28/02/2026
በሲዳማ ክልል የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከል በተደረገ ጥረት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ተካሄደ።
***********************************
ዛሬ በቀን 21/06/18 ዓም በሲዳማ ክልል የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከል በተደረገ ጥረት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የእውቅናና የምስጋና መርሃ ግብር ተካሂዷል።
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ሳህረላ አብዱላሂ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፣ በሀገሪቱ የተዘረጋው ጠንካራ የጤና ሥርአት በተለይ ለድንገተኛ አደጋዎች ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም መገንባት አስችሏል።
ለአብነትም የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በተደመረና በተባበረ አቅም ለመቆጣጠር በተደረገ ጥረት ስኬታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ነው የገለጹት።
በሽታውን ለመቆጣጠር በጂንካና በሃዋሳ ከተሞች የላቦራቶሪ ማዕከል በማቋቋም የመርመር አቅምን በማሳደግና ባለሙያዎችን በማሰልጠን በቅንጅት በተሰሩ ሥራዎች ወረርሽኙን መቆጣጠር ተችሏል ብለዋል፡፡