Ethiopian Pharmaceutical Supply Agency Gondar Branch

Ethiopian Pharmaceutical Supply Agency Gondar Branch I supply !!

እንቁጣጣሽ!!!🌼!!!
11/09/2023

እንቁጣጣሽ!!!🌼!!!

ጎንደር ቅርንጫፍ መስሪያቤት የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር አከናወነ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት  ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ  ከጎንደር...
22/07/2023

ጎንደር ቅርንጫፍ መስሪያቤት የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር አከናወነ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ከጎንደር ከተማ አስተዳደር በተረከበው ቦታ ላይ በየአመቱ ችግኝ በመትከል ፣ በመንከባከብ እና ጥበቃ በማድረግ የአረንጓዴ አሻራውን ሲያሳርፍ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን፡፡

በዚህም ኢትዬጵያን አረንጓዴ ለማልበስ በዛሬዉ እለት የጎንደር ቅርንጫፍ ሰራተኞች ከ 500 በላይ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ተከናውኗል ።

#ማገልገል ክብር ነዉ

30/03/2023
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ የጎንደር ከተማ በሚያዘጋጀው የጤና እግር ኳስ ውድድር የማራኪ ክፍለ ከተማን 11ለ 3 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸነፈ።
31/01/2023

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ የጎንደር ከተማ በሚያዘጋጀው የጤና እግር ኳስ ውድድር የማራኪ ክፍለ ከተማን 11ለ 3 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸነፈ።

ቅርንጫፉ መስሪያ ቤቱ የሁለተኛ ሩብ አመት የቆጠራውን እያካሄደ ይገኛል።የመጋዝን አያያዝ እና አስተዳደርን በማዘመን አመታዊ ቆጠራ ወደ ሩብ አመት ቆጠራ እንዲሁም ቆጠራው የሚወስደውን ግዜ በአ...
14/01/2023

ቅርንጫፉ መስሪያ ቤቱ የሁለተኛ ሩብ አመት የቆጠራውን እያካሄደ ይገኛል።
የመጋዝን አያያዝ እና አስተዳደርን በማዘመን አመታዊ ቆጠራ ወደ ሩብ አመት ቆጠራ እንዲሁም ቆጠራው የሚወስደውን ግዜ በአማካኝ ከ15 ቀን ወደ አንድ ቀን ማውረድ የቻለው የመአኤ ጎንደር ቅርንጫፍ በታታሪ ሰራተኞቹ በመታገዝ የ2015 ዓ/ም የሁለተኛ ሩብ አመት የቆጠራውን በብቃት እና በጥራት ከአንድ ቀን በታች ለመጨረስ አልም ቆጠራውን እያካሄደ ይገኛል።

ሁለቱ አጋር ተቋማት በደም ልገሳ እየተሳተፉ ይገኛል...የመድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ጎንደር ቅርንጫፍ እና የጠዳ ሳይንስ ኮሌጅ በጋራ የስምምነት ሰነድ በመፈራረም ስራ ከጀመሩበት ግዜ ጀምሮ በጋ...
12/01/2023

ሁለቱ አጋር ተቋማት በደም ልገሳ እየተሳተፉ ይገኛል...
የመድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ጎንደር ቅርንጫፍ እና የጠዳ ሳይንስ ኮሌጅ በጋራ የስምምነት ሰነድ በመፈራረም ስራ ከጀመሩበት ግዜ ጀምሮ በጋራ በርካታ ተግባራትን እየፈፀሙ ያሉ ተቋማት ሲሆኑ የዚህ ተግባር አንዳ አካል የሆነው የደም ልገሳ መርሀግብር በየሶስት ወሩ በሁለቱ ተቋማት ሰራተኞች ደሜን ለወገኔ በሚል መሪ ቃል ለአምስተኛ ግዜ ደም እየለገሱ ይገኛል።
Teda Health Science College

06/01/2023

እንኳን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ!

በዓሉ የሠላም፣ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆን እንመኛለን!

ማገልገል ክብር ነው!!!!!

ከመአኤ ጎንደር ቅርንጫፍ!!

27/12/2022

መልካም አፈፃፀም ላሳዩ የስራ ክፍሎች አውቅና በአግሎቱ ተሰጣቸው።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ለቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶች ፣ ዳይሬክቶሬቶች ፣ ቡድን መሪዎች እንዲሁም ሴት አመራሮች እውቅና የተሰጠ ሲሆን ሀገር በጦርነት በነበረችበት ወቅት የህክምና ግብአት ላቀረቡ ቅርንጫፎችም ልዩ ሽልማት ተሰጥቷል፡፡

በቅርንጫፍ አምሰት ጥሩ አፈጻጸም ያላቸው ቅርንጫፎች አዲስ አበባ ቁጥር 1፣ ጎንደር ፣ ሃዋሳ ፣ አዳማ እና ባህር ዳር ።

እንደ ሃገር ጦርነት እና በግጭት በነበረበት ወቅት የህክምና ግብአትን ለህብረተሰቡ በማቅረብ ከመንግስት አካላት ጋር በመቀናጀት ያደረሱ እንደ ደሴ ፣ ነቀምት ፣ ጎንደር ፣ ነጌሌ ቦረና ፣ ሰመራ ፣ ባህር ዳር እና አሶሳ ቅርንጫፎች ልዩ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡

የመድኃኒትና የህክምና መገልገያዎች ኮንትራት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ፤ የመጋዘን አያያዝና ክምችት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት እና የመድኃኒትና የህክምና መገልገያዎች ጥራትና ቁጥጥር ዳይሬክቶሬቶች ባስመዘገቡት ውጤት እዉቅና አግኝተዋል፡፡

ጥሩ አፈፃፀም ላመጡ ሴት ሃላፊዎችም አገልግሎቱ እዉቅና የሰጠ ሲሆን የድሬደዋ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አስናቀች ለችሳ እና የመጋዘን አያያዝና ክምችት አስተዳደር ዳይሬክተር ወ/ሮ ገዳምነሽ አስፈራው እውቅና ተሰጥቷል ፡፡

ሽልማቱ የበለጠ ለመስራት የሚያነሳሳቸው መሆኑን እና ውጤት ያመጣን መሸለም ባህል መሆን ይገባዋል ሲሉ እውቅናውን የተቀበሉ የሥራ አመራሮች ተናግረዋል።

#ማገልገል ክብር ነው።

አማኑኤል ወርቃየሁ

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ በ2013 ዓ/ም በአጠቃላይ ከቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶቾ አንደኛ በመሆን ተሸላሚ የነበር መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በ2014 ዓ/ም በተደረገው ...
26/12/2022

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ በ2013 ዓ/ም በአጠቃላይ ከቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶቾ አንደኛ በመሆን ተሸላሚ የነበር መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በ2014 ዓ/ም በተደረገው ግምገማ ቅርንጫፉ በወቅታዊ ሁኔታ ላይ የነበር ቢሆንም በአሰራር እና በአሰመዘገበው ውጤት የላቀ አፈፃፀም በማስመዘገብ ተሸላሚነቱን ማስጠበቅ ችሏል።
በተጨማሪም ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱ አገረ በገጠማት ፈተና በህክምናው ዘረፍ የግብአት አቅርቦት ላደረገው ከፍተኛ አስተዋጸኦ የዋንጫ እና የምስጋና ሰርተፍኬት ተሸላሚ መሆን ችሏል።

25/11/2022
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ የ2015 በጀት አመት አንደኛ ሩብ አመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ በቆላድባ ከተማ በማካሄድ ላይ ይገኛል።አገር በገጠማት ፈተና የግብአት...
22/10/2022

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ የ2015 በጀት አመት አንደኛ ሩብ አመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ በቆላድባ ከተማ በማካሄድ ላይ ይገኛል።
አገር በገጠማት ፈተና የግብአት አቅርቦቱ ላይ የአንበሳውን ድርሻ የሚወስደው ቅርንጫፉ በአጠቃላይ ከ 288 ሚሊዮን በላይ ግብአት አሰራጭቷል።
ተቋሙ ደራሽ ስራዎች ቢበዙበትም በመደበኛ ስራ ተጽዕኖ ሳያድርበት እየሰራ እንደሚገኝ እና ከአለፈው በጀት አመት አፈፃፀም እንዲሁም ከእቅድ አንፃር አመርቂ ውጤት እያስመዘገበ እንደሚገኝ የአፈፃፀም ሪፖርት ያቀረብት ተወካይ የእቅድ ክትትል ባለሞያ አቶ ደረጀ ሙሌ ገልፀዋል።

ጎንደር ቅርንጫፉ የ2015 የመጀመሪያው ሩብ አመት አጣቃላይ ቆጠራ በአንድ ቀን አጠናቆ ወደ ስራ ተመለሰ ::አገር በገጠማት ፈተና ግብአት በማድረስ እንዲሁም ዕለታዊ ስራዎቹ ፉታ ቢያሳጡትም ከ...
15/10/2022

ጎንደር ቅርንጫፉ የ2015 የመጀመሪያው ሩብ አመት አጣቃላይ ቆጠራ በአንድ ቀን አጠናቆ ወደ ስራ ተመለሰ ::
አገር በገጠማት ፈተና ግብአት በማድረስ እንዲሁም ዕለታዊ ስራዎቹ ፉታ ቢያሳጡትም ከመርህ ዝንፍ የማይለው በቁርጠኝነት ስራዎችን ለመከወን ፈተና የማይበግረው የቅርንጫፉ ስራተኛ በ2014 የጀመረውን በየሩብ አመቱ ቆጠራ ማካሄድ በ2015 በጀት አመትም የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ ዛሬ 05/02/2014 በአንድ ቀን ቆጠራውን አጠናቆ ወደ መደበኛ ስራው ተመልሷል።

09/09/2022
ጎንደር ቅርንጫፉ ድጋሚ ተመሰከረለት …………..                                                                                           ...
08/09/2022

ጎንደር ቅርንጫፉ ድጋሚ ተመሰከረለት ………….. የመድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ጎንደር ቅርንጫፍ ጷጉሜ 3/2013 ዓ/ም የአለም አቀፍ የጥራት አስተዳደር በመተግበር የ Iso 9001:2015 ስረተፍኬት ባለቤት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተሰጠዉ ስልጣን መሰረት ገምግሞ የጥራት እዉቅናዉን የሰጠዉ የኢትዮጲያ ተስማሚነት ጥራት ኤጀንሲ በየአመቱ የጥራት አስተዳደር ተግበራዉ ቀጣይነት ፣ መሻሻሎችን እና ሰነዶችን መሰረት ኦዲቲ (Surveillance Audit) የሚያደርጉ በመሆኑ በቅርንጫፉ በአካል በመገኝት ኦዲቱን (Surveillance Audit) አከናዉኗል፡፡ የኦዲቱ ዉጤት የተሰጠዉን ሰርተፍኬት የሚያስቀጥል ፣ የሚያሳግድ ወይም የሚያሰነጥቅ ሊሆን እንደሚችል ያሳዎቁት ኦዲተሮቹ የኦዲቱ ግብም የጥራት አስተዳደር ቀጣይነቱን ፣ የተደረጉ መሻሻሎችን እና ሰነዶችን በተቀመጠዉ እና አለም አቀፍ ስታንዳርድ መሰረት የተከተለ ሲሆን በኦዲቱ መሰረትም ቅርንጫፉ አለማቀፍ የጥራት መመዘኛወችን ያሟላ መሆኑ የተረጋገጠ በመሆኑ ቅርንጫፉ የጥራት አስተዳደር ያሰቀጠለ መሆኑ ተመስክሮለታል፡፡

የመድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ጎንደር ቅርንጫፍ በሐምሌ ወር 2011 ዓ/ም የአረንጓዴ አሻራ ለማሰቀመጥ ከጎንደር ከተማ አስተዳደር የችግኝ ቦታ በመረከብ በወቅቱ የነበረዉን የኤጀንሲዉ አመታዊ የስ...
26/08/2022

የመድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ጎንደር ቅርንጫፍ በሐምሌ ወር 2011 ዓ/ም የአረንጓዴ አሻራ ለማሰቀመጥ ከጎንደር ከተማ አስተዳደር የችግኝ ቦታ በመረከብ በወቅቱ የነበረዉን የኤጀንሲዉ አመታዊ የስራ አፈፃፀም ግምገማ ተከትሎ በግዜዉ በነበሩ የኤጀንሲዉ ዋና ዳይሬክተር ፣ ም/ዋና ዳይሬክተሮች እንዲሁም የጤና ሚኒሰተር አመራሮች በተገኙበት የችግን በተከለለዉ ቦታ ላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን ለችግኙ በየግዜዉ አስፈላጊዎን እንክብካቤ ሲያደርግ የቆየዉ ቅርንጫፉ በዚህ አመትም አረንጓዴ አሻራችን እናስቀጥላለን መትከል ብቻ ሳይሆን ተንከባክበን እናጸድቃለን በሚል መሪ ቃል መላ የመ/ቤቱ ሰራተኞች በነቂስ በመዉጣት ችግኞችን የመንከባከብ እንዲሁም ባለ ክፍት ቦታ ከከተማዉ ግብራና ጽ/ቤት ያገኛቸዉን 500 (አምስት መቶ) አዲስ ችግኞችን በተለያየ ቦታ መትከል ተችሏል፡፡ Gondar city communication Teda Health Science College

ሰሜን ምዕራብ ክላስተር 💪💪💪💪
04/08/2022

ሰሜን ምዕራብ ክላስተር 💪💪💪💪

31/07/2022
የመድኃኒት አቅረቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርነጫፍ በአመታዊ ቆጠራ ወቅት ሹፌሮች ነፃ መሆናቸዉን ተከትሎ ለ አምስት ቀናት ከጎንደር ዩኒቭርሲቲ ኤንስቲዩቲቭ  ቴክኖሎጅ ሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ዲፓር...
13/07/2022

የመድኃኒት አቅረቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርነጫፍ በአመታዊ ቆጠራ ወቅት ሹፌሮች ነፃ መሆናቸዉን ተከትሎ ለ አምስት ቀናት ከጎንደር ዩኒቭርሲቲ ኤንስቲዩቲቭ ቴክኖሎጅ ሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ዲፓርተመንት ጋራ ስምምነት በመፈራረም በተግባር የተደገፈ Driving and Vehicles preventive Maintenance ስልጠና በማሰጠት የሰርተፊኬት ባለቤት አድረጓል፡፡
ስለጠናዉ በርካታ እዉቀቶችን እንዳስገኝላቸዉ የገለጹት ሹፌሮቹ በግል የሰረተፊኬቱ ባለቤት መሆናቸዉ እንዳስደሰታቸዉ እና በስልጠናዉ ያገኙት እዉቀት የተቋማችን መኪኖች ከብልሽተ ነፃ ሆነዉ አገልግሎት እንዲሰጡ እንደሚያግዝ በመግለጽ ይህን እድል ላመቻቹት የቅርንጫፉ አመራሮች እና ለዩነቭርሲቲዉ መምህሮች ያላቸዉን ክብር እና ምስጋና ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ጎንደር ቅርንጫፍ የ2014 በጀት አመት አመታዊ የመድኃኒት እና የህክምና መገልገያዎች ቆጠራ ከአንድ  ቀን በታች በማጠናቀቅ ወደ መደበኛ ስራ ተመለሰ።
08/07/2022

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ጎንደር ቅርንጫፍ የ2014 በጀት አመት አመታዊ የመድኃኒት እና የህክምና መገልገያዎች ቆጠራ ከአንድ ቀን በታች በማጠናቀቅ ወደ መደበኛ ስራ ተመለሰ።

03/07/2022
01/07/2022

የተከበራቹሁ ደንበኞቻችን ከሰኞ (27/10/2014) በኃላ በአመታዊ ቆጠራ ምክንያት አገልግሎት የማንስጠ በመሆኑ ከዚህ ቀን በኃላ ደንበኛ የማናስተናግድ መሆኑን እየገለጽን ስራ የምንጀምርበትን ቀን በአጭር ቀን የምናሳዉቅ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

28/05/2022

ሱክሳሚቶኒየም (Suxamethonium) የተሰኘው የሠመመን ሰጭ መድሃኒት ወደ ሀገር ውስጥ ገብቶ መሰራጨት ጀመረ፡፡
================
በአለም አቀፍ የአቅርቦት ሰንሰለት ተግዳሮቶች ምክንያት ሰሞኑን እጥረት ይታይበት የነበረው ሱክሳሚቶኒየም የተባለው ሰመመን ሰጭ በመድኃኒት ከውጭ የሚገባ ከመሆኑም በላይ አንድ አቅራቢ የነበረው በመሆኑ የአቅርቦት መቆራረጥ ተከስቶ እንደነበር እና በዛሬ ቀን ግን ወደ ሀገር ውስጥ ገብቶ በመሰራጨት ላይ መሆኑን አቶ ሰለሞን ንጉሴ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ም/ ዋና ዳይሬክተር ግንቦት 19 ቀን 2014 ዓ.ም ገለጹ፡፡

ከህንድ ሀገር በአውሮፕላን ተጓጉዞ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ የደረሰው ሰመመን ሰጭ መድሀኒት በመላው ሀገሪቱ ለሚገኙ የመንግስት ሆስፒታሎች ለሁለት ወራት የሚያቆይ 37 ሺህ 500 ቪያልስ መጠን ያለው የሱክሳሚቶኒየም ማደንዘዣ መድኃኒት እንደሆነ አቶ ሰለሞን ገልጸዋል።

በአዲስ አበባ ለሚገኙ ሆስፒታሎች የተሰራጨ ሲሆን ለክልል ሆስፒታሎችም በጥቂት ቀናት ውስጥ ባሉን ቅርጫፎቻችን አማካኝነት ተጓጉዞ እንዲደርስ ይደረጋል ብለዋል፡፡

አቶ ሰለሞን አያይዘውም የሰመመን ሰጭ መድኃኒቶችን ጨምሮ በህይዎት አድን እና መሰረታዊ የህክምና ግብአቶች ላይ ወትሮ ዝግጁ የሆነ የአሰራር ስርዓት በመዘርጋት ከአቅራቢዎችም ሆነ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ በመስራት ዳግም ተመሳሳይ ችግሮች እንዳይከሰት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በቀጣዮቹ ሶስት ሳምንታት ደግሞ ለአንድ ዓመት ከአራት ወራት የሚያቆይ ክምችት ወደ ሀገር ውስጥ እንደሚገባ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አክለዋል፡፡

ቦሌ አውሮፕላን ጣቢያ እንደደረሰ በሶስት ሰአት ቆይታ አስፈላጊው የክሊላንስ ስራ ተሰርቶ ወደ አገልግሎቱ መጋዘን በማስገባት ሙያተኞች ኦፕሬሽን ስራ ላይ መሆናቸውን የተናገሩት በአገልግሎቱ የኮንትራት እስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ናሆም ገመቹ ያጋጠመውን የአቅርቦት መቆራራጥ በመረዳት በቅንጅት መሰራት ትልቅ ለውጥ እያመጣልን ነው ብለዋል፡፡ ይህን ችግር ለመቅረፍ አብረው ለሠሩ ባለ ድርሻ አካላትም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

16/05/2022

ከሰክሳሚቶኒየም (Suxamethonium) የተሰኘው የሠመመን ሰጭ መድሃኒት ውጭ ሌሎቹ ሰመመን ሰጪ መድኃኒቶች በበቂ መጠን መኖራቸውን አገልግሎቱ ገለፀ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በመድሃኒት የግዥ መዘርዝሩ ተካተው በመላ ሀገራችን ለሚገኙ ጤና ተቋማት የግብአቶችን ምጠና በማድረግ በግዥ ከሚያቀርባቸው፣ ከሚያከማቻቸው እና ከሚያሰራጫቸው የተመረጡ ከአስራ ሁለት (12) አይነት በላይ ለሰመመን ህክምና ከሚውሉት ግብአቶች ውስጥ ከሰክሳሚቶኒየም (Suxamethonium) በስተቀር በሌሎቹ ላይ እጥረት እንደሌለ የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ንጉሴ ግንቦት 7 ቀን 2014 ዓ.ም ገለፁ።
በመሆኑም መድሀኒቱን ከሚመረትበት ሀገር በዘላቂነት በማስመጣት እንዲሁም አሁን የተፈጠረውን የአቅርቦት መቆራረጥ ችግር በአስቸኳይ ለመቅረፍ በአየር ትራንስፖርት ከጎረቤት ሀገር ለማስገባት እየተሰራ ሲሆን በዚህ ሳምንት ውስጥ እጥረቱ ለተከሰተባቸው ጤና ተቋማት እንዲሰራጭ እናደርጋለን ብለዋል።
1. Bupivicaine-0.5% in 10ml ampoule injection
2. Cistracurium-2mg/ml in 10ml ampoule injection
3. Halothane-inhalation
4. Isofluroane-250ml-inhalation
5. Ketamine HCL 50mg/ml in 10ml ampoule injection
6. Lidocaine HCL 2% in 20ml injection
7. Lidocaine HCL + adrenalin (2% + 1:200,000) in 20ml vial injection
8. Pethidine HCL - 50mg/ml in ampoule injection
9. Propofol 10mg /ml in 20ml injection
10. Thiopental sodium 0.5g powder for injection
11. Vecuronium bromide 10mg in vial powder for Injection
የተባሉት በበቂ መጠን በክምችት ያሉ ሲሆን እነዚህን መድኃኒቶችን በመላው ሃገሪቱ ባሉ 17 ቅርንጫፎቻችን ላይ የሚገኙ በመሆናቸው እንዲሁም በየ ሁለት ሳምንቱ የክምችት ትንተና ሪፖርት በሚደረገዉ የFILL-IFS reporting system በማቅረብ ማግኘት እንደሚቻል ኃላፊው ገልፀዋል።
በተጨማሪም ከየቅርንጫፎቻችን ያለዉን ክምችት ወቅታዊ መረጃ ቀጣይነት ባለው መልኩ የምናቀርብ ይሆናል ።

Address

Ethiopia, Amhara, Gondar
Azezo

Telephone

+251918725144

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Pharmaceutical Supply Agency Gondar Branch posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian Pharmaceutical Supply Agency Gondar Branch:

Videos

Share