Alamura Primary Hospital , Hawassa

Alamura Primary Hospital , Hawassa Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Alamura Primary Hospital , Hawassa, Medical and health, Awassa.

ለመላው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በሙሉ፣ እንኳን ለከተራ እና ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በአል በሰላም አደረሳችሁ!
18/01/2026

ለመላው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በሙሉ፣ እንኳን ለከተራ እና ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በአል በሰላም አደረሳችሁ!

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የስድስት ወር የበሽታ መከላከል አፈፃፀም ተገመገመ።**********************************ዛሬ በቀን 8/05/18 ዓም የሀዋሳ ከተማ አስተዳ...
16/01/2026

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የስድስት ወር የበሽታ መከላከል አፈፃፀም ተገመገመ።
**********************************
ዛሬ በቀን 8/05/18 ዓም የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ የድጋፍ ቡድን በተገኘበት የበሽታ መከላከል የስድስት ወር አፈፃፀም ተገምግሟል።
በዕለቱ የበሽታ መከላከልና የቤተሰብ ጤና ቡድን የስድስት ወር ሪፖርት፣ የሞዴል ቀበሌ validation ሪፖርት ግብረመልስ እና የመቶ ቀን እቅድ አፈፃፀም ሪፖርቶች ቀርበዋል።
በቀረቡት ሪፖርቶች ዙሪያ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከተሳታፊዎች ጥያቄና አስተያየቶች ተነስተው በሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ አማካኝነት ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
በመጨረሻም በመቶ ቀን እቅድ ውስጥ የተካተተው ሞዴል ቀበሌ የመፍጠር ስራ እስከ ጥር 30 እንዲጠናቀቅ የድርጊት መርሀግብር የወጣ ሲሆን ተፈፃሚ እንዲሆንም የስራ መመሪያ ተላልፏል።

በአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሁለተኛ ሩብ አመት የEPAQ ሁለተኛ ዙር ድጋፋዊ ክትትል እና  የክላስተር ስብሰባ ተካሄደ።******አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በEPAQ mentor...
16/01/2026

በአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሁለተኛ ሩብ አመት የEPAQ ሁለተኛ ዙር ድጋፋዊ ክትትል እና የክላስተር ስብሰባ ተካሄደ።
******
አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በEPAQ mentorship ድጋፍ ከሚያደርግለት የቡልቻ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ጋር በጋራ የሁለተኛ ሩብ አመት ክላስተር ስብሰባ አካሂዷል።
በዕለቱም የ2018 ሁለተኛ ሩብ አመት EPAQ ሁለተኛ ዙር ድጋፋዊ ክትትል ግብረመልስ ሪፖርት፣ የላይዘን ፎረምና የፀረ ተዋሲያን መድሀኒቶች በጀርሞች መለመድ ሳምንትን በተመለከተ“ አሁን እንተግብር፣ ዛሬን እንጠብቅ፣ የወደፊታችንን እናረጋግጥ” በሚል መሪ ቃል የግንዛቤ ማስጨበጫ ተካሂዷል።
በቀረቡት ሪፖርቶች እና ግንዛቤ ማስጨበጫ ዙሪያ ሰፋ ያለ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስያየቶች ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።

‎“ፈጠራና ዘላቂ ፋይናንስ ለጤናማ እናትነት” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ መርሃ ግብሮች ከሚከበረው የጤናማ እናትነት ወር አንድ አካል የሆነው የነፍሰጡር እናቶች ፎረም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ...
13/01/2026

‎“ፈጠራና ዘላቂ ፋይናንስ ለጤናማ እናትነት” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ መርሃ ግብሮች ከሚከበረው የጤናማ እናትነት ወር አንድ አካል የሆነው የነፍሰጡር እናቶች ፎረም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተከናወነ።
****************************
ዛሬ በቀን 05/05/18 ዓም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል “ፈጠራና ዘላቂ ፋይናንስ ለጤናማ እናትነት በሚል መሪ ቃል የነፍሰጡር እናቶች ፎረም ተከናውኗል።
በእለቱም ሁሉም እናቶች ጤናማ የእርግዝና፤ የወሊድና የድህረ-ወሊድ ጊዜ እንዲያሳልፉ አስፈላጊውን የጤና መረጃ እንዲኖራቸው የሚያግዝ የጤና ትምህርት ተሰጥቷል።
ከ200 በላይ ነፍሰጡር እናቶች በተሳተፉበት ፎረም ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከተሳታፊ እናቶችም ለተነሱ ጥያቄዎች ከመድረኩ መልስ ተሰጥቶባቸዋል።

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የመኪና ድጋፍ ተደረገለት****************************************የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በቀን 2/05/18 ዓም ከሀዋሳ ...
10/01/2026

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የመኪና ድጋፍ ተደረገለት
****************************************
የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በቀን 2/05/18 ዓም ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ለሆስፒታሉ ስራ የሚያገለግል የሀርድ ቶፕ መኪና ድጋፍ ተበርክቶለታል።
በዕለቱ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ሀላፊ አቶ ይርዳቸው አናቶ ለአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ ቁልፍ አስረክበዋል።
የመኪና ድጋፉን ላበረከቱልን የጤና መምሪያ ሀላፊ አቶ ይርዳቸው አናቶና ለመምሪያው ማናጅመንት በሆስፒታሉ ማህበረሰብ ስም ከልብ እናመሰግናለን።

ዛሬ በቀን 29/04/18 ዓ.ም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና የስራ አስተባባሪዎች ከተረኛ ባለሙያዎች ጋር በዛሬው እለት የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት መታሰቢያ በአል የሆነውን...
07/01/2026

ዛሬ በቀን 29/04/18 ዓ.ም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና የስራ አስተባባሪዎች ከተረኛ ባለሙያዎች ጋር በዛሬው እለት የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት መታሰቢያ በአል የሆነውን የገና በአልን በጋራ አክብረዋል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች የ 2018 ዓ.ም የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በአልን ከአቅመደካሞች ጋር አከበሩ።*********************************...
06/01/2026

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች የ 2018 ዓ.ም የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በአልን ከአቅመደካሞች ጋር አከበሩ።
*****************************************
በቀን 28/04/18 ዓም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በአላሙራ ካችመንት ስር ከሚገኙ ቀበሌያት ከተለዩ አቅመደካሞች ጋር የገና በአልን አክብረዋል።
በ MCC ኮሚቴ አስተባባሪነት ከስታፍ በተሰበሰበ መዋጮ በተዘጋጀው በአል ላይ ከ 50 በላይ ለሚሆኑ በቀበሌያችን የድሀድሀ ተብለው ለተለዩ አቅመደካሞች የዘይት ዱቄት እንዲሁም የሳሙና ድጋፍ ተደርጎላቸዋል።
የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ዮሴፍ ዮዌ በዚህ መልካም ተግባር ላይ ከወር ደመወዛቸው መዋጮ በማድረግ ለተሳተፉት የሆስፒታሉ ስታፍ እንዲሁም ዝግጅቱን በማቀናጀት የተሳካ እንዲሆን ላደረጉት ለMCC ኮሚቴ አባላት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን እንዲ ያለው በጎ ተግባር በቀጣይነትም እንደሚካሄድ ቃል ገብተዋል።
በመጨረሻም ድጋፍ የተደረገላቸው አካላት ደስታቸውን በመግለፅ የሆስፒታሉንም ሰራተኞች አመስግነዋል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ፅዱ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር አካል የሆነውና የ100 ቀን እቅድ ውስጥ የተካተተውን ወርሀዊ የፅዳት ዘመቻ በቀን 25/04/...
03/01/2026

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ፅዱ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር አካል የሆነውና የ100 ቀን እቅድ ውስጥ የተካተተውን ወርሀዊ የፅዳት ዘመቻ በቀን 25/04/18 ዓ.ም በሆስፒታሉ ቅጥር ጊቢ እና በሆስፒታል ዙሪያ ባሉት መንደሮች ከጠዋት 12:00 ጀምሮ አካሂደዋል።

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የመጀመሪያ ግማሽ አመት የእውቀት፤ ክህሎትና አተገባበር ምዘና (KAP Assessment ) ፈተና ተሰጠ።********************************...
29/12/2025

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የመጀመሪያ ግማሽ አመት የእውቀት፤ ክህሎትና አተገባበር ምዘና (KAP Assessment ) ፈተና ተሰጠ።
********************************
በነርሲንግና ሚድዋይፈሪ ዳይሬክቶሬት አማካኝነት የመጀመሪያ መንፈቅ አመት የእውቀት፤ ክህሎትና አተገባበር ምዘና (KAP Assessment ) ፈተና በሆስፒታሉ ቅጥር ጊቢ ተሰጥቷል።
ይህ አይነቱ ፈተና ሆስፒታሉ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ለሶስተኛ ጊዜ የተሰጠ ሲሆን በዚኛው ዙር 52 ነርሶችና 19 ሚድዋይፈሪ ነርሶች ተሳታፊ ሆነዋል።
ተፈታኝ ባለሙያዎች ፈተናው ያሉበትን ደረጃ ለማወቅ የረዳቸው መሆኑን ገልፀው፤ ክፍተት በሚታይበት ቦታ ላይ ዳይሬክቶሬቱ ባዘጋጀው የእውቀትና ክህሎት ማሳደጊያ ስርአት ውስጥ ተካተው ቀጣይነት ያለው ለውጥ ለማምጣት እራሳቸውን ማዘጋጀታቸውን ገልፀዋል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል  በቀጣይ በጤና ተቋሙ በሚፈፀሙ የ100 ቀናት ዕቅድ  ላይ ውይይት አደረገ ።****************************************በቀን 20/04...
29/12/2025

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በቀጣይ በጤና ተቋሙ በሚፈፀሙ የ100 ቀናት ዕቅድ ላይ ውይይት አደረገ ።
****************************************

በቀን 20/04/18 ዓም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በጤና ተቋሙ በሚፈፀሙ የ100 ቀናት ዕቅድ ላይ ውይይት አካሂዷል።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የጤና ልማት እቅድ እና ኢኮኖሚ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አክሊሉ ዮሀንስ፣ በጤና ሴክተር ለማሳካት የተያዘውን እቅድ እውን ለማድረግ ተግባራትን በመፍጠር፣ በመፍጠን እና በመመዝለል መርህ መቃኘት አስፈላጊ እንደሆነ ጠቅሰው የ 100 ቀን ዕቅዱ በዋናነትም የትራንስፎርሜሽን ግብ ስራዎችን ማጠናከር፣ የቤተሰብ ብልፅግና ፓኬጆችን እና የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤን ማጠናከር፣ ለበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ተግባራት ትኩረት በመስጠት ፣የእናቶችና ህጻናት ጤናን ማሻሻልና የስርዓተ ምግብ አገልግሎትን ማጠናከር፣ የጤና አገልግሎት አሰጣጡን ማዘመን፣ የጤናና ጤና ነክ ቁጥጥር ዘርፉን ማሻሻል፣በሴክተሩ የዘመነ መረጃን በተገቢው መሰነድና መጠቀምን እንደ ምሰሶ የሚቀመጡ መሆናቸውን አክለው ገልፀዋል።

የሆስፒታሉ የ100 ቀን እቅድ በሆስፒታሉ ልማት ዕቅድ የቀረበ ሲሆን የእለቱ የክብር እንግዳ አቶ አክሊሉ ዮሀንስና የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ በቀረበ ሪፖርት ዙሪያ የሚደረገውን ውይይት መድረክ በጋራ መርተውታል። ከተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን ከመድረኩ ምላሽ ተሰቶባቸዋል።

እንኳን ደስ አለን/አላችሁ!🎉🎉🎉አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በሲዳማ ክልል ጤናና ጤና ነክ ግብአት ቁጥጥር ባለሰልጣን በተደረገ ምዘና ከፍተኛ ውጤት አስመዘገበ!🎉***************...
27/12/2025

እንኳን ደስ አለን/አላችሁ!🎉🎉🎉
አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በሲዳማ ክልል ጤናና ጤና ነክ ግብአት ቁጥጥር ባለሰልጣን በተደረገ ምዘና ከፍተኛ ውጤት አስመዘገበ!🎉
*********************************
በESA/FDA checklist መሰረት በአራቱ Pዎች (Practice፣ Premise፣ Product እና Professional ) በሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የምዘና ቡድን በተደረገ አሰሳ 86% በማምጣት በክልል ደረጃ ከፍተኛ የተባለ ውጤትን አስመዝግቧል። በሆስፒታል ደረጃ ከተደራጀ አጭር ጊዜ የሆነው ተቋሙ፣ በጠንካራ አደረጃጀት እየተመራ በፍጥነት ሪፎርሞችን በመተግበርና የታለመለትን ግብ ለመድረስ ፈጠራን በማከል እጅግ አስደናቂ ለውጥን አሳይቷል። ይህ ውጤት እንዲመጣ ከፍተኛ አስተዋፆ ያበረከታችሁ የሆስፒታላችን ማናጅመንት፣ የክፍልና ስራ ሂደት አስተባባሪዎች ፣የጥራት ቁጥጥር ክፍል፣ የሲዳማ ክልል ጤናና ጤና ነክ ግብአት ቁጥጥር ባለስልጣን እንዲሁም መላው ሰራተኞቻችን ይህ አፈፃፀም በጋራ የመተባበር ውጤት ነውና ላቅ ያለ ምስጋና ይገባችኋል።

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በሁለተኛ ሩብ አመት የደም ልገሳ መርሀግብር ከፍተኛ ዩኒት ደም ሰበሰበ፡፡*****************ከቀን 13-14/04/18 ዓም ለሁለት ተከታታይ ቀናት በ...
23/12/2025

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በሁለተኛ ሩብ አመት የደም ልገሳ መርሀግብር ከፍተኛ ዩኒት ደም ሰበሰበ፡፡
*****************
ከቀን 13-14/04/18 ዓም ለሁለት ተከታታይ ቀናት በተካሄደ የደም ልገሳ መርሀግብር ለተቋሙ ሪከርድ የሆነ 112 ዩኒት ደም መሰብሰብ ተችሏል። በMCC ኮሚቴ አስተባባሪነት በተካሄደው የበጎ ፈቃደኞች ደም ልገሳ የሆስፒታሉ ማናጅመንት እንዲሁም ሰራተኞች በስፋት ተሳትፈዋል።
በዚህ በጎ አድራጎት ተግባር በማስተባበር የተሳተፋችሁ የሆስፒታሉ ማናጅመንት፣ MCC committee እና QIT team እንዲሁም ውድ የሆነውን ስጦታ ላበረከታችሁ የሆስፒታላችን ሰራተኞችና ተገልጋዮች ምስጋና ይገባችኋል።
ደም እንለግስ ህይወትን እንታደግ!

Address

Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alamura Primary Hospital , Hawassa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram