Awaash Magaalahe Xiinissok Qaafiyate Fenteeyna

Awaash Magaalahe Xiinissok Qaafiyate Fenteeyna "እኛ ማህበረሰባችን ውስጥ ነን "

የ 2017 አመታዊ  የ ስራ ሪፖርት ግምገማ እና የ 2018 አመታዊ የስራ ዕቅድ ዝግጅት፨፨፨በዛሬው ዕለት የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የ18  ዲፓርትመንት ሀላፊዎችም ከጠዋቱ 2 ሰዐት በተገ...
28/07/2025

የ 2017 አመታዊ የ ስራ ሪፖርት ግምገማ እና የ 2018 አመታዊ የስራ ዕቅድ ዝግጅት፨፨፨

በዛሬው ዕለት የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የ18 ዲፓርትመንት ሀላፊዎችም ከጠዋቱ 2 ሰዐት በተገኙበት አመታዊ የስራ ሪፖርት ግምገማ እና ለ 2018 የስራ ዕቅዶችን የተቋሙ ሀላፊ አቶ አሊ አደም ባሉበት አስጀምረዋል ፣አክለውም የተቋሙ ሀላፊ የሪፖርት ግምገማው ለ 7 ቀናት የሚካሄድ ሲሆን በየ ዲፓርትመንቱ ያሉ ችግሮች ከስራው ጋር በተያያዘ ቀርቦ ለማህበረሰቡ የተሻለና ጥራት ያለው አገለግሎት ለመስጠትና ለ 2018 የተሻለ የስራ አፈፃፀሞችን ይበልጥ ለማድረግ እንሚረዳና ተቋሙም አስፈላጊውን ግምገማ አድርጎ ከጨረሰ በኋላ ክፍተት የታየባቸውን ዲፓርትመንቶች አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትልም ለማድረግም ዝግጁ እንደሆነ ገልፀዋል ፨፨፨

የማህበረሰባችንን የውስጥ ትርታ እናዳምጣለን ፨፨፨በዛሬው ዕለት በ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ከሁሉም ቀበሌ የተውጣጡ የማህበረሰቡ ተወካዮች በሁሉም ቀበሌ የህዝብ ውይይት ( Conference ...
18/07/2025

የማህበረሰባችንን የውስጥ ትርታ እናዳምጣለን ፨፨፨

በዛሬው ዕለት በ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ከሁሉም ቀበሌ የተውጣጡ የማህበረሰቡ ተወካዮች በሁሉም ቀበሌ የህዝብ ውይይት ( Conference ) አድርገው ተቋሙ ላይ ማህበረሰቡ ባነሷቸው ጥያቄዎች ላይ ከ ህዝብ ተወካዮች ኮሚቴ ጋር ከጤና ጣቢያው ሀላፊ አቶ አሊ አደም ጋር ውይይት አድርገዋል አክለውም ኮሚቴው ከህዝቡ በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ጤና ተቋሙ ካለበት ጥሩ ጎን ባሻገር ተያያዥ ክፍተቶቹም ስላሉ ክፍተቶችን በምን አይነት መልኩ መስተካከል እንደሚችሉ የጤና ተቋሙን ሀላፊ ጠይቀዋል አቶ አሊ አደም የህዝቡን ተወካዮች አመስግነው በተነሱ ጥያቄዎች ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያ በመስጠትና ተቋሙ ያለበትን ችግሮች በአስቸኳይ ለማስተካከልና የህዝቡን ጥያቄ ከዚሁ ኮሚቴ ጋር ሆነው ደረጃ በደረጃ እንደሚፈቱ ቃል ገብተዋል የአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ከማህበረሰቡ ጎን ሆኖ አገልገሎቱን ለተገልጋዮች ምቹ እና ቀልጣፋ እንደሚያደርግ ተቋማችን ለ አዋሽ ህዝብ ጥሪውን ያስተላልፋል ፨፨፨

ለማህበረሰባችን የጤና ትምህርት ፨፨፨በዛሬው ዕለት ከ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የተውጣጡ ጤና ባለሙያዎች የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራሙን ለመደገፍ በ3 ቀበሌዎች ላይ በእናቶችና ህፃናት , በክ...
10/07/2025

ለማህበረሰባችን የጤና ትምህርት ፨፨፨

በዛሬው ዕለት ከ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የተውጣጡ ጤና ባለሙያዎች የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራሙን ለመደገፍ በ3 ቀበሌዎች ላይ በእናቶችና ህፃናት , በክትባት , በማህፀን በር ጫፍ ካንሰር ዙሪያ ማህበረሰቡን ሰብስበው ትምህርት ሰጥተዋል ለዚህ ፕሮግራም አስተዋጽኦ ላደረጉ የቀበሌ በጎ ፍቃደኞችን እንደ ተቋም ምስጋናችንን እናቀርባለን ፨፨፨፨፨

እኛ እንደ ተቋም ለደካሞች ድጋፍ እንሆናለን የ እርስዎስ ድርሻ ምንድነው?፨፨፨የአዋሽ  ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ባለሙያዎች አረጋውያንን አቅመደካማ ሆነው ምንም ረዳት የሌላቸውን ማህበረሰቦች ያሉበ...
09/07/2025

እኛ እንደ ተቋም ለደካሞች ድጋፍ እንሆናለን የ እርስዎስ ድርሻ ምንድነው?፨፨፨

የአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ባለሙያዎች አረጋውያንን አቅመደካማ ሆነው ምንም ረዳት የሌላቸውን ማህበረሰቦች ያሉበት ድረስ ወርደው በባለሙያዎች በየወሩ አደሞዝ ላይ የሚዋጣ ገንዘብ መድሀኒት ገዝተው በማገልገል ላይ 🙏🙏

እኛ ማህበረሰባችን ውስጥ ነን ፨፨ለማህበረሰባችን አስፈላጊውን የጤና ትምህርት ባሉበት ቀበሌ ድረስ ወርደን በቂ ግንዛቤ በመስጠት የማህበረሰባችንን ጤና በራሳቸው እንዲጠብቁ የበኩላችንን እንወጣ...
08/07/2025

እኛ ማህበረሰባችን ውስጥ ነን ፨፨

ለማህበረሰባችን አስፈላጊውን የጤና ትምህርት ባሉበት ቀበሌ ድረስ ወርደን በቂ ግንዛቤ በመስጠት የማህበረሰባችንን ጤና በራሳቸው እንዲጠብቁ የበኩላችንን እንወጣለን ፨፨፨

የእርጉዝ እናት ህመም የጋራችን ነው ፨በዛሬው ዕለት የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ እንደ ከተማ የቤት ውስጥ ወሊድን ለመቆጣጠርና በእርግዝና ወቅት ለሚከሰቱ ተያያዥ ችግሮች በቀበሌ ደረጃ ወርደ...
19/06/2025

የእርጉዝ እናት ህመም የጋራችን ነው ፨

በዛሬው ዕለት የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ እንደ ከተማ የቤት ውስጥ ወሊድን ለመቆጣጠርና በእርግዝና ወቅት ለሚከሰቱ ተያያዥ ችግሮች በቀበሌ ደረጃ ወርደው የ እርጉዝ እናቶች ኮንፍረንስ አካሂደዋዋል ፨፨

የ9ተኛ ወር የ ስራ ሪፖርት ግምገማ ፨፨በዛሬው ዕለት የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የ14 ዲፓርትመንት ሀላፊዎችም ከሰዐት በኋላ በተገኙበት የ9ተኛ ወር ሪፖርት ግምገማ የተቋሙ ሀላፊ አቶ አሊ...
03/06/2025

የ9ተኛ ወር የ ስራ ሪፖርት ግምገማ ፨፨

በዛሬው ዕለት የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የ14 ዲፓርትመንት ሀላፊዎችም ከሰዐት በኋላ በተገኙበት የ9ተኛ ወር ሪፖርት ግምገማ የተቋሙ ሀላፊ አቶ አሊ አደም ባሉበት አስጀምረዋል ፣አክለውም የተቋሙ ሀላፊ የሪፖርት ግምገማው ለ 7 ቀናት የሚካሄድ ሲሆን በየ ዲፓርትመንቱ ያሉ ችግሮች ከስራው ጋር በተያያዘ ቀርቦ ለማህበረሰቡ የተሻለና ጥራት ያለው አገለግሎት ለመስጠትና የስራ አፈፃፀሞችን ይበልጥ የተሻለ ለማድረግ እንሚረዳና ተቋሙም አስፈላጊውን ግምገማ አድርጎ ከጨረሰ በኋላ ክፍተት የታየባቸውን ዲፓርትመንቶች አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትልም ለማድረግም ዝግጁ እንደሆነ ገልፀዋል ፨፨፨

 #የልፋትህ ውጤት በተግባር ሲመዘን 🙏🙏🙏፨፨፨በ2016 እንደ ተቋም ለማህበረሰቡ የተሻለ አገልገሎት በመስጠትና የማህበረሰብ ተሳትፎና የመጀመሪያ ደረጃ ጤና እንክብካቤ አሀድ በጥራት የላቀ አፈ...
03/06/2025

#የልፋትህ ውጤት በተግባር ሲመዘን 🙏🙏🙏፨፨፨

በ2016 እንደ ተቋም ለማህበረሰቡ የተሻለ አገልገሎት በመስጠትና የማህበረሰብ ተሳትፎና የመጀመሪያ ደረጃ ጤና እንክብካቤ አሀድ በጥራት የላቀ አፈፃፀም በማምጣት እንደ ክልል 2ተኛ ደረጃ በመውጣት ከ ክልል ጤና ቢሮ ይህን የእውቅና ሰርተፊኬት ከ ጤና ሚኒስቴር 2 Desketop በዋጋቸው 105,400 ተበርክቶልናል !! ይህንንም ተከትሎ እንደ ተቋም በ 2016 የተለያዩ ችግሮችን ተቋቁመን ለማህበረሰቡ የተሻለ አገልገሎት በመስጠት ረገድ ከፍተኛ ሚናውን የተጫወታቹህ የ ጤና አጠበበቅ ጣቢያ ባለሙያዎች እጅጉን እንደ ተቋም እያመሰገንን ነገር ግን ይህ ደረጃ እንደ ተቋም የምንሰጠውን አገልገሎት ስለማይመጥን እንደ ሀገር ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን በ 2017 የተሻለ አፈፃፀም ለማምጣት የሁላችንም ቁርጠኝነት ስለሚፈልግ ከወዲሁ ዝግጁ እንድትሆኑ ተቋሙ ጥሪውን ያቀርባል ፨፨፨

Hawaash Magaalah XiinissoLaqin alsak 23/2017.ILL**********************************************************************👉a...
31/05/2025

Hawaash Magaalah Xiinisso
Laqin alsak 23/2017.ILL
**********************************************************************
👉asaakih ayro awaashe magaalah xiinissok qaafiyat fanteynal rakaakayak fayaale mirac masakadda le cuseen bolkoq kee magaala xiinissoh abba masakadda le qabdo qali kee mgaala^miraaciinuuy,awda^miraaciinuuy,qaafiyat mihratleelaay,ayyunti edde angaluk qaafiyat fannteynal saytunaane taama abak maacisneen 🙏

የአዋሽ ከተማ አስተዳደር
ግንቦት 23/2017 ዓ.ም
**************************************************************************
👉በዛሬው ቀን በአዋሽ ከተማ ከንቲባ ጤና ጣቢያ በመገኛት የክልሉ ከፍተኛ አመራር የሆኑት የተከበሩ አቶ ሁሴንቦልኮእ መሀመድ እና የከተማው ከንቲባ አብዶ አሊ አንዲሁም የከተማው አመራር ,የቀበሌ አመራሮች ,የጤና ባለሞያዎች ከህዝብ ገራ በመሆን በጤና ጣቢያ ውስጥና አከባቢው ፅዳት ባማራ መልኩ አድርገዋል🙏

አከባቢን በማፅፅዳት ጤናኛ መህበረሰብ በመፍጣር ከተማችንን ዉብና ፅዱ ለኑሮ ምቹ በመድረግ የከተማችንን እንዲሁም የህዝባችን ብልፅግና እውን አናርግ ❤🙏❤👌

የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ (Mpox) መተላለፊያ እና መከላከያ መንገዱ*****የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ (Mpox) “ክሌድ 1” እና “ክሌድ 1ቢ” በሚባሉ በሁለት ዋነኛ የቫይረስ ዝርያዎች አማካይነ...
26/05/2025

የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ (Mpox) መተላለፊያ እና መከላከያ መንገዱ
*****

የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ (Mpox) “ክሌድ 1” እና “ክሌድ 1ቢ” በሚባሉ በሁለት ዋነኛ የቫይረስ ዝርያዎች አማካይነት ሲሠራጭ ቆይቷል።

“ክሌድ 1” የሚባለው የቫይረሱ ዓይነት በማዕከላዊ አፍሪካ በስፋት የሚገኝ ሲሆን፣ “ክሌድ 1ቢ” የተባለው ደግሞ ከ“ክሌድ 1” ኋላ እየተስፋፋ ያለ እና በጣም አደገኛ መሆኑ ይነገራል።

በፈረንጆቹ 2022 ቀለል ያለው እና በምዕራብ አፍሪካ የሚገኘው “ክሌድ 2” የተባለው የበሽታው ዝርያ በዓለም ዙሪያ በወረርሽኝ መልክ ተከስቶ እንደነበር መረጃዎች ያመላክታሉ።

በወቅቱ በሽታው ቫይረሱ ተከስቶባቸው የማያውቁት የአውሮፓ እና የእስያ አገራትን ጨምሮ 100 በሚጠጉ አገራት ውስጥ ተከስቶ ነገር ግን ለበሽታው ተጋላጭ የሆኑ ሰዎችን በመከተብ ወረርሽኙ በቁጥጥር ስር ውሏል።

የበሽታው ምልክቶች

በዝንጀሮ ፈንጣጣ በተያዘ ሰው ላይ መጀመሪያ የሚታዩት ምልክቶች ትኩሳት፣ ራስ ምታት፣ እብጠት፣ ጀርባ ህመም እና የጡንቻ ህመምን ያካትታል።

ትኩሳት ከተከሰተ በኋላ ከፊት ጀምሮ ቀሪውን የሰውነት ክፍልን የሚያዳርስ ሽፍታ የሚከሰት ሲሆን፣ በአብዛኛው በእጅ መዳፍ እና በእግር መረገጫ ላይ ይከሰታል።

በሰውነት ላይ የሚያጋጥመው ሽፍታ በጣም የሚያሳክክ እና የሚቆጠቁጥ ሲሆን፣ በተለያዩ የለውጥ ደረጃዎች ውስጥ አልፎ በመጨረሻም እብጠት በመፍጠር ኋላ ላይም ይከስማል።

ቁስለቱም ጠባሳን ትቶ ሊያልፍ ይችላል።

በሽታው በአብዛኛው ከሁለት እስከ ሦስት ሳምንት ባለው ጊዜ ውስጥ በራሱ የሚጠፋ ይሆናል።

በበሽታው የተያዘው ሰው በጣም የተጎዳ ከሆነ፣ ቁስለቱ አጠቃላይ ሰውነቱን፣ በተለይ አፍ፣ ዐይን እና የመራቢያ አካላት ላይ ከባድ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል።

የበሽታው ከሰው ወደ ሰው የመተላለፊያ መንገድ

በሽታው ቤተ ሙከራ ውስጥ በሚደረግ ምርመራ የሚገኝ ቫይረስ ሲሆን፣ በሰውነት ንክኪ ይተላለፋል።

የዝንጀሮ ፈንጣጣ ወሲባዊ ግንኙነትን፣ የቆዳ ንክኪን እና በቅርብ ርቀት ላይ ሆኖ ማውራትን ወይም መተንፈስን ጨምሮ በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር በሚኖር የቀረበ ግንኙነት ከሰው ወደ ሰው ይተላለፋል።

የበሽታው ቫይረስ ወደ ሰውነት በቆሰላ ቆዳ፣ በመተንፈሻ አካላት፣ በዐይን፣ በአፍንጫ ወይም በአፍ በኩል ሊገባ ይችላል።

በቫይረሱ የተበከሉ የመኝታ አልባሳት፣ በልብሶች እና በፎጣዎች አማካይነት በሚኖር ንክኪም በሽታው ሊተላለፍ ይችላል።

ቫይረሱ ካለባቸው ዝንጀሮ እና አይጦችን ከመሳሳሉ ጋር የሚኖር ንክኪም ሌላኛው የበሽታው መተላለፊያ መንገድ ነው።

ከሁለት ዓመት በፊት የዝንጀሮ ፈንጣጣ በዓለም ዙሪያ በበርካታ ሀገራት ውስጥ በተከሰተበት ጊዜ ቫይረሱ በዋናነት በወሲባዊ ግንኙነት በሚፈጠር ንክኪ አማካይነት ነበር የተሠራጨው።

ባለፈው ዓመትም በዲሞክራቲክ ኮንጎ ውስጥ የተከሰተው የበሽታው ወረርሽኝ የተስፋፋው በወሲባዊ ግንኙነት በሚፈጠር ንክኪ ሲሆን፣ ነገር ግን በሌሎችም አካባቢዎች ተመሳሳይ ቫይረስ ሊገኝ ችሏል።

መከላከያ እና ህክምናው

የዝንጀሮ ፈንጣጣን ለማከም የተዘጋጀ ህክምና የታመሙ ሰዎችን ለማዳን በጣም ጠቃሚ ቢሆንም፣ ነገር ግን ህክምናው ምን ያክል ውጤታማ እንደሆነ የሚያሳይ ውስን ጥናት እንዳለ ነው የሚገለጸው።

የዝንጀሮ ፈንጣጣ ወረርሽኝን፣ በሽታውን በመከላከል መቆጣጠር የሚቻል ሲሆን፣ ይህንንም ለማድረግ ተመራጩ መንገድ የመከላከያ ክትባት መስጠት ነው።

በአሁኑ ጊዜ ሦስት በሽታውን መከላከያ የክትባት ዓይነቶች ቢኖሩም፣ ክትባቶቹ የሚሰጡት ለበሽታው ተጋላጭ ለሆኑ እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር የቀረበ ንክኪ ላላቸው ብቻ ነው።

ይሁንና ያሉት የክትባት ዓይነቶች አዲስ ከተከሰተው የበሽታው ዝርያ አንፃር ምን ያክል የመከላከል አቅም አላቸው የሚለውን ለማወቅ ተጨማሪ ሙከራዎች ማድረግ ስለሚያስፈልግ፣ የዓለም ጤና ድርጅት ሁሉም ሰው መከተብ አለበት ብሎ አይመክርም።

ባለፈው ዓመትም የአፍሪካ ህብረት ለኮቪድ ተመድቦ ከነበረ ገንዘብ ላይ 10.4 ሚሊየን ዶላር ለሲዲሲ በመስጠት የዝንጀሮ ፈንጣጣን ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት መደገፉን የቢቢሲ ዘገባ አመላክቷል።

የአፍሪካ ሲዲሲ እንደሚለው ካለፈው ዓመት ጥር መጀመሪያ አንስቶ እስከ ሐምሌ መጨረሻ ድረስ ባሉት ሰባት ወራት ውስጥ ከ14 ሺህ 500 በላይ በዝንጀሮ ፈንጣጣ የተያዙ ሰዎች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ከ450 በላይ ሰዎች ደግሞ በበሽታው ህይወታቸው አልፏል።

የበሽታው ክስተት 96 በመቶው በዲሞክራቲክ ኮንጎ ውስጥ የተመዘገበ ሲሆን፣ ጎረቤት ወደሆኑት እና የዝንጀሮ ፈንጣጣ እምብዛም ወደ ማይታወቅባቸው ቡሩንዲ፣ ኬንያ፣ ሩዋንዳ እና ኡጋንዳ ተስፋፍቶ እንደነበርም ይታወሳል።

17/9/2017

በወቅታዊ የጤና አገልግሎት ዙሪያ ከጤና ሚኒስቴር የተሰጠ መግለጫ*****************የጤና ሚኒስቴር ለማኅበረሰባችን ጥራቱን የጠበቀ እና ፍትሐዊ የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የጤ...
15/05/2025

በወቅታዊ የጤና አገልግሎት ዙሪያ ከጤና ሚኒስቴር የተሰጠ መግለጫ
*****************
የጤና ሚኒስቴር ለማኅበረሰባችን ጥራቱን የጠበቀ እና ፍትሐዊ የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የጤና ፖሊሲ እና ስትራቴጂ በመቅረጽ የኅብረተሰቡን ባለቤትነት ባረጋገጠ መልኩ ሥራዎችን በትኩረት እያከናወነ መሆኑ የዐደባባይ ሐቅ ነው።

ምክንያቱም መቼምና በምንም ሁኔታ መቋረጥ ከሌለባቸው ማኅበራዊ አገልግሎቶች አንዱ የጤና አገልግሎት በመሆኑ፤ ስለዚህም ዛሬን ጨምሮ ባለፉት ቀናት በመላ ሀገራችን በሚገኙ የጤና ተቋማት እንደ ወትሮው ሁሉ መደበኛ የጤና አገልግሎቶች ለማኅበረሰባችን ያለምንም መቆራረጥና መስተጓጎል እየተሰጡ ይገኛሉ፡፡

ይሄንን የተረዳው የጤና ባለሞያ በማኅበራዊ ሚዲያ በሚሠራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች ጫና ሳይገፋ የገባውን የሞያ ቃል ኪዳን እና መሐላ ጠብቆ ማኅበረሰቡን እያገለገለ በመሆኑ ምስጋና ይገባዋል፡፡

ይሁን እንጂ በጥቂት የማስተማሪያ የጤና ኮሌጆች/ተቋማት በመደበኛ የሥራ ገበታቸው ላይ ያልተገኙ የተወሰኑ ባለሞያዎች እንዳሉ መረጃዎች ደርሰውናል፡፡ ከእነዚህ የጤና ባለሞያዎች መካከል ብዙዎቹ በሐሰተኛ መረጃ የተወናበዱ ሲሆኑ ጥቂቶቹ ደግሞ ጥፋትን ዓላማቸው ያደረጉ ናቸው።

ድርጊቱ የራስን ቤተሰብ፣ ዘመድ፣ ወገን እና መላውን ማኅበረሰብ ከመጉዳት ባለፈ ከሞያ ሥነ ምግባር፣ ከሰብአዊነት አኳያ ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው።

ከሕግ አኳያም የጤና ሞያ የሥራ ማቆም አድማ ከማይደረጉባቸው የሥራ ዘርፎች መካከል አንዱ መሆኑ በግልጽ ተደንግጓል። የጤና ባለሞያዎች ጥያቄ እንኳን ቢኖራቸው በሥራ ገበታቸው ተገኝተው መደበኛ ሥራቸውን እያከናወኑ ጉዳያቸውን ለሚመለከተው አካል ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

በመሆኑም እነዚህ የጤና ባለሞያዎች ወደ ሥራ ገበታቸው ተመልሰው ማኅበረሰባቸውን እንዲያገለግሉ በየተቋማቸው ጥሪ ተደርጓል።

መንግሥት የጤና ባለሞያውን ዘላቂ ተጠቃሚነት ባረጋገጠ መልኩ በጥናት ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ለመስጠት ቀደም ብሎ የጤና አገልግሎት አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ 1362 /2017 አጸድቆ ደንብና መመሪያዎችን በማውጣት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል።

በጎ ኅሊና ያላቸው የጤና ባለሞያዎች ይህንን በመገንዘብ ሥራቸውን በአግባቡ እንዲያከናውኑ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤታችን በዚሁ አጋጣሚ ጥሪ ያቀርባል።

በሌላ በኩል ደግሞ ኅብረተሰቡ በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች በሚሠራጩ የሐሰት መረጃዎች ሳይረበሽ የሚፈልገውን የጤና አገልግሎት በተለመደው መልኩ በጤና ተቋማት ማግኘት እንደሚችል እናሳውቃለን ።

መንግሥት በሆደ ሰፊነት ችግሩን ለመፍታት ያሳየውን ትዕግሥት ወደጎን በመተው በሥራ ገበታቸው ላይ ባልተገኙ እንዲሁም በጤና ተቋሙም ሆነ ከጤና ተቋሙ ውጭ ሆነው ሁከትና ብጥብጥ በሚፈጥሩት ላይ አስፈላጊ የሆነ ሕጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ቀድመን እናሳውቃለን፡፡

የጤና ሚኒስቴር

#አፋብክመጤናቢሮ


የ6 ወር የ ስራ ሪፖርት ግምገማ ፨፨በዛሬው ዕለት የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የ14 ዲፓርትመንት ሀላፊዎችም በተገኙበት የ6 ወር ሪፖርት ግምገማ የተቋሙ ሀላፊ አቶ አሊ አደም ባሉበት አስጀ...
29/01/2025

የ6 ወር የ ስራ ሪፖርት ግምገማ ፨፨

በዛሬው ዕለት የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የ14 ዲፓርትመንት ሀላፊዎችም በተገኙበት የ6 ወር ሪፖርት ግምገማ የተቋሙ ሀላፊ አቶ አሊ አደም ባሉበት አስጀምረዋል ፣አክለውም የተቋሙ ሀላፊ የሪፖርት ግምገማው ለ 7 ቀናት የሚካሄድ ሲሆን በየ ዲፓርትመንቱ ያሉ ችግሮች ከስራው ጋር በተያያዘ ቀርቦ ለማህበረሰቡ የተሻለና ጥራት ያለው አገለግሎት ለመስጠትና የስራ አፈፃፀሞችን ይበልጥ የተሻለ ለማድረግ እንሚረዳና ተቋሙም አስፈላጊውን ግምገማ አድርጎ ከጨረሰ በኋላ ክፍተት የታየባቸውን ዲፓርትመንቶች አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትልም ለማድረግም ዝግጁ እንደሆነ ገልፀዋል ፨፨፨

Address

Awash

Telephone

+251938664444

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Awaash Magaalahe Xiinissok Qaafiyate Fenteeyna posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram