Awaash Magaalahe Xiinissok Qaafiyate Fenteeyna

Awaash Magaalahe Xiinissok Qaafiyate Fenteeyna "እኛ ማህበረሰባችን ውስጥ ነን "

 #የእርሶ አስተያየት ለኛ ገንቢ ነው ፨፨፨ወደ ተቋማችን ስትመጡ ይህንን "QR CODE "በስልካቹህ Scan በማድረግ በአገልግሎት አሰጣጡ ዙሪያ ያሉ መስተጓጐሎችን ለመቀነስ ይረዳን ዘንድ በተ...
31/03/2026

#የእርሶ አስተያየት ለኛ ገንቢ ነው ፨፨፨

ወደ ተቋማችን ስትመጡ ይህንን "QR CODE "በስልካቹህ Scan በማድረግ በአገልግሎት አሰጣጡ ዙሪያ ያሉ መስተጓጐሎችን ለመቀነስ ይረዳን ዘንድ በተቋሙ ግድግዳዎች ላይ ስለተለጠፉ አስተያየታቹሁን እንድትሰጡን ስንል ጥሪ እናቀርባለን ፨፨፨

 # # #    የማህበረሰባችን አስተያየት ለኛ ገንቢ ነው ፨፨፨በዛሬው ዕለት የአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የሚያገለግለውን ማህበረሰብ አስተያየት ለመቀበልና አገልግሎቱን የበለጠ እንዲያሻሽል ይ...
29/03/2026

# # # የማህበረሰባችን አስተያየት ለኛ ገንቢ ነው ፨፨፨

በዛሬው ዕለት የአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የሚያገለግለውን ማህበረሰብ አስተያየት ለመቀበልና አገልግሎቱን የበለጠ እንዲያሻሽል ይረዳው ዘንድ ከቀድሞው ያረጀና አሰልቺ ከሆነ አስተያየት መስጫ ሳጥን አንድ እርምጃ ከፍ በማለት ማንኛውንም አገልግሎት ላይ የተለያዩ መስተጓጎሎችን ለመቀነስና የተገልጋዩን እርካታ ለሟሟላት የ ኤሌክትሮኒክስ አስተያየት መቀበያ ድህረገጽ ያስተዋወቅን በመሆኑ ማንኛውም የከተማውም ሆነ ከ አጎራባች ወረዳዎች የምትመጡ ተገልጋዮቻችን ተቋሙ ላይ የሚስተዋሉ በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮችን በቀጥታ ወደ መተግበሪያው አስተያየት መስጫ ስትገቡ ለ ተቋሙ ሀላፊ አቶ አሊ አደም በእጃቸው ባለው ስልክ መልእክቱ ስለሚደርሳቸው ተቋሙም በአፋጣኝ ለ ችግሩ መልስ በመስጠት አልያም ደሞ አስተያየትዎን ተቀብለው ችግሩ ለማስተካከል ስለሚረዳ የናንተ አስተያየት ለተቋማችን ገንቢ በመሆኑ ከታች ባለው Link በመንካት መተግበሪያውም ለአጠቃቀም ምቹና ዘመናዊ በመሆኑ እንዲሁም ተቋም ላይ በምትመጡ ሰአት QR CODE በተቋሙ ግድግዳዎች ስለምንለጥፍ ለተሻለ አገልግሎት በጋራ ተረባርበን የበኩላቹሁን እንድትወጡ ሲል ተቋሙ ጥሪውን ያስተላልፋል ፨፨

http://awash7healthcenter.rf.gd

 #ተቋማችንን ለተገልጋዮች ምቹ ለማድረግ አስፈላጊውን ርብርብ ማድረግ ቀዳሚ ተግባራችን ነው ፨በዛሬው ዕለት የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ለ ተቋሙ የቀለም እድሳት ድጋፍ በጠየቀዉ መሠረት የሚ...
20/02/2026

#ተቋማችንን ለተገልጋዮች ምቹ ለማድረግ አስፈላጊውን ርብርብ ማድረግ ቀዳሚ ተግባራችን ነው ፨

በዛሬው ዕለት የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ለ ተቋሙ የቀለም እድሳት ድጋፍ በጠየቀዉ መሠረት የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ድርጅት ከ ከፍተኛው ቢሮ የመጡና አዋሽ ካለው የቅርንጫፉ ስራ አስኪያጆች ጋር የተቋሙን ቀለም ለማስቀባት በተቋሙ ሀላፊ አቶ አሊ አደም ቢሮ ተገኝተው ተቋሙን እድሳት ለማድረግ ቁርጠኛ አቋማቸውን ገልፀው ተቋሙ የቀለም እድሳቱን በምን መልኩ እንደሚደረግ ተወያይተው የተቋሙን ካሬ ለክተው አስፈላጊውን ትብብር በአጭር ቀናት ውስጥ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል አክለውም የተቋሙ ሀላፊ ለሚያደርጉት ድጋፍ እጅጉን አመስግነዋል ፨፨፨፨

ለተገልጋዮች ምቹ አገልግሎት ለመፍጠር አስፈላጊውን ርብርብ እናደርጋለን ፨፨በዛሬው ዕለት ከክልል ጤና ቢሮ Wash ዳይሮክቴሮት ዳይሬክተር ሼክ ኑሩ በአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ከተቋሙ ሀላፊ ...
02/02/2026

ለተገልጋዮች ምቹ አገልግሎት ለመፍጠር አስፈላጊውን ርብርብ እናደርጋለን ፨፨

በዛሬው ዕለት ከክልል ጤና ቢሮ Wash ዳይሮክቴሮት ዳይሬክተር ሼክ ኑሩ በአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ከተቋሙ ሀላፊ አቶ አሊ አደም ጋር በጋራ በመሆን ጉብኝት አድርገዋል አክለውም ዳይሬክተሩ ተቋሙ ላይ በመዘዋወር በተቋሙ በራሱ ተነሳሽነት የሚሰሩ ስራዎችን አድንቀው የ እናቶችና ህፃናት ቀዶ ጥገና ክፍል የሚሆን ተጀምሮ ያላለቀውን መፀዳጃ ቤት እንደሚጨርሱ ቃል በመግባት አመርቂ ውይይት አድርገው አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል ከዚህም ጋር በተያያዘ የአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ክልል ጤና ቢሮ ለተቋሙ የሚያደርገውን ቅርብ ክትትልና ድጋፍ እጅጉን ያመሰግናል ፨፨፨

የተገልጋዩችን እርካታ ሟሟላት ተቋሟዊ ግዴታችን ነው ፨፨፨በዛሬው ዕለት የአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ በቦርዱ የተፈቀደለትን የመድሀኒት ግዢ ከ ኢትዮጵያ መድሀኒት አቅርቦት ኤጀንሲ የ 493,97...
31/01/2026

የተገልጋዩችን እርካታ ሟሟላት ተቋሟዊ ግዴታችን ነው ፨፨፨

በዛሬው ዕለት የአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ በቦርዱ የተፈቀደለትን የመድሀኒት ግዢ ከ ኢትዮጵያ መድሀኒት አቅርቦት ኤጀንሲ የ 493,978.65 መድሀኒት ግዢ አድርጎ ከተማ መ/ድር ቢሮን ጨምሮ ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት ኮሚቴዎች ባሉበት ገቢ አድርጓል ፤ እንደ ተቋም ለማህበረሰቡ የመድኃኒት አቅርቦትን የበለጠ ለሟሟላት ተገቢውን ጥረት እንደሚያደርግ ከወዲሁ እናሳውቃለን ፨፨

 #የአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ቦርድ የ6 ወር የስራ ሪፖርት ግምገማ፨፨፨በዛሬው ዕለት የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የቦርድ አባላቶች በከተማ መስተዳደሩ ቢሮ ( የቦርዱ ሰብሳቢ ) የ 6 ወር...
22/01/2026

#የአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ቦርድ የ6 ወር የስራ ሪፖርት ግምገማ፨፨፨

በዛሬው ዕለት የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የቦርድ አባላቶች በከተማ መስተዳደሩ ቢሮ ( የቦርዱ ሰብሳቢ ) የ 6 ወር ስራ አፈፃፀም ገምግሞ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል በመቀጠለም የ ተቋሙ ሀላፊ አቶ አሊ አደም ባቀረቡት ሪፖርት መሠረት በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሚስተዋሉ መሠረታዊ ችግሮችን ቦርዱ ትኩረት ሰጥቶበት መፍትሄ እንዲሰጥበት ጠይቀዋል እክለውም የከተማው ክቡር ከንቲባ አቶ አብዶ አሊ ተቋሙ ያለበትን መሻሻሎች የበለጠ አጠናክሮ እንዲቀጡልና የተቋሙን ችግሮች ደረጃ በ ደረጃ እንደሚፈቱ ቃል ገብተዋል በመቀጠለም ፤ የከተማው ጤና ፅ/ቤት ሀላፊ ክብርት ወ/ሮ ማሊካ ኢብራሂም ጤና ተቋሙ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶች ከተቋሙ በላይ በመሆናቸው የቦርዱ አባላት በጋራ ተረባርበው የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጥ ፅኑ አቋማቸው
‎ እንደሆነ ገልፀዋል አክለውም ፣የከተማው ፋ/ፅ/ቤት ሀላፊ ክቡር መሀመድ ሁመድ እንደ ተቋም የተጀመሩ ለውጦችንና ጥረቶችን አበረታተው በቀጣይ 3ወር ሪፖርቱ ከዚህ የበለጠ አፈፃፀም እንደሚጠብቁና ያሉትንም ችግሮች ለመፍታት ዝግጁ መሆናቸውንም ገልፀዋል ከዚህ ጋር በተያያዘ የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የቦርድ አባላት ለመድሀኒት ግዢ የሚውል 60000 ሺህ ብር አፅድቀዋል፣ የአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያም ለተቋሙ ክቡር ከንቲባውን ጨምሮ ሌሎች የቦርድ አባላቶችን ጊዜያቸውን ሰውተው ለማህበረሰቡ ጥራት ያለው አገልግሎት እንዲሰጥ ያሳዩትን ቁርጠኝነት ተቋሙ ላቅ ያለምስጋና ያቀርባል፨፨፨፨

ለማህበረሰባችን ትኩረት እንሰጣለን ፨፨፨ #በዛሬው ዕለት በአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ በተቋሙ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ከተቋሙ ማኔጅመንት አባላት ጋር በተቋሙ ሀላፊ አቶ አሊ አደም ቢሮ ...
15/01/2026

ለማህበረሰባችን ትኩረት እንሰጣለን ፨፨፨

#በዛሬው ዕለት በአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ በተቋሙ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ከተቋሙ ማኔጅመንት አባላት ጋር በተቋሙ ሀላፊ አቶ አሊ አደም ቢሮ ሰፊ ውይይት አድርገው የተሻለ አገልግሎት ለመስጠትና ችግሮችን ደረጃ በ ደረጃ በመፍታት ተቋሙን ለማህበረሰቡ ምቹ ለማድረግ ትልቁን ድርሻ በመውሰድ ውይይቱን በተሳካ መልኩ ተደርጓል ፨፨፨

BSC plan ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ሰራተኛን መፍጠር የተቋማት ድርሻ ነው ፨፨፨በዛሬው ዕለት ከ ቀኑ 9 ሰዐት ጀምሮ በአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ለ ሰራተኞች ውጤት ተኮር ሰራተኛና የተቋ...
05/01/2026

BSC plan ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ ሰራተኛን መፍጠር የተቋማት ድርሻ ነው ፨፨፨

በዛሬው ዕለት ከ ቀኑ 9 ሰዐት ጀምሮ በአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ለ ሰራተኞች ውጤት ተኮር ሰራተኛና የተቋሙን ግብና ስትራቴጂ በተጠናከረ መልኩ ለማስቀጠል እንደ ክልል የተጀመረውን (BSC plan implementation ) አጠቃላይ የተቋሙን ሰራተኞች በመሰብሰብ ስልጠናውን ለ3 ተከታታይ ቀናት እንዲከታተሉ የተቋሙ ሀላፊ አቶ አሊ አደም ባሉበት አስጀምረዋል አክለውም አቶ አሊ አደም እንደ ተቋም የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን በጋራ ድክመቶቻችንን እየለየን ጥንካሬያችን ላይ ደሞ ይበለጥኑ እየሰራን ተቋሙን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ የጋራ ርብርብ እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል ፨፨

የአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ውጤት ተኮር አሰራር ( Bsc implementing ) ዝግጅቱን ጨርሶ ለ ስራ ሂደቶች ግንዛቤ የማስጨበጫ መድረክ ፨፨፨  በዛሬው ዕለት በአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ...
02/01/2026

የአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ውጤት ተኮር አሰራር ( Bsc implementing ) ዝግጅቱን ጨርሶ ለ ስራ ሂደቶች ግንዛቤ የማስጨበጫ መድረክ ፨፨፨

በዛሬው ዕለት በአዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ከክልል ጤና ቢሮ በተሰጣቸው አቅጣጫ መሰረት እንደ ክልል የተጀመረውን የመንግስት ተቋማትን ውጤትን መሰረት ያደረገ የአሰራር ስርዓትን እንዲዘረጋ ሚዛናዊ በሆነ ዕይታ አስተሳስሮ ለመምራት ፣ የሚፈለገውን ውጤት ከበጀት ጋር አጣጥሞ ለመተግበር ፣ ስትራቴጂካዊ ግቦችን የመመዘን ሂደትን በማከናወን የውጤት ላይ የተመሰረተ የምዘና ስርዐት ተግባራዊ በማድረግ እንዲሁም ተቋሙ ተልዕኮውንና ግቡን ወደ ፈፃሚ አካላት በማውረድ የሚጠበቀውን ስኬት ለመቀዳጀት አስፈላጊውን ግንዛቤ ለ ተለያዩ የክፍል ስራ ሂደቶች የተቋሙ ሀላፊ አቶ አሊ አደም ግንዛቤ ሰጥተዋል አክለውም የተቋሙ ሀላፊ ስልጠናው ከ ሰኞ ጀምሮ ለሁሉም ባለሙያ የሚሰጥ ሲሆን አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አስገንዝበዋል ፨፨፨

 #እኛ ማህበረሰባችን ውስጥ ነን ፨፨በዛሬው ዕለት የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ባለሙያዎች የቤተሰብ ጤና ቡድን የቤት ለ ቤት ምርመራ በሱባህ ቀበሌ እናቶችም ህፃናትን በማከም ተገቢውን አገል...
30/12/2025

#እኛ ማህበረሰባችን ውስጥ ነን ፨፨

በዛሬው ዕለት የ አዋሽ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ባለሙያዎች የቤተሰብ ጤና ቡድን የቤት ለ ቤት ምርመራ በሱባህ ቀበሌ እናቶችም ህፃናትን በማከም ተገቢውን አገልገሎት በመስጠት ላይ ይገኛል ለማህበረሰባችን አስፈላጊውን ህክምና ቤታቸው በመሄድ ሙያዊ ግዴታችንን እንወጣለን ፨፨

ተቋማችንን ለተገልጋዮች ፅዱ እና ማራኪ ማድረግ የጋራ ግዴታችን ነው ፨፨፨
17/12/2025

ተቋማችንን ለተገልጋዮች ፅዱ እና ማራኪ ማድረግ የጋራ ግዴታችን ነው ፨፨፨

Address

Awash

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Awaash Magaalahe Xiinissok Qaafiyate Fenteeyna posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share