Alamura Primary Hospital , Hawassa

Alamura Primary Hospital , Hawassa Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Alamura Primary Hospital , Hawassa, Medical and health, Awassa.

በሲዳማ ክልል የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከል በተደረገ ጥረት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ተካሄደ።*********************************...
28/02/2026

በሲዳማ ክልል የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከል በተደረገ ጥረት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ተካሄደ።
***********************************
ዛሬ በቀን 21/06/18 ዓም በሲዳማ ክልል የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከል በተደረገ ጥረት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ተካሂዷል።

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ በሀገሪቱ የተዘረጋው ጠንካራ የጤና ሥርአት በተለይ ለድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም መገንባት አስችሏል።

ለአብነትም የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በተደመረና በተባበረ አቅም ለመቆጣጠር በተደረገ ጥረት ስኬታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ነው የገለጹት።

በሽታውን ለመቆጣጠር በጂንካና በሃዋሳ ከተሞች የላቦራቶሪ ማዕከል በማቋቋም የመርመር አቅምን በማሳደግና ባለሙያዎችን በማሰልጠን በቅንጅት በተሰሩ ሥራዎች ወረርሽኙን መቆጣጠር ተችሏል ብለዋል፡፡

የአላሙራ መ/ደ/ሆስፒታል የጨቅላ ህፃናት ፅኑ ህክምና ክፍል የተመሰረተበትን አንደኛ አመት አከበረ።***********************************ዛሬ በቀን 17/06/18 ዓም የአላሙ...
24/02/2026

የአላሙራ መ/ደ/ሆስፒታል የጨቅላ ህፃናት ፅኑ ህክምና ክፍል የተመሰረተበትን አንደኛ አመት አከበረ።
***********************************
ዛሬ በቀን 17/06/18 ዓም የአላሙራ መ/ደ/ሆስፒታል ፅኑ ህክምና ክፍል የተመሰረተበትን አንደኛ አመት በተለያየ ሁነቶች አክብሯል።
በዕለቱም የጨቅላ ህፃናት ህክምና ከምስረታው አሁን እስከደረሰበት ጊዜ ያለው አጠቃላይ ጉዞን የሚዳስስ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን የፓናል ውይይትም ተኳሂዷል።በተጨማሪም በክፍሉ ጨቅላ ህፃናቶቻቸው በህክምና የተረዱና ከህመም ያገገሙላቸው ወላጆች ስለአገልግሎቱ አስተያየት የሰጡ ሲሆን ሆስፒታሉንም አመስግነዋል።
በመጨረሻም ለክፍሉ መደራጀት ከፍተኛ አስተዋዕፆ ላበረከቱት ለዶ/ር ህሊና ሲሳይ (Neonatology Fellow) የምስጋና ስጦታ ተበርክቷል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በ65 ኛው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ምስረታ ክብረበአል ላይ ተሳታፊ ሆኑ***********************************ዛሬ በቀን 15/...
22/02/2026

የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በ65 ኛው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ምስረታ ክብረበአል ላይ ተሳታፊ ሆኑ
***********************************
ዛሬ በቀን 15/06/17 ዓም የአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች የኢፌድሪ መከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ተኛ አመት አስመልክቶ በተዘጋጀ የምስረታ በዓል ላይ ተሳታፊ ሆነዋል። በእለቱም “ የልዩ ዘመቻዎች እዝ የላቀ ጀግንነት፣ ፅናትና ፍጥነት ከትክክለኛነት ጋር መለያው ነው”፣ “የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ የኢትዮዽያ የባህር በር ፍላጎት ታሪካዊ ባለቤትነታችንን የሚያረጋግጥ ነው” የሚልና ሌሎች መፈክሮች በሆስፒታሉ ሰራተኞች ተደምጧል። በክብረ በዓሉ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስቴርና የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶ/ር ዐብይ አህመድን ጨምሮ በርካታ የፌደራል፣ የመከላከያ፣የክልል እንዲሁም የከተማ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በ65 ኛው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ምስረታ ክብረበአል በተዘጋጀ የጎዳና ላይ ሩጫ ተሳታፊ ሆኑ*******************************...
14/02/2026

የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች በ65 ኛው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ምስረታ ክብረበአል በተዘጋጀ የጎዳና ላይ ሩጫ ተሳታፊ ሆኑ
***********************************
ዛሬ በቀን 07/06/17 ዓም የአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች የኢፌድሪ መከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ተኛ አመት በአልን አስመልክቶ በተዘጋጀ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ተሳታፊ ሆነዋል። የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ፣ የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ዋና አዛዥ ሌትናል ጀነራል ሹማ አብደታ እና ሌሎች የሀዋሳ ከተማ እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ የሁለተኛ ሩብ አመት ስብሰባ አካሄደ።********************************‎የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል ስራ አመራር ቦ...
30/01/2026

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ የሁለተኛ ሩብ አመት ስብሰባ አካሄደ።
********************************
‎የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ የ 2018 ዓም የሁለተኛ ሩብ አመት ስብሰባውን አከናውኗል።
‎የሆስፒታሉን የቦርድ ስብሰባ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ፣ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ እና የሆስፒታሉ ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አገና ነቶ መርተውታል።
‎በመድረኩ የሁለተኛ ሩብ አመት አፈፃፀም፣በባለፈው ስብሰባ በቦርዱ ውሳኔ ተላልፎባቸው የነበሩ ተግባራትን የአፈፃፀም ደረጃ እና በቀጣይ ውሳኔ የሚፈልጉ ጉዳዮች የቀረቡ ሲሆን የመስክ ምልከታም ተከናውኗል።
በቀረቡት ሪፖርቶች መነሻም ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን በቀጣይ የሚሰሩ ተግባራት ላይም የድርጊት መርሀግብር ማውጥት ያስቻለ ውይይት ተደርጓል።‎
‎ሆስፒታሉ ባጭር ጊዜ ውስጥ የላቀ ውጤት ስለማስመዝገቡም በውይይቱ ወቅት ማወቅ ተችሏል።

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 የሁለተኛ ሩብ አመት የህዝብ ፎረም መድረክ ተካሂዷል።*******************************ዛሬ በቀን 14/05/18 ዓም አላሙራ የመጀ...
22/01/2026

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 የሁለተኛ ሩብ አመት የህዝብ ፎረም መድረክ ተካሂዷል።
*******************************
ዛሬ በቀን 14/05/18 ዓም አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ከሆስፒታሉ ተገልጋይ ማህበረሰብ ጋር የህዝብ ፎረም መድረክ አካሂዷል።
በዕለቱም የሁለተኛ ሩብ አመት የሆስፒታሉ አፈፃፀም ሪፖርት፣ከዚህ በፊት የተነሱ ችግሮችና አሁን ላይ የተፈቱ፣እንዲሁም በMCC ኮሚቴ አማካኝነት የተሰሩ ስራዎች ቀርበዋል። በቀረቡት ሪፖርቶች ዙሪያ በሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ መድረክ ያዢነት ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ከተሳታፊዎችም አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተም ጥያቄና አስተያየት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል። በመጨረሻም የፎረሙ ታዳሚዎች በተቋሙ እየተሰራ ያለውን ስራ ያደነቁ ሲሆን መልካም አፈፃፀሞች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ለመላው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በሙሉ፣ እንኳን ለከተራ እና ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በአል በሰላም አደረሳችሁ!
18/01/2026

ለመላው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በሙሉ፣ እንኳን ለከተራ እና ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በአል በሰላም አደረሳችሁ!

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የስድስት ወር የበሽታ መከላከል አፈፃፀም ተገመገመ።**********************************ዛሬ በቀን 8/05/18 ዓም የሀዋሳ ከተማ አስተዳ...
16/01/2026

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የስድስት ወር የበሽታ መከላከል አፈፃፀም ተገመገመ።
**********************************
ዛሬ በቀን 8/05/18 ዓም የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ የድጋፍ ቡድን በተገኘበት የበሽታ መከላከል የስድስት ወር አፈፃፀም ተገምግሟል።
በዕለቱ የበሽታ መከላከልና የቤተሰብ ጤና ቡድን የስድስት ወር ሪፖርት፣ የሞዴል ቀበሌ validation ሪፖርት ግብረመልስ እና የመቶ ቀን እቅድ አፈፃፀም ሪፖርቶች ቀርበዋል።
በቀረቡት ሪፖርቶች ዙሪያ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከተሳታፊዎች ጥያቄና አስተያየቶች ተነስተው በሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ አማካኝነት ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።
በመጨረሻም በመቶ ቀን እቅድ ውስጥ የተካተተው ሞዴል ቀበሌ የመፍጠር ስራ እስከ ጥር 30 እንዲጠናቀቅ የድርጊት መርሀግብር የወጣ ሲሆን ተፈፃሚ እንዲሆንም የስራ መመሪያ ተላልፏል።

በአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሁለተኛ ሩብ አመት የEPAQ ሁለተኛ ዙር ድጋፋዊ ክትትል እና  የክላስተር ስብሰባ ተካሄደ።******አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በEPAQ mentor...
16/01/2026

በአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሁለተኛ ሩብ አመት የEPAQ ሁለተኛ ዙር ድጋፋዊ ክትትል እና የክላስተር ስብሰባ ተካሄደ።
******
አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በEPAQ mentorship ድጋፍ ከሚያደርግለት የቡልቻ ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ጋር በጋራ የሁለተኛ ሩብ አመት ክላስተር ስብሰባ አካሂዷል።
በዕለቱም የ2018 ሁለተኛ ሩብ አመት EPAQ ሁለተኛ ዙር ድጋፋዊ ክትትል ግብረመልስ ሪፖርት፣ የላይዘን ፎረምና የፀረ ተዋሲያን መድሀኒቶች በጀርሞች መለመድ ሳምንትን በተመለከተ“ አሁን እንተግብር፣ ዛሬን እንጠብቅ፣ የወደፊታችንን እናረጋግጥ” በሚል መሪ ቃል የግንዛቤ ማስጨበጫ ተካሂዷል።
በቀረቡት ሪፖርቶች እና ግንዛቤ ማስጨበጫ ዙሪያ ሰፋ ያለ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስያየቶች ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።

‎“ፈጠራና ዘላቂ ፋይናንስ ለጤናማ እናትነት” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ መርሃ ግብሮች ከሚከበረው የጤናማ እናትነት ወር አንድ አካል የሆነው የነፍሰጡር እናቶች ፎረም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ...
13/01/2026

‎“ፈጠራና ዘላቂ ፋይናንስ ለጤናማ እናትነት” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ መርሃ ግብሮች ከሚከበረው የጤናማ እናትነት ወር አንድ አካል የሆነው የነፍሰጡር እናቶች ፎረም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተከናወነ።
****************************
ዛሬ በቀን 05/05/18 ዓም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል “ፈጠራና ዘላቂ ፋይናንስ ለጤናማ እናትነት በሚል መሪ ቃል የነፍሰጡር እናቶች ፎረም ተከናውኗል።
በእለቱም ሁሉም እናቶች ጤናማ የእርግዝና፤ የወሊድና የድህረ-ወሊድ ጊዜ እንዲያሳልፉ አስፈላጊውን የጤና መረጃ እንዲኖራቸው የሚያግዝ የጤና ትምህርት ተሰጥቷል።
ከ200 በላይ ነፍሰጡር እናቶች በተሳተፉበት ፎረም ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከተሳታፊ እናቶችም ለተነሱ ጥያቄዎች ከመድረኩ መልስ ተሰጥቶባቸዋል።

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የመኪና ድጋፍ ተደረገለት****************************************የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በቀን 2/05/18 ዓም ከሀዋሳ ...
10/01/2026

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የመኪና ድጋፍ ተደረገለት
****************************************
የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በቀን 2/05/18 ዓም ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ለሆስፒታሉ ስራ የሚያገለግል የሀርድ ቶፕ መኪና ድጋፍ ተበርክቶለታል።
በዕለቱ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ሀላፊ አቶ ይርዳቸው አናቶ ለአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ ቁልፍ አስረክበዋል።
የመኪና ድጋፉን ላበረከቱልን የጤና መምሪያ ሀላፊ አቶ ይርዳቸው አናቶና ለመምሪያው ማናጅመንት በሆስፒታሉ ማህበረሰብ ስም ከልብ እናመሰግናለን።

ዛሬ በቀን 29/04/18 ዓ.ም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና የስራ አስተባባሪዎች ከተረኛ ባለሙያዎች ጋር በዛሬው እለት የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት መታሰቢያ በአል የሆነውን...
07/01/2026

ዛሬ በቀን 29/04/18 ዓ.ም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና የስራ አስተባባሪዎች ከተረኛ ባለሙያዎች ጋር በዛሬው እለት የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት መታሰቢያ በአል የሆነውን የገና በአልን በጋራ አክብረዋል።

Address

Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alamura Primary Hospital , Hawassa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram