Alamura Primary Hospital , Hawassa

Alamura Primary Hospital , Hawassa Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Alamura Primary Hospital , Hawassa, Medical and health, Awassa.

ዛሬ በቀን 04/08/18 ዓ.ም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና የስራ አስተባባሪዎች ከተረኛ ባለሙያዎች ጋር በዛሬው እለት የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ መታሰቢያ  የሆነውን የ...
12/04/2026

ዛሬ በቀን 04/08/18 ዓ.ም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና የስራ አስተባባሪዎች ከተረኛ ባለሙያዎች ጋር በዛሬው እለት የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ መታሰቢያ የሆነውን የፋሲካ በአልን በጋራ አክብረዋል።

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለትና የትንሳኤ በአል በሰላም አደረሰን/አደረሳችሁ!
11/04/2026

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለትና የትንሳኤ በአል በሰላም አደረሰን/አደረሳችሁ!

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች የ 2018 ዓ.ም የ ትንሳኤ በአልን ከአቅመደካሞች ጋር አከበሩ።****************************************በቀን...
11/04/2026

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች የ 2018 ዓ.ም የ ትንሳኤ በአልን ከአቅመደካሞች ጋር አከበሩ።
****************************************
በቀን 03/08/18 የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ከአቅመደካሞች ጋር የትንሳኤ በአልን አክብረዋል።
በ MCC ኮሚቴ አስተባባሪነት ከስታፍ በተሰበሰበ መዋጮ በተዘጋጀው በአል ላይ ከ 50 በላይ ለሚሆኑ በቀበሌያችን የድሀድሀ ተብለው ለተለዩ አቅመደካሞች የዘይትና ዱቄት ድጋፍ ተደርጓል።
በዕለቱም የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ዮሴፍ ዮዌ በዚህ መልካም ተግባር ላይ ከወር ደመወዛቸው መዋጮ በማድረግ ለተሳተፉት የሆስፒታሉ ስታፍ እንዲሁም ዝግጅቱን በማቀናጀት የተሳካ እንዲሆን ላደረጉት ለMCC ኮሚቴ አባላት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን እንዲ ያለው በጎ ተግባር በቀጣይነትም እንደሚካሄድ ቃል ገብተዋል።
በመጨረሻም ድጋፍ የተደረገላቸው አካላት ደስታቸውን በመግለፅ የሆስፒታሉንም ሰራተኞች አመስግነዋል።

የሲዳማ ብሄር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው የፍቼ ጫምባላላ በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተከበረ።*****************************************ዛሬ በቀን 07/07/...
16/03/2026

የሲዳማ ብሄር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው የፍቼ ጫምባላላ በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተከበረ።
*****************************************
ዛሬ በቀን 07/07/18 ዓም የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ የፊቼ ጫምባላላ በዓል በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቅጥር ጊቢ ከአካባቢ ማህበረሰብ፣ ከሀገር ሽማግሌ እንዲሁም ከሆስፒታሉ ማናጅመንትና ሰራተኞች ጋር በጋራ በድምቀት ተከብሯል።
በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት በጀመረው ዝግጅት ፣የሲዳማ ብሄር ባህል ፣ ወግ እንዲሁም ትውፊትን የሚያወሱ ዝግጅቶች የተሰናዱ ሲሆን የተለያዩ አዝናኝ ፕሮግራሞችም ለታዳሚያን ቀርበዋል።
በዕለቱ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ፣ ፍቼ ጫምባላላ የሰላምና የእርቅ በአል መሆኑን አውስተው፣ ያለፈ ቂምና ጥላቻን አስወግደን ወደአዲሱ አመት መሻገር እንደሚገባ በንግግራቸው አፀንኦት ሰጥተዋል።
በመጨረሻም የሲዳማ ብሄር ባህላዊ ምግብ ቀርቦ በጋራ ማዕድ ተቋድሰዋል።

Hawalle Sidaamu Daga Diru sooro Fichee Cambalaallate ayyanira keeruni iillishinke!

እንኳን ለሲዳማ ብሔር የዘመን መለዋጫ ፍቼ ጫምባላላ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ !

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች የፍቼ ጫምባላላ በአልን ምክኒያት በማድረግ ፅዱ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር አካል የሆነውን የፅዳት ዘመቻ በቀን 05/07/18...
14/03/2026

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች የፍቼ ጫምባላላ በአልን ምክኒያት በማድረግ ፅዱ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር አካል የሆነውን የፅዳት ዘመቻ በቀን 05/07/18 ዓ.ም በሆስፒታሉ ቅጥር ጊቢ እና በሆስፒታል ዙሪያ ባሉት መንደሮች ከጠዋት 12:00 ጀምሮ በጋራ አካሂደዋል።
በዘመቻው ላይ ተሳታፊ የሆናችሁ የሆስፒታሉ ማናጅመንትና ሰራተኞች ምስጋና ይገባችኋል።

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ6 ወር አፈፃፀምና የሁለተኛ ኳርተር የስታፍ ፎረም ተካሄደ።***********************************ዛሬ በቀን 25/06/18 ዓም በአላሙራ...
04/03/2026

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ6 ወር አፈፃፀምና የሁለተኛ ኳርተር የስታፍ ፎረም ተካሄደ።
***********************************
ዛሬ በቀን 25/06/18 ዓም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ6 ወር አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ እና የሁለተኛ ኳርተር ስታፍ ፎረም ተካሄዷል። በዕለቱ የ6 ወር አፈፃፀም ሪፖርት፣ Hospital accreditation baseline assessment እና ፅዱ Initiative baseline assessment ሪፖርት ቀርቧል። በቀረበው ሪፖርት ዙሪያ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከተሰብሳቢው ለተነሳው አስተያየትና ጥያቄዎች ከመድረኩ መልስ ተሰጥቶባቸዋል። በመጨረሻም ከተሳታፊዎች የተጠቆሙ የስታፍ ተወካይ እጬዎች ለምርጫ የቀረቡ ሲሆን አብላጫውን ድምፅ ያገኘው ግለሰብ የስታፍ ተወካይ ሆኖ ተመርጧል።

በሲዳማ ክልል የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከል በተደረገ ጥረት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ተካሄደ።*********************************...
28/02/2026

በሲዳማ ክልል የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከል በተደረገ ጥረት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ተካሄደ።
***********************************
ዛሬ በቀን 21/06/18 ዓም በሲዳማ ክልል የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከል በተደረገ ጥረት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ተካሂዷል።

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ በሀገሪቱ የተዘረጋው ጠንካራ የጤና ሥርአት በተለይ ለድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም መገንባት አስችሏል።

ለአብነትም የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በተደመረና በተባበረ አቅም ለመቆጣጠር በተደረገ ጥረት ስኬታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ነው የገለጹት።

በሽታውን ለመቆጣጠር በጂንካና በሃዋሳ ከተሞች የላቦራቶሪ ማዕከል በማቋቋም የመርመር አቅምን በማሳደግና ባለሙያዎችን በማሰልጠን በቅንጅት በተሰሩ ሥራዎች ወረርሽኙን መቆጣጠር ተችሏል ብለዋል፡፡

የአላሙራ መ/ደ/ሆስፒታል የጨቅላ ህፃናት ፅኑ ህክምና ክፍል የተመሰረተበትን አንደኛ አመት አከበረ።***********************************ዛሬ በቀን 17/06/18 ዓም የአላሙ...
24/02/2026

የአላሙራ መ/ደ/ሆስፒታል የጨቅላ ህፃናት ፅኑ ህክምና ክፍል የተመሰረተበትን አንደኛ አመት አከበረ።
***********************************
ዛሬ በቀን 17/06/18 ዓም የአላሙራ መ/ደ/ሆስፒታል ፅኑ ህክምና ክፍል የተመሰረተበትን አንደኛ አመት በተለያየ ሁነቶች አክብሯል።
በዕለቱም የጨቅላ ህፃናት ህክምና ከምስረታው አሁን እስከደረሰበት ጊዜ ያለው አጠቃላይ ጉዞን የሚዳስስ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን የፓናል ውይይትም ተኳሂዷል።በተጨማሪም በክፍሉ ጨቅላ ህፃናቶቻቸው በህክምና የተረዱና ከህመም ያገገሙላቸው ወላጆች ስለአገልግሎቱ አስተያየት የሰጡ ሲሆን ሆስፒታሉንም አመስግነዋል።
በመጨረሻም ለክፍሉ መደራጀት ከፍተኛ አስተዋዕፆ ላበረከቱት ለዶ/ር ህሊና ሲሳይ (Neonatology Fellow) የምስጋና ስጦታ ተበርክቷል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በ65 ኛው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ምስረታ ክብረበአል ላይ ተሳታፊ ሆኑ***********************************ዛሬ በቀን 15/...
22/02/2026

የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በ65 ኛው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ምስረታ ክብረበአል ላይ ተሳታፊ ሆኑ
***********************************
ዛሬ በቀን 15/06/17 ዓም የአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች የኢፌድሪ መከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ተኛ አመት አስመልክቶ በተዘጋጀ የምስረታ በዓል ላይ ተሳታፊ ሆነዋል። በእለቱም “ የልዩ ዘመቻዎች እዝ የላቀ ጀግንነት፣ ፅናትና ፍጥነት ከትክክለኛነት ጋር መለያው ነው”፣ “የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የኢትዮዽያ የባህር በር ፍላጎት ታሪካዊ ባለቤትነታችንን የሚያረጋግጥ ነው” የሚልና ሌሎች መፈክሮች በሆስፒታሉ ሰራተኞች ተደምጧል። በክብረ በዓሉ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስቴርና የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶ/ር ዐብይ አህመድን ጨምሮ በርካታ የፌደራል፣ የመከላከያ፣የክልል እንዲሁም የከተማ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በ65 ኛው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ምስረታ ክብረበአል በተዘጋጀ የጎዳና ላይ ሩጫ ተሳታፊ ሆኑ*******************************...
14/02/2026

የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በ65 ኛው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ምስረታ ክብረበአል በተዘጋጀ የጎዳና ላይ ሩጫ ተሳታፊ ሆኑ
***********************************
ዛሬ በቀን 07/06/17 ዓም የአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች የኢፌድሪ መከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ተኛ አመት በአልን አስመልክቶ በተዘጋጀ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ተሳታፊ ሆነዋል። የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ፣ የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ዋና አዛዥ ሌትናል ጀነራል ሹማ አብደታ እና ሌሎች የሀዋሳ ከተማ እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ የሁለተኛ ሩብ አመት ስብሰባ አካሄደ።********************************‎የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል ስራ አመራር ቦ...
30/01/2026

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ የሁለተኛ ሩብ አመት ስብሰባ አካሄደ።
********************************
‎የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ የ 2018 ዓም የሁለተኛ ሩብ አመት ስብሰባውን አከናውኗል።
‎የሆስፒታሉን የቦርድ ስብሰባ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ፣ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ እና የሆስፒታሉ ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አገና ነቶ መርተውታል።
‎በመድረኩ የሁለተኛ ሩብ አመት አፈፃፀም፣በባለፈው ስብሰባ በቦርዱ ውሳኔ ተላልፎባቸው የነበሩ ተግባራትን የአፈፃፀም ደረጃ እና በቀጣይ ውሳኔ የሚፈልጉ ጉዳዮች የቀረቡ ሲሆን የመስክ ምልከታም ተከናውኗል።
በቀረቡት ሪፖርቶች መነሻም ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን በቀጣይ የሚሰሩ ተግባራት ላይም የድርጊት መርሀግብር ማውጥት ያስቻለ ውይይት ተደርጓል።‎
‎ሆስፒታሉ ባጭር ጊዜ ውስጥ የላቀ ውጤት ስለማስመዝገቡም በውይይቱ ወቅት ማወቅ ተችሏል።

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 የሁለተኛ ሩብ አመት የህዝብ ፎረም መድረክ ተካሂዷል።*******************************ዛሬ በቀን 14/05/18 ዓም አላሙራ የመጀ...
22/01/2026

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 የሁለተኛ ሩብ አመት የህዝብ ፎረም መድረክ ተካሂዷል።
*******************************
ዛሬ በቀን 14/05/18 ዓም አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ከሆስፒታሉ ተገልጋይ ማህበረሰብ ጋር የህዝብ ፎረም መድረክ አካሂዷል።
በዕለቱም የሁለተኛ ሩብ አመት የሆስፒታሉ አፈፃፀም ሪፖርት፣ከዚህ በፊት የተነሱ ችግሮችና አሁን ላይ የተፈቱ፣እንዲሁም በMCC ኮሚቴ አማካኝነት የተሰሩ ስራዎች ቀርበዋል። በቀረቡት ሪፖርቶች ዙሪያ በሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ መድረክ ያዢነት ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ከተሳታፊዎችም አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተም ጥያቄና አስተያየት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል። በመጨረሻም የፎረሙ ታዳሚዎች በተቋሙ እየተሰራ ያለውን ስራ ያደነቁ ሲሆን መልካም አፈፃፀሞች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

Address

Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alamura Primary Hospital , Hawassa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share