል፣ ከመተንፈሻ አካልና ከአይን በሽታዎች መከላከል ይቻላል፡፡

ከግል ንፅህና ጉድለት ከሚመጡ እንደ ትራኮማ ካሉ ተላላፊ በሽታዎች ለመጠበቅ የቤተሰብ አባላት ጠዋትና ማታ ፊታቸውን በንጹህ ውሃና ሳሙና እንዲታጠቡ በማድረግ ፣ምግብ ከተመገቡ በኋላ ጥርስን ጠዋትና ማታ በንፁህ ብሩሽ ወይም መፋቂያ ማፅዳት፣ምግብ ከማዘጋጀትዎና ከመመገብዎ በፊት፣ህፃናትን ካፀዳዱ በኋላ እና መፀዳጃ ቤት ከተጠቀሙ በኋላ እጅዎን በሚገባ በንፁህ ውሃና በሳሙና በመታጠብ እንደ አጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት ወይም ኮሌራ፣የአንጀት ተስቦ እና ጥገኛ ትላትል እንዲሁም ሌሎች መሰል ተላላፊ ከሆኑ በሽታዎች እራስዎንና በተሰብዎን መከላከል ይችላሉ።

‹‹ የግልና የአከባቢ ንፅህና በመጠበቅ ከግልና ከአከባቢ ንፅህና ጉድለት ከሚመጡ የተለያዩ በሽታዎች ለመከላከል ሀላፊነታችንን እንወጣ ›› !

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ

የመክፈል አቅምን መሠረት ያደረገ የመዋጮ አከፋፈል ስርዓት በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች  እና የከተማ አስተዳደሮች ወጥ በሆነ መልኩ  መተግበር እንዳለበት ተገለጸ፡፡ የቤ/ጉ/ክ/መ/ጤና ቢሮ  ከ...
17/01/2026

የመክፈል አቅምን መሠረት ያደረገ የመዋጮ አከፋፈል ስርዓት በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች እና የከተማ አስተዳደሮች ወጥ በሆነ መልኩ መተግበር እንዳለበት ተገለጸ፡፡

የቤ/ጉ/ክ/መ/ጤና ቢሮ ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ከአሶሳ ዞን ለተውጣጡ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አስተባባሪዎችና ባለሞያዎች ገቢን መሰረት ያደረገ የመዋጮ አከፋፈል ማስፈጸሚያ ማኑዋል ላይ ውይይት አካሄደዋል ፡፡

በጤና ቢሮ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አስተባባሪ አቶ መገርሳ ገለታ ማኑዋሉ ከ2017ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገ ቢሆንም በተፈለገው ልክ ለውጥ ያልመጣ በመሆኑ የውይይት መድረክ መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡

በማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን አዋጅ ቁጥር 1273/2014 መሠረት የአባልነት መዋጮ በገቢ መጠን ላይ ተመስርቶ የሚወሰን መሆኑን በመግለጽ ቀደም ሲል ሁሉም ማህበረሰብ መዋጮን እኩል ያዋጣ እንደነበርና ተሻሽሎ የመጣው መመሪያ ግን መዋጮ ገቢን መሰረት ያደረገና በገጠርና በከተማ የተለየ ነው ብለዋል፡፡

እንደ አስተባባሪው አገላለጽ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ማህበረሰቡን ባለው የገቢ መጠን አባል በማድረግ ተገቢውን የጤና አገልግሎት በመስጠት ጤናማ ማህበረሰብ መፍጠር ማስቻል ነው በማለት ለውጤታማነቱ የሁሉም ባለድርሻ አካል ርብርብ የሚጠይቅ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፤

ማንዋሉ ለገጠርና ለከተማ ነዋሪዎች የተለያየ የመክፈያ መስፈርት ያለው ሲሆን የገጠር መለያ መስፈርቶች በእርሻ ሥራ ለተሠማሩ የማህበረሰብ ክፍሎች የእርሻ መሬት ስፋት፣አመታዊ የምርት መጠን፣ የእንስሳት ሀብት ፣የቋሚ ተክል ብዛት ፣የመኖሪያ ቤት አይነት ፣የአትክልት ምርት መጠን፣እንዲሁም የከተማ ለሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎች መለያ መስፈርቶች የተሰማሩበት የንግድ አይነት የተመደበበት የግብር ከፋይነት ደረጃ፣ቤተሰቡ የሚኖርበት ቤት አይነት፣ስፋት የክፍሎች ብዛት ፣በጥቃቅን ሥራዎች በመሠማራት የሚሠራ በአነስተኛ ድርጅቶች፣ በግለሰቦች እና በማህበረሰቡ በመቀጠር የሚሠሩ፣ንብረት ማከራየት የመሳሰሉት ላይ መሰረት ያደረገ ሲሆን የራሱ የምደባ ኮሚቴ ሲኖረው በገጠርም ሆነ በከተማ እንዲሁም እንደ ወረዳ ተጨባጭ ሁኔታ የተመረጡ ግለሰቦች አካቶ ያዋቀረ መሆኑን አገልጸዋል፡፡

ተሳታፊዎች በቀረበው የመዋጮ አከፋፈል ማስፈጸሚያ ማኑዋል ላይ ያላቸውን ጥያቄ በማንሳት የደረሱበት ደረጃ ገና መስራት እናዳለባቸው የሚያመላክት ነው ብለዋል፡፡

አቶ አብዱልሙኒየም አልበሽር በጤና ቢሮ የፕግራም ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ በፕሮግራሞ ማጠቃለያ ላይ በመገኘት እንደተናገሩት የመድረኩ ዋና አላማ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ስራ አጠናክሮ ለማስቀጠል ወሳኝ ወቅት ላይ የምንገኝ በመሆኑ ንቅናቄ ተሰርቶ አባላት የማፍራት ሂደት የሚከናወንበትና ወደ ስራ የሚገባበት ነው በማለት ለባለሞያዎች ተነሳሽነትን በመፍጠር በማኑዋሉ ላይ ጥርት ያለ ግንዛቤ እንዲኖራችሁ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን በመግለጽ ባለሞያዎች በቀሩት አጭር ቀናት ወደ የቀበሌዎች በመውረድ የንቅናቄ ስራዎችን አጠናክረው የማስቀጠል፤ አዳዲስ አባላትን የማፍራት ስራን እንዲሁም መታወቂያን አድሎ በመጨረስ መረጃን የማጥራትና ወደ ኤክ ኤል የማስገባት ስራን መቶ በመቶ በማጠናቀቅ ሃላፊነታችሁን መወጣት ያለባቸው መሆኑን በማስገንዘብ ከዛሬ ጥር 8 እስከ 15 ባሉት ተከታታይ ቀናት ስራዎች መጠናቀቅ እነዳለባቸው በማሳሰብ በተሰጡት ቀናት የማያጠናቅቅ አካል ላይ ቢሮው እርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድ በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡

የክልሉ ጤና ቢሮ!

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ  ክልል መንግስት ጤና ቢሮ በባለፉት 6 ወራት የተከናወኑ ተግባራት  ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር መሻሻሎች  መታየታቸዉን የቢሮ ሀላፊ ክቡር አቶ ወልተጅ በጋሎ ገ...
13/01/2026

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ በባለፉት 6 ወራት የተከናወኑ ተግባራት ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር መሻሻሎች መታየታቸዉን የቢሮ ሀላፊ ክቡር አቶ ወልተጅ በጋሎ ገለፁ።በባለፉት 6 ወራት የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም የቢሮ ማኔጅመንት አባላት በተገኙበት ተገምግሟል ።

(ጥር 5/2018 ዓ.ም) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ወልተጅ በጋሎ በሪፖርት ግምገማ ወቅት በክልሉ መንግስት ጤና ቢሮ በባለፉት 6 ወራት የተከናወኑ ተግባራት እና የተመዘገቡ ዉጤቶች ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር መሻሻሎች መታየታቸዉን ገልጸዋል ።

እነዚህ የታዩ መሻሻሎች ለማስቀጠል በቢሮ በተካሄደው የተቀናጀ ድጋፋዊ ክትትል እና በባለፉት 6 ወራት የሥራ አፈጻጸም የተለዩ ዉስንነቶችን መሠረት በማድረግ ዝቅተኛ አፈፃፀም የተመዘገበባቸው ወረዳዎች እና የጤና ተቋማት ላይ በልዩ ሁኔታክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል ቢሮ ሀላፊዉ ገልጸዋል ።

በተለይም የጤና መረጃ ሥርዓትን ለማዘመን እና ከቢሮ ጀምሮ እስከታችኛዉ የጤና መዋቅሮች የተዘረጉ የተለያዩ የጤና መረጃ ስርዓቶችን በመጠቀም ወቅታዊና ተዓማኒነት ያላቸዉን መረጃዎች ሞልቶ ከመላክ አኳያ አሁንም ክፍተቶች በመኖራቸዉ የሚመለከታቸዉ ዳይሬክቶሬት ትኩረት ሰጥተዉ መስራት እንደአለባቸዉ ቢሮ ሀላፊዉ አሳስበዋል።

የባለፉት 6 ወር የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በቢሮዉ የጤና ልማት ዕቅድ፣ክትትል፣ ግምገማ እና የሪፎርም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ቀርቦ ተገምግሟል ።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ  ክልል መንግስት  ጤና ቢሮ የተደረገው የተቀናጀ ድጋፍዊ ክትትል  የተለዩ ጠንካራ አሰራሮችን  ይበልጥ  ለማስቀጠል  እና የታዩ ተግዳሮቶችን  ለመፍታት የሁሉም  አካላት  ...
13/01/2026

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ የተደረገው የተቀናጀ ድጋፍዊ ክትትል የተለዩ ጠንካራ አሰራሮችን ይበልጥ ለማስቀጠል እና የታዩ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሁሉም አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ መሆኑን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ገለፀ። ቢሮ በክልሉ በተመረጡ የጤና ተቋማት የተደረገውን የተቀናጀ ድጋፋዊ ክትትል አፈጻጸም ገምግሟል ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ወልተጂ በጋሎ የተደረገው የተቀናጀ ድጋፋዊ ክትትል ከቢሮ ጀምሮ እስከታችኛው የጤና መዋቅሮች የተናበበ እና ወጥ የሆነ የአሰራር ሥርዓት ለመዘርጋት ለአሰራር ማነቆ የሆኑ ችግሮችን በወቅቱ ለመፍታት እና ለቀጣይ ወራት አፈጻጸም ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ታልሞ የተደረገዉ የተቀናጀ ድጋፋዊ ክትትል በርካታ ዉጤታማ የሆኑ ሥራዎች የተሰራበት እና ለቀጣይ ሥራዎች አቅጣጫ ያመላከተ ነው ብለዋል።

እነዚህ የተለዩ ጠንካራ አሰራሮችን ለማስቀጠል እና መሻሻል የሚገባቸውን አሰራሮች ለማሻሻል ደግሞ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ መሆኑን የቢሮ ኃላፊው ገልፀዋል ።

በተደረገው የተቀናጀ ድጋፋዊ ክትትል የተለዩ ክፍተቶች የክትባት አገልግሎት እና ቀዝቃዛ ሰንሰለት ተደራሽ ከማድረግ፣ ከቤተሰብ ዕቅድ፣ የሰነ ተዋልዶ ጤና፣ የሥርዓተ ምግብ ፕሮግራም እና የእናቶች ማቆያን ወደ ሥራ የማስገባት ሥራ በእናቶች ወጣቶች ህፃናት ጤና ዳይሬክቶሬት በትኩረት መሰራት እንደአለበት አቶ ወልተጅ ገልጸዋል ።

የጤና ኤክስቴንሽን እና መረታዊ የጤና አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የጤና ጣቢያ ጤና ኬላ ትስስር የማጠናከር፣ የወባ መከላከል ሥራ፣ በሀይጅንና ሳንቴሽን፣ በወረዳ ትራንስፎርሜሽን፣ ሞዴል ቤተሰብ እና ተላላፊ ያልሆኑ ትኩረት የሚሹ በሽታዎች ላይ የተስተዋሉ ክፍተቶች በአጭር ጊዜ ዉስጥ መቅረፍ እንደሚጠበቅበት ተብራርቷል ።

የህክምና መገልገያ መሣሪያዎችና የፋርማሲ አሰተዳደር ሥራዎች በክሊኒካል ዳይሬክቶሬት በልዩ ሁኔታ መስራት እንዳለበት የገለፁት አቶ ወልተጅ በጤና ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማሻሻል እንደሀገር የተቀመጡ ሪፎርሞች ትግበራ ላይ ክትትል መደረግ አለበት ብለዋል።

በክልሉ ከጤና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ በቢሮ ደረጃ የወጡ ደንቦችና መመሪያዎች እንዲሁም የግል ጤና ተቋማት ቁጥጥር እና የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸውን መድሀኒቶች የማስወገድ ሥራ በምግብና መድሀኒት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት መሰራት እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል ።

የበሽታ ዳሰሳ እና ቅኝት እንዲሁም ከቢሮ ጀምሮ የበሽታ ወረርሽኝ ፈጣን ምላሽ አሰጣጥ ሥርዓት በሁሉም ተቋማት ላይ መጠናከር እንዳለበት የህ/ጤ/አ/ቁ/ክ/ምላሽ አሰጣጥ ዳይሬክቶሬት በልዩ ሁኔታ መስራት እንዳለበት የገለፁት ሲሆን የኤች.አይ.ቪ ኤዲስ መከላከል እና መቆጣጠር ሥራዎች በተለይ ኤድስ ፋንድ፣ ሜንስትሪሚንግና ግብዓት አቅርቦት በቀሪ ወራት በትኩረት መፈጸም እንደአለባቸዉ የቢሮ ሀላፊ አቅጣጫ አስቀምጧል ።

ቢሮ ሀላፊ አክለውም የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህንና ማህበራዊ ጤና መድህን ሥራ በቀጣይ ወራት በልዩ ሁኔታ እንደሚሰራ ተናግረዋል ።

ከሰዉ ሀይል ጋር ተያይዞ የሚታየው የሰዉ ሀይል እጥረት ችግሮች ለመቅረፍ የቢሮው የሰዉ ሀብት ልማት ዳይሬክቶሬት ሁሉም ጤና ተቋማት ላይ ያለዉን የሰዉ ሀብት ክፍተት በማጥራት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ለማሟላት መሰራት እንዳለበት አቶ ወልተጅ አስረድተዋል ።

የቢሮ የዕ/ዝ/ክ/ግ/እና ሪፎርም ዳይሬክቶሬት የመረጃ ሥርዓት ለማሻሻል የድጋፍና ክትትል ሥራዉ ተጠናክሮ መቀጠል እንሚገባዉ ሀላፊው አሳስበዋል ።

እነዚህ የተለዩ ጠንካራ አሰራሮችን ለማስቀጠል እና መሻሻል የሚገባቸውን አሰራሮች ለማሻሻል ደግሞ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ መሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸዉን እገዛ እንዲያደርጉ የቢሮ ሀላፊው ጥሪ አቀርበዋል ።

በክልሉ በጤናው ዘርፍ  በሁሉም አከባቢዎች የተካሄደው የተቀናጀ ድጋፋዊ ጉብኝት በዘርፉ የተሻለ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ለመስጠት አቅም የሚፈጥር መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ  አስታወቀ ። ቢሮው ...
12/01/2026

በክልሉ በጤናው ዘርፍ በሁሉም አከባቢዎች የተካሄደው የተቀናጀ ድጋፋዊ ጉብኝት በዘርፉ የተሻለ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ለመስጠት አቅም የሚፈጥር መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ ።

ቢሮው በሁሉም አከባቢዎች በሚገኙ ጤና ተቋማት የተካሄደው የድጋፋዊ ጉብኝት ሪፖርት የቢሮው ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች በተገኙበት ግምገማ እያካሄደ ይገኛል።

ድጋፋዊ ጉብኝቱ በሁሉም የጤና ፕሮግራሞችን በጥልቀት የዳሰሰ ሲሆን በዘርፉ የሚታዩ ጠንካራ አሰራሮችን አጠናክሮ ለማስቀጠል እንዲሁም መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮችን በጥልቀት በመለየት የእርምት እርሚጃ ለመውሰድ የሚያግዝ መሆኑንም ተመላክቷል።

የድጋፋዊ ጉብኝት ሪፖርቱ የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊ አቶ ወልተጂ በጋሎ በተገኙበት እየተገመገመ የሚገኝ ሲሆን በቀረቡ ሪፖርቶች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል ።

የክልሉ ጤና ቢሮ!

የወጣቶች  እና አፍላ ወጣቶች  የስነ ተዋልዶ  ጤና ለማሻሻል  የጤናና የትምህርት  መዋቅሮች  ቅንጅታዊ አሰራር  ወሳኝ  መሆኑ  ተገለፀ። በቤኒሻንጉል  ጉሙዝ  ክልል በአሶሳ ዞን በሆሞሻ ወ...
10/01/2026

የወጣቶች እና አፍላ ወጣቶች የስነ ተዋልዶ ጤና ለማሻሻል የጤናና የትምህርት መዋቅሮች ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ዞን በሆሞሻ ወረዳ በተመረጡ 15 ት/ቤቶች እና በ2 ጤና ጣቢያዎች በባለፉት 6 ወራት የተከናወኑ ተግባራት ተገምግሟል ።

የወጣቶች እና የአፍላ ወጣቶች ስነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት ለማሻሻል በክልሉ በፖይሌት ከተመረጡ ወረዳዎች መካከል አንዱ የሆሞሻ ወረዳ ነው ።

በወረዳው በጤና እና በትምህርት መዋቅሮች ቅንጅታዊ አሰራር የወጣቶችና አፍላ ወጣቶች የስነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት ከተጀመረ 6 ወራትን አስቆጥሯል ።

በባለፉት 6 ወራት የተከናወኑ ሥራዎችን የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በመገምገም ጠንካራ አሰራሮችን አጠናክሮ ለማስቀጠል እና መሻሻል በሚገባቸው አሰራሮች ላይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ የግምገማ መድረክ መዘጋጀቱን የቤ/ጉ/ክ/መ/ጤና ቢሮ የእናቶች፣ወጣቶች፣ህፃናት እና ሥርዓተ ምግብ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ገልጸዋል ።

በወረዳው በባለፉት 6 ወራት በተመረጡ ት/ቤቶችና ጤና ጣቢያዎች የተከናወኑ ተግባራት የሥራ አፈጻጸም አበረታች ቢሆንም በአንዳንድ ት/ቤቶች የተመዘገቡ ዉጤቶች አበረታች ባለመሆናቸው የትምህርት መዋቅሮችና የጤና መዋቅሮች በመቀናጀት የህብረተሰቡን ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራዎች መሠራት እንደአለባቸዉ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል ።

በመድረኩ ላይ ከክልል ጤና ቢሮ፣ከአሶሳ ዞን ጤና መምሪያ፣ከክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ እንዲሁም ከሆሞሻ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት፣ትምህርት ጽ/ቤት እና የ15 ት/ቤት ርዕሳነ መምራን ተገኝተዋል ።

በክልሉ የቤተሰብ ዕቅድ  አገልግሎትን በማሻሻል ተደራሽነቱን ለማረጋገጥ የወንዶች ተሳትፎ ማጠናከር እንደሚገባ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ። የክልሉ ጤና ቢሮ ከጤና ሚኒስቴር ጋር ...
09/01/2026

በክልሉ የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎትን በማሻሻል ተደራሽነቱን ለማረጋገጥ የወንዶች ተሳትፎ ማጠናከር እንደሚገባ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ ገለጸ።

የክልሉ ጤና ቢሮ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በስነ-ተዋልዶ ጤና በተለይ የቤተሰብ ዕቅድ ተጠቃሚነት ላይ የወንዶች ተሳትፎን ለማጠናከር የሚያግዝ የንቅናቄ መድረክ በአሶሳ ከተማ ተካሂደዋል።

በጤና ሚኒስቴር የቤተሰብ ዕቅድ የስነ-ተዋልዶ ወጣቶች ጤና ዲስክ ሀላፊ ዶ/ር አለማየሁ ሁንዱማ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እንደ ሀገር በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

አገልግሎቱን በማጠናከር የሚከሰተውን የእናቶችና የህጻናት ሞት መቀነስ ይገባል ያሉት ዶ/ር አለማየሁ በተለይ በዘርፉ የሚታዩ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችና የተሳሳቱ አመለካከቶች ለመቅረፍ በጋራ መረባረብ እንደሚገባም ነው የጠቆሙት ።

የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ አብዱልሙኒየም አልበሽር በዚህ ወቅት እንዳሉት በክልሉ የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት ተደራሽነት 39 % ላይ መሆኑን ገልጸዋል።

አገልግሎቱን በሚፈለገው መልኩ ተደራሽ ለማድረግ ብዙ ይቀራል ያሉት ምክትል ቢሮ ሀላፊው በተለይ የተሳሳቱ ግንዛቤዎች፣የባህል ተጽዕኖዎች እንዲሁም የእምነት ተጽዕኖዎችና ለሎች ምክንያቶች በቅንጅት ማስቀረት እንደሚገባም አስገንዝበዋል ።

የሀማኖት አባቶችን ጨምሮ፣በየደረጃው የሚገኙ አመራር አካላት፣የሚዲያ አካላትና ለሎች ባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲወጡም ምክትል ቢሮ ሀላፊው ጥሪ አቅርበዋል።

በስነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት ዙሪያ የወንዶች ተሳትፎ አስፈላጊና ወሳኝ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በጤና ሚኒስቴር የሚኒስትር ደኤታ አማካሪ ፕሮፌሰር ስለሺ ጋሩማ ሲሆን ወንዶች ሴቶችን በማገዝ በዚህ ዘርፍ ግንባር ቀደም ተሳትፎ እንዲያደርጉም አሳስበዋል ።

በአሶሳ ከተማ በተካሄደው የንቅናቄ መድረክ ላይ የጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች፣የክልል የዞንና የወረዳ የስራ ሀላፊዎች፣የሀማኖት አባቶችና ለሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን በስነ ተዋልዶ ጤና ላይ ያተኮረ ሀገራዊና ክልላዊ ሰነዶች ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

ለመላው  የክርስቲና  እምነት  ተከታዮች  በሙሉ።እንኳን ለጌታችንና  ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ  የልደት በዓል በሠላም አደረሳችሁ! አደረሰን !ብርሃነ ልደቱ የእግዚአብሔር ሰላምና ፍቅ...
06/01/2026

ለመላው የክርስቲና እምነት ተከታዮች በሙሉ።

እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሠላም አደረሳችሁ! አደረሰን !

ብርሃነ ልደቱ የእግዚአብሔር ሰላምና ፍቅር ለሰው ልጆች ሁሉ የታወጀበት በዓል በመሆኑ በዓሉን ስናከበር ለሰው ልጆች ሁሉ ፍቅር በመስጠት፣ የተቸገሩትን በመደገፍ፣ የተራቡትን በማብላት የክርስቲያናዊ ግዴታችን በመወጣት ሊሆን ይገባል፡፡

መልካም የልደት በዓል !

ክቡር አቶ ወልተጅ በጋሎ
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ
ታህሳስ 28 / 2018 አሶሳ

Address

Asosa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Benishangul Gumuz Health Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Benishangul Gumuz Health Bureau:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram