ዶ/ር ሰናይ ዘሪሁን ፡ የህፃናት ስፔሻሊስት

ዶ/ር ሰናይ ዘሪሁን ፡ የህፃናት ስፔሻሊስት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ዶ/ር ሰናይ ዘሪሁን ፡ የህፃናት ስፔሻሊስት, Health & Wellness Website, Gamby Hospital, Bahir Dar.

22/05/2025

“...
'ብራዲ' ግን ምንድን ናት ?
እኔ D እባላለሁ የሁለት ልጆች እናት ነኝ የልጆቼ አባትም የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ሀኪም ነው። Intern እያለ ነበረ ፍቅር የጀመርነው ቶሎ ወደቁም ነገር እናሳድገው ብለን Gp ሆኖ በአመታችን ለመጋባት ወሰንን።እኔም በተመረቋት ትምህርት በትንሽዩ ደሞዝ ተቀጥሬ መስራት ጀመርኩ (ትንሽ አለመሆኗን እና ከሱ እኩል ይከፈለኝ እንደነበር ያወኩት ስራየን ከለቀኩኝ በኋላ ነበር😭😭)
አንድ በጣም መልከመልካም ፣ፀባዪ ንጉስ፣ሀኪም በስርዓተ ቤተክርስቲያን ላገባ እንደሆነ ቤተሰቦቼ የሰሙ ጊዜ....አቤት 😃😃😃ደስታ ፣ፈንጠዝያ። ሰርጉ እንደተጠበቀው በጥሎሽ እና በቁርጥ ያበደ አልነበረም፣ እኔም እሱም አላማችን ቶሎ ቤት መመስረት እንጅ ሰፈር ማብላት አልነበረም።(ውስጡን ለ...)
ኑሮ ጀመርን፣ ልጅ ተወለደ፣ ሀሳብ መጣ፣ኑሮ ጨመረ፣ ደሞ ሌላ እድል መጣ:- የትምህርት እድል (Residency)። ተመችቶን ከምንኖርባት የገጠር ከተማ ወደ አዲስአበባ ስደት፣ ከመንግስት ሰራተኝነት እኔ ስራ አጥ እሱ ደሞ ተማሪ ብቻ ህይወታችን በፈተና የተመላች ሆነች።
የአዲስአበባን ኑሮ ማሰብ አልፈልግም ለእግዚአብሔር ነግሬ መልስ አገኝበታለሁ ብዪ በእምባዪ ፅፌ አስቀምጬዋለሁ😭😭😭
ከተከራየናት ቤት ጀርባ ያለው ባለሱቅ ገና ስሄድ የዱቤ መመዝገቢያ ደብተሩን ያወጣ ነበር፣ብር ይዤ እንደማልሄድ ያውቃል ዋጋ ከፋይ ያድርግልኝ ብዪ እወስዳለሁ አሁንም ዱቤ አሁንም ብድር አሁንም የልጅ ወተት መግዣ ብድር።😭😭
ዶክተሩ ባለቤቴ ቤታችን ከሚማርበት በጣም ሩቅቅቅቅቅቅ ስለሆነ 11:00 ይነሳል ምሳ እቃውን እና 5ተኛ አመት ተማሪ እያለ አጎቱ የገዛለትን ላፕቶፕ ይዞ ይወጣል፣ ተረኛ ካልሆነ ማታ 1:30 ቤት የደርሳል አዳር ተረኛ ከሆነ ደግሞ እዛው ውሎ ከ36 ስዓታት በኋላ ይመለሳል።አቤት ድካም፣አቤት መጎሳቆል፣አቤት የእንቅልፍ እጦት፣አቤት ርሀብ😭😭
ቤት ይመጣል ስላችሁ በአካል ነው እንጅ መንፈሱ ሁሌም እዛው ሆስፒታል ነች፣ይደውላል፣ሜሴጅ ይልካል፣Voice ይልካል...ወዘተ
''ያቺ CS የሰራንላት.....ያቺኛዋ 'ብራዲ' ሆና....ጁኒየሩ ጋር ይደውላል
አስተማሪዎቹ ይደውላሉ
ህፃኑ እንዴት ሆነ
የየትኛዋ
የብራዲዋ😂
ሳላውቃት ይቺን ቃል ስወዳት😂
ሁሌ ይጠራታል
'None' ብላ ደግሞ የምትጀምር ሌላ ቃል አለች እሷም እኛ ቤት ቤተሰብ ነች😂
ብቻ አራት ሆነናል አኔ ፣ባለቤቴ፣ልጄ እና ታካሚዎቹ❤
እኔ በፊት ከቢሮ ቤቴ ሄጄ አንድም ስሰራው የዋልኩት ነገር ትዝ አይለኝም ነበር፣ እሱ ግን ቤት ይዟቸው ይመጣል ለካን የኔ ወረቀት እና ኮምፑዪተር የሱ ደሞ የሰው ህይወት ነው።
ሌሊት 5:30 ስልክ ይደወላል አነሳሁት ሴት ነች😏😏😏
ባሌ ሀኪም ባይሆን ምን ሊታሰብ እንደሚችል ታቁታላችሁ።
Intern ነች sorry
Doc
ዶ/ር የለም እንዴ
Hello
ኤጭ
ሰላም ነሽ እሱ ተኝቷል አስቸኳይ ነገር ከሆነ...ተናግሬ ሳልጨርስ ጆሮዪ ላይ ዘጋችው
ቀሰቀስኩት
መልሶ ደወለ
OR እየገባን ነው አሉት
ደም የፈሰሳትን እናት በድጋሚ ሊሰሩላት
ቁጭ ብለን እስከሚወጡ ጠበቅን
አይከፈለኝም አንጅ በጣም ብዙ ከተፃፉ ብዙ መፅሀፍ የሚወጣላቸው ገጠመኞች እና እንቅልፍ አልባ ሌሊቶችን አሳልፌያለሁ።
R4 እያለ አጎቱ ታመው መጡ፣ በአስተማሩት ዶክተሩ ልጃቸው ሊታከሙ😏😏😏
ኡኡ እቴ
በገንዘብ ማገዙን ተውትና ምናለበት ቤተሰብ ለማሳከም እንኳን ጊዜ ቢኖርህ ብሎ ተስፋ ቆርጦበት ተመለሰ
እናቴ ልትጠይቀን ዘመድም ልትሰናበት መጣች፣ቤታችንን ስታያት ደነገጠች፣ ወደ ውስጥ ስትገባ ደግሞ የበለጠ ተበሳጨች ሁሉ። አልጋና ፍራሽ ፣2 ኩርሲ፣ የምግብ መስሪያ እቃዎች በጣም በጥቂቱ ነበር ያለን። አዘነችልን፣ ምነው ተዘርፋችሁ ይሆን አለች😭 አይ እማ አወ ሌባው አልታወቀም እንጅ አወ ተዘርፈን ነው😭
መጨረስ አይቀርም 4ቱ አመት አለፈ፣አለቀ ተመስገን🙏🙏🙏አልኩኝ አልን አመሰገንን ስለታችንን አስገባን🙏
አዲስአበባንም ለቀቅን👏
እንደገና ሌላ አዲስ ቅጥር እና አዲስ ህይወት ተጀመረ። እዚህ ጋ ነው አለም ልክ አለመሆኗን የተረዳሁት፣ለተማሩ ሰዎች ቦታ እንደሌላት ያወኩት። ከበፊቱ በተመሳሳይ ደሞዝ ተቀጠረ፣ የሚሰራው ስራ ግን የስፔሻሊት ነው ገንዘቡ ግን ከ 4 አመት በፊት ሲከፈለው የነበረው ጋ ምንም ልዪነት የለውም።
ለምን???????
እሱም አኔም ተስፋ ቆረጥን
ቤተሰቦቻቸን እማ ቆዩ በኛ ተስፋ ከቆረጡ፣የጠላናቸው ሁሉ ከመሰላቸው ቆዪ። የኔን ባል ሳይሆን የታላቅ እህቴን እንጨት ነጋዴ ባሏን እያመሰገኑ እየመረቁ ይኖራሉ።
ተጨማሪ ስራ መስራት እንዳለብን መነጋገር ጀመርን፣ሆስፒታል ከሚያሳልፈው ጊዜ ላይ ቀንሶ ለኔና ለልጁ፣ለእምነቱ ፣ለራሱ፣ለቤተሰቡ ማዋል እንዳለበት ሽማግሌ አስቀምጬ አስመከርኩት።
ወደ ቀልቡ ተመለሰ እና ከነበረበት አዚም መንቃት ጀመረ እኔ ስራ እንድጀምር ገንዘብ ከቤተሰብ ተበደርን🙏 ትንሽየ የግል ስራ ጀመርኩ፣ እሱም የቤቱን ሀሳብ ማገዝ ጀመረ።
በሶስተኛው ወር አንድ ኩንታል ጤፍ ከራሴ ገንዘብ ላይ ስገዛ እና የልጄን የትምህርት ቤት ክፍያ ስከፍል የተሰማኝ ስሜት🙏🙏🙏
መማር ቤተሰብን መበተን ከሆነ ይቅር
መማር ልጅን ማስራብ ከሆነ ተውት
መማር እና ማወቅ ራስን መጉዳት ከሆነ ለምን ተብሎ ቢቀርስ
አሁንም ህዝብ አልነቃ ብሎ ነው እንጅ የጤና ባለሙያዎች ጥያቄ የኛ ነበር መሆን የነበረበት።
አልገባንም እንጅ የተማሩት የሰው ህይወት ማዳንን ነው፣ ወረቀት ላይ መግለጫ እንደመፃፍ ቀላል ነገር አይደለም ።
ሀኪሞች በስራቸው እና በትምህርት ምክንያት የበተኑት ቤተሰብ አሁን ላይ ወጥቶ ጥያቄው የኛ ነው ማለት ነበረበት።
መንግስት ቀልድ የሚመስል ቁማር በህዝቡ ላይ እየተጫወተ ይመስላል፣ አንዲት ነርስ ታካሚን የምትንከባከበውን ያክል ለልጇ ጊዜ ሰጥታ ለመንከባከብ አትችልም ሁኔታዎች አያስችሏትም።
ብራዲ
ታኪ
ነን ሪያሹሪንግ
ምን እንደሆኑ አሁን ገብተውኛል
አሁን አልገባሽ ያለኝ የዚህ System Non-reassuring Pattern ነው
ሁለተኛ ልጄ ወንድ ነው ስሙን 'ስር ነቀል' ብለውስ🤔
የጤና ባለሙያ በማግባቴ ከከፈልኩት ዋጋ ፣ካሳለፍኩት መከራ 0.1% አካፈልኳችሁ።
አይዟችሁ፣አይዞን🙏🙏
እህታችሁ D”

የዶ/ር አንዷለም ዳኜ ጠብቀው አጭር የህይወት ታሪክ========================[“ሕያው ሁኖ የሚኖር፣ ሞትንስ የማያይ ሰው ማን ነው?" መዝሙር 89:48]ዶ/ር አንዷለም ዳኜ ከአባታ...
04/02/2025

የዶ/ር አንዷለም ዳኜ ጠብቀው አጭር የህይወት ታሪክ
========================

[“ሕያው ሁኖ የሚኖር፣ ሞትንስ የማያይ ሰው ማን ነው?" መዝሙር 89:48]
ዶ/ር አንዷለም ዳኜ ከአባታቸው ከአቶ ዳኜ ጠብቀው እና ከወ/ሮ ደጌ ጥጉ ግንቦት 5 ቀን 1980 ዓ•ም• በምዕራብ ጎጃም ዞን ጓጉሳ ወንበርማ ወረዳ ቡራፈር ቀበሌ ተወለዱ። በወላጆቻቸው እንክብካቤ አድገው ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል በቡራፈር የመጀመሪያ ደርጃ ት/ቤት፣ መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ደግሞ በሽንዲ ከተማ ሽንዲ ት/ቤት ተከታትለዋል።

ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያለውን ትምህርታቸውን በቡሬ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተምረዋል። ከዚያም የ10ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ሁሉንም የትምህርት ዓይነት በማምጣት በከፍተኛ ነጥብ አልፈዋል። ከዚያም የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና የላቀ ውጤት በማምጣት አጠቃላይ ከት/ቤቱ አንደኛ በመሆን አጠናቀዋል።
ከዚያም በ2000 ዓ•ም• ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከገቡ በኋላ በዩኒቨርሲቲው ታሪክ በውስን የህክምና ተማሪዎች የተያዘውን ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ በ2005 ዓ•ም• የመጀመሪያ የህክምና ዶክትሬት ዲግሪያቸውን በእጅግ ከፍተኛ ማዕረግ የወርቅ ሜዳሊያና በዩኒቨርሲቲ ደርጃ የዋንጫ ተሸላሚ ሁነዋል።

በመቀጠልም በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በሌክቸረርነት ማዕረግ ተቀጥረው ከማስተማሩ እና ከምርምሩ ጎን ለጎን የሚውዱትን የህክምና ሙያ በመተግበር እያሉ ለላቅ ብቃት ደግሞ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቀዶ ህክምና ት/ት ክፍል ውስጥ በመማር በ2011 ዓ•ም• ተመርቀው ታዋቂ የቀዶ ህክምና ሀኪም ለመሆን በቅተዋል። በተጨማሪም በበጎ አድራጎት ህክምና በተለያዩ ሆስፒታሎች የቀዶ ህክምና አገልግሎት ለማህበረሰባቸው ሰጥተዋል።

ወጣትና ተመራማሪው ረዳት ፕሮፌሰር ዶ/ር አንዷለም ዳኜ ከነበራቸው የዕውቀት መሻት እና ከተገነዘቡት ከፍተኛ የወገን ችግር በመነሳት የጉበት፣ የሀሞት ከረጢት እና የቆሽት ሰብ ስፔሻላይዜሽን ት/ት በአ•አ• ዩኒቨርሲቲ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተከታትለው በ2016 ዓ•ም• አጠናቀው ዕንቁ ባለሙያ ለመሆን ችለው ነበር።
ዶ/ር አንዷለም ዳኜ በተለያዩ የት/ት እርከን ሲያልፉ በተለያዩ የውጭ ሀገራት ማለትም በጀርመን፣ በእንግሊዝ፣ በህንድ፣ በደ/አፍሪካ እና በቱርክ የተለያዩ ስልጠናዎችን የወሰዱና በዚህም ከፍተኛ ከበሬታን እንዳተረፉ የሙያ አጋሮቻቸው፣ መምህሮቻቸው፣ ተማሪዎቻቸው እና ታካሚዎቻቸው ይመሰክራሉ።

በስራቸውም ደከመኝ ሰለቸኝ የማያውቁ ቅን ፣ ትሁት፣ ሰው አክባሪ አዛኝና ሩህሩህ ሐኪም ነበሩ:: ለዚህም ብዙ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ተቋማት ለቅጥር ሲያጯቸው በማለት ለሚቀርብላቸው አጓጊ ገንዘብ እና ክብር አልተንበረከኩም::
ዶ/ር አንዱዓለም ዳኜ ህዝባቸውን ለማገልገል ካላቸው ከፍተኛ ፍቅር የተነሳ የሚሰጣቸውን ኃላፊነት ሁሉ በቅንነት ፈጽመዋል:: ዶ/ር አንዱዓለም ዳኜ ሀይማኖተኛ፣ ለሰው ሁሉ መልካም አሳቢ፣ ታጋሽ፣ ደግ፣ አንደበተ ርቱዕ ነበሩ::

የቤተሰባቸውን ሁኔታ በተመለከተ ጋብቻቸውን በስርዓተ ተክሊል በታላቁ ደብረ ሮሀ ቅዱስ ላሊበላ ገዳም በ2006 ዓ•ም• የፈጸሙ ሲሆን ከውድ ባለቤታቸው ከወ/ሮ ቤዛየ ግርማ የስምንት ዓመትና የአምስት ወር ዕድሜ ያላቸው ሁለት ሴቶችና የአምስት ዓመት ዕድሜ ያለው አንድ ወንድ ልጅ አፍርተዋል። ለቤተሰባቸውም ፍቅር የሚሰጡ፣ እጅግ የሚናፈቁ ተወዳጅ አባት ነበሩ::
ይህ በእንዲህ እንዳለ ወጣቱ ሐኪም፣መምህርና ተመራማሪ ዶ/ር አንዱዓለም ዳኜ ሩቅ አስበው ስራ ውለው ወደ ቤታቸው ለመድረስ ጥቂት ሲቀራቸው መኪናቸውን እያሽከረከሩ እያለ በተተኮሰባቸው ጥይት ተመተው ጥር 24/2017 ዓ• ም• በተወለዱ በ 37 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል::

ሥርዓተ ቀብራቸውም ቤተሰቦቻቸው፣ የሥራ ባል ደረቦቻቸው፣ ተማሪዎቻቸው፣ታካሚዎቻቸው እና ወዳጆቻቸው በተገኙበት ጥር 25 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ7:00 በባህር ዳር ከተማ በድባንቄ መካነ-ህያዋን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።
ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መጽናናትን እየተመኘን ፤ ነፍሳቸውን በአባቶቻችን በአብርሃም፣ በይስሀቅ እና በያዕቆብ ቦታ በአጸደ ገነት ያሳርፍልን።

የሀዘን እንጉርጉሮ
==========
በክፉ በደጉ ከፊት የሚቀድም ፣
አንዷለም አንዷለም አንዱ እንቋችን የለም።
ለጆሮ ይከብዳል ውስጥን ለማሳመን ፣
ይኸንን ሞት መስማት እንደምን ያሳዝን።
ስንቱ እየለመነህ ስንቱ እያማተረ፣
ዕንቁ ጭንቅላትህ ቆሼ ላይ አደረ፣
የወዳጅ ዘመድህ ልቡ ተሰበረ።
ሜዳሊያ ያንተ ነው ሞራልና ወርቁ፣
አንተን የሚመሰል አይገኝም ዕንቁ።
አሜሪካ አማትራህ ለምኖህ አውሮፓ፣
ለወገንህ ፍቅር በገንዘብ ሳትለካ፣
ሌት ተቀን ስትለፋ ነበር የምትረካ።
ጉበቱና ጣፊያው ቆሽቱ ተቃጠለ፣
አንተ እምታክመው ለአንተ ሲል ቀለለ፣
ሀዘኑ ቅጥ አጣ እያለ።

በዶር ዓለማየሁ ባዬ

03/11/2024
ይድረስ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ላለባቸው ወገኖቻችን በሙሉ!!!ለባሕር ዳር ከተማ እና አካባቢው ህዝብ ከፍተኛ አገልግሎት በመስጠት በቀዳሚነት የሚታወቀው የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስ...
03/08/2024

ይድረስ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ላለባቸው ወገኖቻችን በሙሉ!!!

ለባሕር ዳር ከተማ እና አካባቢው ህዝብ ከፍተኛ አገልግሎት በመስጠት በቀዳሚነት የሚታወቀው የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከHCP cure blindness ጋር በመተባበር ለ12ኛ ጊዜ ከነሐሴ 25 እስከ 29/2016 ዓ.ም ድረስ ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ጥገና ህክምና ይሰጣል እንደሚሰጥ አስታውቋል።

ስለሆነም በዓይን ሞራ ግርዶሽ የሚሰቃዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ጤና ለመታደግ በሚሰጠው የነፃ ህክምና እድሉ ተጠቃሚ ለመሆን ከዚህ በታች በተቀመጡት የምዝገባ ቦታና ጊዜ መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን ሆስፒታሉ ያወጣ መሆኑን አገልግሎቱን የሚፈልጉ ወገኖቻችን በሙሉ:-
1ኛ: ከሐምሌ 29-30/2016 በመራዊ ከተማ
2ኛ: ነሐሴ 05/2016 በዓርብ ገበያ ከተማ
3ኛ፡ ነሐሴ 11/2016 በአንበሳሜ ከተማ
4ኛ፡ ነሐሴ 12/2016 በሐሙሲት ከተማ
5ኛ: ከነሐሴ 18-19/2016 በአዴት ከተማ
6ኛ፡ ከነሐሴ 18-23/2016 በባሕር ዳር ፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ላይ የቅድመ ልየታ ስራ ስለሚሰራ በተጠቀሱት ቦታዎች በመገኘትና በመመርመር የእድሉ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ተጋብዘዋል።

ሆስፒታሉ ባለፉት ተከታታይ 11 ጊዜያት ከ11ሺ 500 ለሚሆኑ ታካሚዎች የነፃ ቀዶ ህክምና ተደራሽ በማድረግ የላቀ ማህበረሰብ አገልግሎት የመስጠት አድማሱን እያሰፋ የመጣ ሲሆን በዚህ ዙርም 500 ለሚሆኑ ታካሚዎች ለመስጠት የሚያስችለውን የቅድመ ዝግጅት ስራ አጠናቆ የምዝገባ እና ልየታ ስራ ሊጀምር መሆኑን ስላሳወቀ መረጃው ለሚመለከታቸው ሁሉ እንዲደርስ ማድረግ ይገባል።

ለተጨማሪ መረጃ ፡- ስልክ ቁጥር፡ በ09 21 57 73 68 ይደውሉ፡፡
የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል
ባሕር ዳር

01/01/2024

የሶማሊላንድ ምንጮቼ ጋር ደወል አደረግኩ!

በሚድያዎቻችን እንደተዘገበው ሀገራችን የወደብ "ባለቤት" መሆኗን በመጥቀስ ማብራርያ እና ማረጋገጫ ጠየቅኩ። መልሱ ይህ ነው:

"የተፈራረምነው ለወደብ ኪራይ ስምምነት የሚሆን የመግባብያ ሰነድ (MoU) ነው። ዝርዝር ዶክመንቱን scan በማድረግ ይፋ እናደርጋለን። ከዚህ ውጭ ያለ መረጃ ሁሉ የተሳሳተ ነው"

ታድያ እንዴት በአመታት የተገደበ የወደብ ኪራይ ውል "የወደብ ባለቤት" ተብሎ ይቀርባል?

Elias Meseret

አጣዬ ዳግም ጦርነት ታዉጆባታል 😭 ስርአት አልባ መንግስት።
24/01/2023

አጣዬ ዳግም ጦርነት ታዉጆባታል 😭 ስርአት አልባ መንግስት።

እጅግ ልብ ይነካል። ፍትህ ለዶ/ር ታዘባቸዉ !!!
21/07/2022

እጅግ ልብ ይነካል።

ፍትህ ለዶ/ር ታዘባቸዉ !!!

#ሐኪም

 #በቃን
23/06/2022

#በቃን

የህፃናት የጭንቅላት ውስጥ ኢንፌክሽን | meningitis in childrenየሰው ልጅ አንጎል (brain) በመጠን የሚያድገው እና የሚሰለጥነው (brain growth and development...
30/04/2022

የህፃናት የጭንቅላት ውስጥ ኢንፌክሽን | meningitis in children

የሰው ልጅ አንጎል (brain) በመጠን የሚያድገው እና የሚሰለጥነው (brain growth and development) በመጀመሪያዎቹ ሁለት የእድገት አመታት ነው።

በዚህ ወሳኝ የአንጎል የእድገት ደረጃ የሚፈጠር ማንኛውም ችግር ለወደፊት የቀሪ የህይወት ዘመን ትልቅ ጠባሳ ጥሎ ሊያልፍ ይችላል። ስለዚህ ህፃናት በማህፀን ውስጥ እያሉ የአንጎል አፈጣጠር ችግር ከሌለባቸው በቀር ከተወለዱ በኋላ በሚከሰቱ ተያያዥ ችግሮች የሚመጣውን የአንጎል መጎዳት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል አስፈላጊውን ህክምና በማድረግ መከላከል ይቻላል። ከነዚህ ለህይወት አስጊ ከሆኑ ችግሮች መካከል አንዱ ደግሞ የጭንቅላት ውስጥ ኢንፌክሽን ነው።

ሀ.የጭንቅላት ውስጥ ኢንፌክሽን ምልክቶቹ ምንድናቸው?

የጭንቅላት ኢንፌክሽ በጊዜ ተመርምሮ ካልታከመ ለህፃናት የጤንነት እክል (morbidity) እና ሞት (mortality) ትልቁን ሚና ከሚጫወቱት አስቀያሚ በሽታዎች አንዱ ነው።

ዘመኑ ያፈራቸው የክትባት መድሃኒቶች በብዙ ባክቴሪያ የሚከሰተውን የጭንቅላት ኢንፌክሽን በአለፉት ትንሽ አስርት አመታት በብዙ እንደቀነሱት መረጃዎች ያሳያሉ።

አንድ የጭንቅላት ኢንፌክሽ ያለበት ህፃን ከሚያሳያቸው ምልክቶች መካከል

1.ከፍተኛ የሆነ የማያቋርጥ ትኩሳት

2.ምርር ብሎ በሀይለኛው ማልቀስ (high pitched cry) እና መነጫነጭ (irritability)

3.ያልተለመደ የሰውነት መንዘር/መንቀጥቀጥ (seizure)

4.ራስን መሳት (loss of consciousness)

5. አንገት/ጋንጃ አካባቢ የህመም ስሜት መሰማት (neck stiffness)

6. ከፍተኛ የሆነ የራስ ምታት ስሜት (headache)
7. ማቅለሽለሽ የሌለው ማስመለስ (projectile vomiting) ሊሆኑ ይችላሉ።

ለ.የሚያስከትለው ጉዳት (complications) ምን ሊሆን ይችላል?
1.ለሚጥል በሽታ መጋለጥ (epilepsy)
2.የእድገት መገታት (neurodevelopmental delaye)
3.የጀሮ የመስማት ችግር ና የአይን እይታ ማጣት
4.ግማሽ የሰውነት ክፍል ወይም እጅ እግር መስነፍ (stroke)
5. የጭንቅላት ውስጥ ግፊት መጨመር (increased ICP) እና ሌሎች ችግሮችንም ሊያስከትል ይችላል።

ሐ.የጭንቅላት ውስጥ ኢንፌክሽን የሚመስሉ ምልክቶችን ካዩና የልጅዎ ጤና ካሳሰበዎት ምን ማድረግ አለበዎት?

1.ቶሎ ወደ ጤና ተቋም መውሰድ እና ትክክለኛ ህክምና እንዲያገኝ ማድረግ ይኖርበዎታል።

2.በሃኪም ያልታዘዙ መድሃኒቶችን አልመስጠት።

3.ያልተለመደ የሰውነት መንቀጥቀጥ እና ሃይለኛ ትኩሳት ካለ የባህል ህክምና ወይም ሌላ ባህላዊ የሆነ አማራጭን ከመጠቀም ቅድሚ ወደ ጤና ተቋም መውሰድ ይኖረበዎታል።

መ. የጭንቅላት ውስጥ ኢንፌክሽን መከላከያ መንገዶች

ምንም እንኳ ሙሉ በሙሉ መከላከል ባይቻልም ይሄን ችግር በትንሹም ቢሆን ተጋላጭነትን መቀነስ ይቻላል።

1.ልጀዎትን በሃገሪቱ የክትባት መርህ መሰረት(EPI schadule ) እየተከታተሉ ያስከትቡ

2.በአደጉት ሀገራት እንደአስፈላጊነቱ የጭንቅላት ኢንፌክሽን በሚያመጡ ባክተሪያዎች ከተያዘ ሰው ጋር የቅርብ ንክኪ ላላቸው ሰዎች ቅድመ መከላከያ ፀረ-ባክተሪያ መድሃኒት ይሰጣሉ። ይህም በበሽታው ከመያዝ በትንሹ ቢሆንም ይከላከላል።

መልካም ቀን
ዶ/ር አማረ አስቻለው የህፃናት ስፔሻሊስት ሐኪም (BDU, TGSH)

Address

Gamby Hospital
Bahir Dar
08

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዶ/ር ሰናይ ዘሪሁን ፡ የህፃናት ስፔሻሊስት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to ዶ/ር ሰናይ ዘሪሁን ፡ የህፃናት ስፔሻሊስት:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram