30/12/2022
እንኳን ደስ አላችሁ !!!
በምስራቅ ጎጃም ዞን የባሶ ሊበን ወረዳ በጤና መድህን ከክልል 1ኛ በመውጣቱ #፣አንድ ኮምፒውተር ከነ ፕሪንተሩ የፌደራል መንግስት # አንድ ኮምፒውተር ከነ ፕሪንተሩ የአማራ ክልል መንግስት በድምሩ 2 ኮምፒውተር እና 2ፕሪንተር እንዲሁም ለየጁቤ ጤና ጣቢያ # አንድ አልትራ ሳውንድ በተጨማሪም ዋንጫና ሰርተፍኬት በሽልማት የተበረከተ በመሆኑ የባሶ ሊበን ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ማስተዋል አንማው ለወረዳው አመራርና ህዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ። የባሶ ሊበን ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ማስተዋል አንማው ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ውጤት የተገኘው አመራሩና ህዝቡ እንዲሁም ባለድርሻ አካላት በመቀናጀት ስለሆነ ወደፊትም ይህ መተባበርና መደጋገፍ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።