Alamura Primary Hospital , Hawassa

Alamura Primary Hospital , Hawassa Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Alamura Primary Hospital , Hawassa, Medical and health, Awassa.
(1)

የአለም የህሙማን ደህንነት ቀን /World Patient Safety Day/ በሀዋሳ አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል  ተከበረ።****************************************...
18/09/2025

የአለም የህሙማን ደህንነት ቀን /World Patient Safety Day/ በሀዋሳ አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተከበረ።
********************************************
ዛሬ በቀን 8/01/18 ዓም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የአለም የህሙማን ቀን ስለ ህሙማን ደህንነት ግንዛቤ ማስጨበጫ በመስጠት፣ የፅዳት ዘመቻ በማድረግ እንዲሁም የጤና ትምህርት በመስጠት ተከብሯል።

“ደህንነቱን የጠበቀ ክብካቤ ለሁሉም ጨቅላ ህፃናትና ህፃናት” በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ክብረ በአል ላይ የሆስፒታል ማናጅመንት የስራ ክፍል አስተባባሪዎች እና ስታፍ ተሳታፊ ሆነዋል።

ልንከላከላቸው የምንችላቸውን የህክምና ሞቶችን እንዲሁም ጉዳቶችን ማስቀረት ዋነኛ ትኩረታችን ሊሆን እንደሚገባ ያሳሰቡት የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ፣ ህሙማንን ከፍ ሲል ደህንነታቸውን ጠብቆ ማከም፣ ዝቅ ሲልም አለመጉዳት መርሀችን ሊሆን ይገባል ብለዋል።
የበአሉ ተሳታፊዎችም በቀረበው የግንዛቤ ማስጨበጫ ላይ የተለያዩ ሀሳቦችን አንስተው ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን፣ የህሙማንን ደህንነት ጠብቆ አገልግሎት ለመስጠት የገቡትንም ቃል-ኪዳን አድሰዋል።

ዛሬ በቀን 1/01/18 ዓ.ም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና የስራ አስተባባሪዎች ከተረኛ ባለሙያዎች ጋር በዛሬው እለት የአዲስ አመት በአልን በጋራ አክብረዋል።
11/09/2025

ዛሬ በቀን 1/01/18 ዓ.ም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና የስራ አስተባባሪዎች ከተረኛ ባለሙያዎች ጋር በዛሬው እለት የአዲስ አመት በአልን በጋራ አክብረዋል።

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ተገንብቶ ለባለቤቱ ማስተላለፍን ጨምሮ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የተለያዩ ድጋፎችን አደረገ፣*****...
10/09/2025

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ተገንብቶ ለባለቤቱ ማስተላለፍን ጨምሮ ለአቅመ ደካማ ወገኖች የተለያዩ ድጋፎችን አደረገ፣
***************************************
አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ተገንብቶ ለባለቤቱ የማስተላለፍን ጨምሮ እገዛ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች የእህል፣ የምግብ ዘይት ና የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ በመልዕክታቸው፦÷ ሆስፒታሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ እንደሆነ ገልፀው በዚህም ጊዜ በርካታ ሥራዎች መሰራታቸው የሚደነቅ በማለት ዛሬ የተደረገው ማዕድ ማጋራት ብቻ ሳይሆን በጤናው ዘርፍ በትጋት ፣በቁርጠኝነትና በመሰጠት የህይወት መስዋትነትን ጨምሮ ቤተሰባችሁን መስዋዕት በማድረግ ለበረከታችሁት ዓርአያነት ያለው ተግባር ለማበረታታትና እናመሰግናችኋለን ለማለት እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

አዲስ ዓመት በዓል የሚከበርበት፣ ጥልቅ የሆነ ማህበራዊ ትስስሮች የሚጠናከሩበት፤ ከግለሰብ ጀምሮ በቤተሰብ፣ በማህበረሰብ፣ በመንግስትና በተለያዩ ተቋማት ጭምር አዳዲስ ክንውኖች የሚታዩበት ወቅት በመሆኑ ልዩ ትርጉም እንዳለው አውስተው፤ በመልካም ምኞት መግለጫቸው፥ "መጪው አዲስ ዓመት የሰላም፣ የጤና ፣የፍቅር፣ የመተሳሰብ እንዲሆን እመኛለሁ" ብለዋል።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ማራዶና ዘለቀ በበኩላቸው 2017 ዓ/ም እንደሀገር ስኬት የተመዘገበበት ዓመት መሆኑን በማንሳት ሁሉም በተሰማራበት መስክ ለሀገር ብልጽና እሴትን በሚጨምሩ ተግባራትላ ጠንካራ የአብሮነት፣ የመደጋገፍ፣ የመከባበርና የመረዳዳት ዕሴቶቻችን ሊጎለብቱ እንደሚገበቸው ተናግረዋል፡

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ኃላፊ አቶ ዮሴፍ ዩዌ የሆስፒቲሉ MCCቲም ባለሙያዎች በተቋሙ በርካታ የበጎነት ተግባር እንደሚያከናወኑ ገልጸው ፤ አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤት ተገንብቶ ለባለቤቱ የማስተላለፍን ጨምሮ እገዛ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች የእህልና የትምህርት መርጃ ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረግ እጅግ አበረታች ብለውታል ፡፡

በፕሮግራሙ የጤና ቢሮ የማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች፣የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ፣ የሆስፒታሉ ሰራተኞች ፣ የማጅመቶች የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሠራተኞች ፎረምና የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ግምገማ አደረገ*********************************************በመድረኩም በ2017 ...
05/09/2025

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሠራተኞች ፎረምና የ2017 በጀት ዓመት እቅድ ግምገማ አደረገ
*********************************************
በመድረኩም በ2017 በጀት ዓመት የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ ባለሙያዎች፣ የስራ ሂደት፣ የቀድሞ ማኔጅመንት አካላት፣ ድጋፍ ላደረጉ ድርጅቶች፣ የጤና ተቋማትና ለግለሰቦች እውቅና ተሰጥቷል።

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማራዶና ዘለቀ ሆስፒታሉ በቅርብ ጊዜ ቢቋቋምም በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ለውጥ እንዳለው ገልፀው ከተማውን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ከዚህ በላይ መሠራት እንደሚገባም ገልፀዋል።

ከህብረተሰቡ የተሠጠውን የሆስፒታሉ የአገልግሎት ምስክርነት ለማስቀጠል በ2018 በጀት ዓመት በምን አግባብ እሰራለን የሚለውን በመነጋገር ውጤቱን ማስቀጠል እንደሚገባም አቶ ማራዶና ተናግረዋል።

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊና የሆስፒታሉ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጌቱ ማሞ በንግግራቸው በበጀት ዓመቱ ሆስፒታሉ ባጭር ጊዜ ውስጥ አበረታች ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል።

የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ይርዳቸው አናቶ የሆስፒታሉን የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ለማዘመን ከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊ ድጋፍ እያደረገ መቆየቱን ተናግረው ይህም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ የተቀናጀ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዮን ህብረተሰብ ፍላጎት ለማርካት በበጀት አመቱ መጀመሪያ የታቀዱ ስራዎች በስኬት መጠናቀቁን ተናግረዋል።

በ2017 በጀት ዓመት በአፈፃፀም ወቅት የተገኙ ጥንካሬዎችን ለማስቀጠልና በጉድለት የተለዩ ችግሮችን ለቅሞ በ2018 መፍታትና የእርምት እርምጃዎችን በመውስድ የተሻ አፈፃፀም እንሚያስመዘግብ አቶ ዮሴፍ ተናግረዋል።

በጀት ዓመት በሆስፒታሉ የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የማበረታቻ ሽልማት እንደተደረገላቸው አቶ ዮሴፍ ገልፀዋል።

የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም የሆስፒታሉ ሚዲካል ዳሬክተር ዶ/ር ሄኖክ ኢሳያስ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጓበታል።

የመድረኩ ተሣታፊዎች በበኩላቸው በተቋሙ የተለያዩ አገልግሎት ዘርፎች ላይ በርካታ ቁጥር ላላቸው ማህብረሰብ ክፍሎች አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ገልፀው ከዚህ በተሻለ መልኩ መሰራት እንዳለበት ሀሳብ ሰጥተዋል።

በመድረኩም ተሸላሚዎች የሰረተፍኬት፣ የማዳልያ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የዋንጫና የሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆነ።**************************የ አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በ2017 ዓም በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ...
02/09/2025

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የዋንጫና የሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆነ።
**************************
የ አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በ2017 ዓም በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ስር ካሉ ሆስፒታሎች ጋር ተወዳድሮ የላቀ አፈፃፀም በማስመዝገብ እንዲሁም ጥራት ያለውና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የዋንጫና የሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆኗል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ባዘጋጀው 16ተኛው የፐብሊክ ሰርቫንት አመታዊ የዕውቅናና የሽልማት መርሀግብር ላይ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ መኩሪያ መርሻዬና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

የአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንቲቲውት የእውቅና ሰርተፍኬት ተበረከተለት።***************************************የአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ...
30/08/2025

የአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በክልሉ ህብረተሰብ ጤና ኢንቲቲውት የእውቅና ሰርተፍኬት ተበረከተለት።
***************************************
የአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በላቦራቶሪ አገልግሎት የጥራት ደረጃ መለኪያ ተመዝኖ የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ እና ጥራት ያለው አገልግሎት በመስጠት የዕውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶለታል።
የዕውቅና ሰርተፊኬቱ የሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባዘጋጀው የ2017 ዓም የላቦራቶሪ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ላይ ሲበረከት የኢትዮዽያ ህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲቲውት ምክትል ዳሬክተር ዶ/ር ሳሮ አብደላ፣ የሲዳማ ህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትውት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዳመነ ደባልቄ እንዲሁም ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

የቡሹሎ እናቶችና ህፃናት ህክምና ማዕከል ማናጅመንት የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጎበኙ**************************************በቀን 22/12/17 ዓም የቡሹሎ እ...
29/08/2025

የቡሹሎ እናቶችና ህፃናት ህክምና ማዕከል ማናጅመንት የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ጎበኙ
**************************************
በቀን 22/12/17 ዓም የቡሹሎ እናቶችና ህፃናት ህክምና ማዕከል ማናጅመንት የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የእናቶችና ህፃናት ህክምና አገልግሎትን ጎብኝተዋል። የሆስፒታሉን የጨቅላ ህፃናት ህክምና አገልግሎት ለማስጀመር ከፍተኛ ድጋፍን ያበረቱት የማዕከሉ ማናጅመንት በጉብኝቱ ወቅት ባዩት ነገር መደሰታቸውን ገልፀዋል። በዕለቱም የጨቅላ ህፃናት ህክምና ከጅማሮ አሁን እስከደረሰበት ደረጃ የነበረው አፈፃፀም የቀረበ ሲሆን በቀጣይም በትብብር በጋራ በሚሰራበት ጉዳይ ውይይት ተካሂዷል።

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አንዲት እናት ሶስት መንታ ልጆችን በሰላም ተገላገለች።*******************************በቀን 21/12/17 ዓ.ም  ምሽት  8:20 ላይ አ...
28/08/2025

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አንዲት እናት ሶስት መንታ ልጆችን በሰላም ተገላገለች።
*******************************
በቀን 21/12/17 ዓ.ም ምሽት 8:20 ላይ አንዲት እናት ሶስት መንታ ልጆችን በሰላም ተገላግላለች ።
ለተቋሙ የመጀመሪያው በሆነው ወሊድ ሶስቱም ህፃናት ሁለት ኪሎግራም ሲመዝኑ አሁን ላይ ልጆችም እናትም በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛሉ።

‘በጎ አድራጎት ለጤናማ ማህበረሰብ’ በሚል መሪ ቃል አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እያከውናቸው ከሚገኙ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች አካል የሆነ  ዛሬ በቀን 16/12/17 ዓ.ም በር...
22/08/2025

‘በጎ አድራጎት ለጤናማ ማህበረሰብ’ በሚል መሪ ቃል አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እያከውናቸው ከሚገኙ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች አካል የሆነ ዛሬ በቀን 16/12/17 ዓ.ም በርኆቦት የበጎ አድራጎት ድርጅት በመገኘት የህክምናና የቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል። በሆስፒታሉ የህፃናት ህክምና ስፔሻሊስት ሀኪም በተመራው በጎ አድራጎት፣ የዕድገት ክትትል፣ ስር የሰደደ ሕመም፣የአጥንት ችግር ፣ በአይረን እጥረት የሚከሰት የደም ማነስ ፣አካል ጉዳተኝነት እንዲሁም ከውልደት የመጣ የአፈጣጠር ችግር የምርመራና የህክምና አገልግሎት በተቋሙ ተጠልለው ላሉ ህፃናት የተደረገላቸው ሲሆን የልብስ እንዲሁም የንህጽህና መጠበቂያ ሳሙና ድጋፍም ተበርክቶላቸዋል።

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እያከውናቸው ከሚገኙ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች አካል የሆነ ‘በጎ አድራጎት ለጤናማ ማህበረሰብ’ በሚል መሪ ቃል ዛሬ በቀን 08/12/17 ዓ.ም የደም...
14/08/2025

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እያከውናቸው ከሚገኙ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች አካል የሆነ ‘በጎ አድራጎት ለጤናማ ማህበረሰብ’ በሚል መሪ ቃል ዛሬ በቀን 08/12/17 ዓ.ም የደም ግፊት፤ የስኳር የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር፤ የHIV AIDS፤ የቲቢ እንዲሁም የአይን ምርመራ ዘመቻ ተጀምሯል። በታቦር ክፍለከተማ ፋራ ቀበሌ አዲሱ መናሀሪያ አካባቢ በተጀመረውና ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው ዘመቻ በርካታ የማህበረሰብ ከፍል አገልግሎት ያገኘ ሲሆን መርሀግብሩም በተለያዩ አዝናኝ ዝግጅቶች ታጅቦ ውሏል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባርና ፅዱ፣ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር ኢኒሼቲቭ አካል የሆነውን  የፅዳት ዘመቻ በቀን 0...
09/08/2025

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባርና ፅዱ፣ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር ኢኒሼቲቭ አካል የሆነውን የፅዳት ዘመቻ በቀን 03/12/17 ዓ.ም በሆስፒታሉ ቅጥር ጊቢ እንዲሁም በሆስፒታሉ ዙሪያ ባሉ መንደሮች ህብረተሰቡን በማሳተፍ ከጠዋት 12:00 ጀምሮ በጋራ አካሂደዋል።

በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ የጤናው ዘርፍ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በይፋ ተጀመረ።የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሀምሌ 17/2017 ዓ.ምበሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢ...
24/07/2025

በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ የጤናው ዘርፍ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በይፋ ተጀመረ።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሀምሌ 17/2017 ዓ.ም

በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ የጤናው ዘርፍ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት "በጎ አድራጎት ለጤናማ ማህበረሰብ "በሚል መሪ ቃል በዛሬው ዕለት በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተጀምሯል።

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሀ-ግብሩን በይፋ ያስጀመሩት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ ክቡር አቶ ባጢሶ ዌዲሶ በመልዕክታቸው የጤና ዘርፍ የበጎ አድራጎት ተግባር በጊዜ የማይገደብ ፣ቀን ሌሊት ፣ክረምት በጋ የማይል፣ ሁሌም በበጎነትና በርህራሄ የሚተገበር ፣ መልካምነት ከጤና ባለሙያው ስብዕና የተቀዳ እስኪመስል በፅናት የሚያገለግሉበት የተከበረ የሙያ ዘርፍ መሆኑን ገልፀዋል።

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ወቅታዊ ሃላፊነት ብቻ ሳይሆን ሁሌም በመተግበር ሀገራችንን ወደ ላቀ ብልፅግና ለማሸጋገር የጀመርነውን ጉዞ በደስታ የምናስቀጥለው ትልቅ አሻራ መሆኑን ክቡር አማካሪው አክለው ተናግረዋል ።

የጤና ተቋማትን ውብና ማራኪ ለማድረግ ፣አገልግሎቱም ንፅህናውን የጠበቀ እንዲሆን በማስቻል እንዲሁም ለጤና መድሀኒትነት የሚጠቅሙ እፅዋትን ጭምር በመትከል ለሀገር ኩራት የሚሆኑ ውጤቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው ስራውን ተቋማዊ በማድረግና አሰራሩ ስርዓት ይዞ እንዲቀጥ በማድረግ እንደ ሀገር የተጀመሩ በርካታ ተስፋ ሰጪ ተግባራትን ማስቀጠል እንደሚገባ አቶ ባጢሶ በማሳሰብ መርሀ-ግብሩን በይፋ አስጀምረዋል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ በበኩላቸው የጤና አገልግሎት የህይወት ዋጋ የሚከፈልበት የሙያ ዘርፍ መሆኑን ጠቅሰው የጤና ባለሙያው ከሚሰጠው ሙያዊ አገልግሎት በተጨማሪ ካለዉ ላይ ቀንሶ ለማህበረሰቡ ድጋፍ የሚያደርግ የመልካም ስብዕና ባለቤት መሆኑን ተናግረዋል።

ሀላፊዋ አክለውም የዘንድሮው የጤናው ዘርፍ የክረምት በጎ አድራጎት መርሃ ግብር ከተለመደው ተግባራት በተጨማሪ የጤና ተቋማትን ምቹ እና ፅዱ የማድረግ ስራዎችንም እንደሚጨምር ገልፀው ነጻ የጤና ምርመራና ህክምና አገልግሎት ፣የህክምና ቁሳቁስ ጥገና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ የጤና ተቋማት እድሳት፣ የደም መለገስ፣የህክምና መሳሪያዎች/ መድሃኒቶች እና የመሳሰሉትን መለገስ ፣የወባ መከላከል ስራን ማገዝ ይህም በአጎበር አጠቃቀምና በአካባቢ ጥበቃ ስራ ላይ መሳተፍና መተጋገዝ ፤ በአጠቃላይ ፅዱ የጤና ተቋማት ፣ፅዱ ማህበረሰብ፣ ፅዱ ሲዳማን የማየት ራዕይ ዕውን እንዲሆን አመራሩ፣የጤና ባለሙያው እንዲሁም አጠቃላይ ማህበረሰቡ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ በመሳተፍ የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ መሳተፍ በሰማይም በምድርም የሚያስመሰግን የበረከት ስራ በመሆኑ ለአቅመ ደካማ የህብረተሰብ ክፍሎች የቤት እድሳት የተደረገ ሲሆን፣የደም መለገስና የአረንጓዴ አሻራ አካል የሆነው የችግኝ ተከላ መርሀ ግብርም ተከናውኗል።

በመርሀ-ግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የስራ ሀላፊዎች፣ የጤና ሚኒስቴር የስራ ሀላፊዎችና ባለሙያዎች ፣ከሀገረ አሜሪካ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለመስጠት የመጡ አካላት፣ የታቦር ክፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ፣ የከተማ አስተዳሩ የስራ ሀላፊዎች ፣ የሆስፒታሉ የስራ ሀላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም የሀዋሳን ህዝብ ወክለው የተገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።

# "በጎ አድራጎት ለጤናማ ማህበረሰብ ! "

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ

Address

Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alamura Primary Hospital , Hawassa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram