Debre Markos city administration health office

Debre Markos city administration health office በዚህ ገፅ ዓለም አቀፋዊ፣ አገራዊ፣ ክልላዊ፣ የከተማውንና የአካባቢውን ወቅታዊ የጤና ጉዳይ መረጃዎችን እናጋራለን።

የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ የ2018 በጀት አመት የስድስት ወር አፈፃፀም ገምግሟል። =======================================================...
27/01/2026

የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ የ2018 በጀት አመት የስድስት ወር አፈፃፀም ገምግሟል።
==============================================================

ቀን: 19/05/2018ዓ.ም

የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ የ2018 በጀት አመት የስድስት ወር አፈፃፀም ገምግሟል። በግምገማው የጤና መምሪያ ሰራተኞች፣ የሆስፒታል እና ጤና ጣቢያ ሃላፊዎች እና የስራ ክፍል አስተባባሪዎች፣ የግል ጤና ተቋማት እና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። በመድረኩ የጤና መምሪያው የስድስት ወር አፈፃፀም ቀርቧል፤ በተሳታፊዎችም ሃሳቦች ተነስተዋል።

የጤና ተቋማት መሠረተ ልማት፣ የሰው ሃይል ልማትና ስምሪት፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መለየትና መፍታት፣ የውስጥ ገቢን፣ የመድሃኒት እና ህክምና መሳሪያዎች አቅርቦት ፣ የላቦራቶሪ ምርመራ፣ የህክምና እና ሪፈራል ትስስር፣ የጤና ስራዎችን የሚያግዙ የተቋምና የማህበረሰብ መዋቅሮችን እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።

27/01/2026

The government of today declared the end of its first-ever outbreak of Marburg virus disease.

World Health Organization (WHO) recognizes the measures taken by the Ministry of Health,Ethiopia and the Government of Ethiopia.

The outbreak was contained in less than three months through a response led by the government and supported by WHO and other partners.

WHO activated its emergency response within 24 hours of the outbreak, deploying 36 experts and redirecting 28 additional staff to support field operations.

Our collaboration enabled the rapid expansion of diagnostic capacity, strengthened patient care and supported effective outbreak control at the frontline.

https://www.afro.who.int/countries/ethiopia/news/ethiopia-declares-end-first-ever-marburg-virus-disease-outbreak

26/01/2026
25/01/2026

WHO statement on notification of withdrawal of the United States

As a founding member of the World Health Organization (WHO), the United States of America has contributed significantly to many of WHO’s greatest achievements, including the eradication of smallpox, and progress against many other public health threats including polio, HIV, Ebola, influenza, tuberculosis, malaria, neglected tropical diseases, antimicrobial resistance, food safety and more.

WHO therefore regrets the United States’ notification of withdrawal from WHO – a decision that makes both the United States and the world less safe. The notification of withdrawal raises issues that will be considered by the WHO Executive Board at its regular meeting starting on 2 February and by the World Health Assembly at its annual meeting in May 2026.

WHO takes note of statements from the government of the United States that say WHO has “trashed and tarnished” and insulted it, and compromised its independence. The reverse is true. As we do with every Member State, WHO has always sought to engage with the United States in good faith, with full respect for its sovereignty.
In its statements, the United States cited as one of the reasons for its decision, “WHO failures during the COVID-19 pandemic”, including “obstructing the timely and accurate sharing of critical information” and that WHO “concealed those failures”. While no organization or government got everything right, WHO stands by its response to this unprecedented global health crisis. Throughout the pandemic, WHO acted quickly, shared all information it had rapidly and transparently with the world, and advised Member States on the basis of the best available evidence. WHO recommended the use of masks, vaccines and physical distancing, but at no stage recommended mask mandates, vaccine mandates or lockdowns. We supported sovereign governments to make decisions they believed were in the best interests of their people, but the decisions were theirs.

Immediately after receiving the first reports of a cluster of cases of “pneumonia of unknown cause” in Wuhan, China on 31 December 2019, WHO asked China for more information and activated its emergency incident management system. By the time the first death was reported from China on 11 January 2020, WHO had already alerted the world through formal channels, public statements and social media, convened global experts, and published comprehensive guidance for countries on how to protect their populations and health systems. When the WHO Director-General declared COVID-19 a public health emergency of international concern under the International Health Regulations on 30 January 2020 – the highest level of alarm under international health law – outside of China there were fewer than 100 reported cases, and no reported deaths.

In the first weeks and months of the pandemic, the Director-General urged all countries repeatedly to take immediate action to protect their populations, warning that “the window of opportunity is closing”, “this is not a drill” and describing COVID-19 as “public enemy number one”.
In response to the multiple reviews of the COVID-19 pandemic, including of WHO’s performance, WHO has taken steps to strengthen its own work, and to support countries to bolster their own pandemic preparedness and response capacities. The systems we developed and managed before, during and after the emergency phase of the pandemic, and which run 24/7, have contributed to keeping all countries safe, including the United States.

The United States also said in its statements that WHO has “pursued a politicized, bureaucratic agenda driven by nations hostile to American interests”. This is untrue. As a specialized agency of the United Nations, governed by 194 Member States, WHO has always been and remains impartial and exists to serve all countries, with respect for their sovereignty, and without fear or favour.

WHO appreciates the support and continued engagement of all its Member States, which continue to work within the framework of WHO to pursue solutions to the world’s biggest health threats, both communicable and noncommunicable. Most notably, WHO Member States last year adopted the WHO Pandemic Agreement, which once ratified will become a landmark instrument of international law to keep the world safer from future pandemics. Member States are now negotiating an annex to the WHO Pandemic Agreement, the Pathogen Access and Benefit Sharing system, which if adopted will promote rapid detection and sharing of pathogens with pandemic potential, and equitable and timely access to vaccines, therapeutics and diagnostics.

We hope that in the future, the United States will return to active participation in WHO. Meanwhile, WHO remains steadfastly committed to working with all countries in pursuit of its core mission and constitutional mandate: the highest attainable standard of health as a fundamental right for all people.

24/01/2026
    🧗🏻‍♂️🚵🏻‍♀️የአማራ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት  #ለደብረማርቆስ እና  #ደብረታቦር ቅርንጫፎች  ለተለያዩ የስራ መደቦች የቅጥር ማስታወቂያዎችን አውጥቷል።
23/01/2026

🧗🏻‍♂️🚵🏻‍♀️

የአማራ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት #ለደብረማርቆስ እና #ደብረታቦር ቅርንጫፎች ለተለያዩ የስራ መደቦች የቅጥር ማስታወቂያዎችን አውጥቷል።

የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር አዋጅ 🗞📘(የፌደራል ነጋሪት ጋዜጣ አዋጅ ቁጥር 1362/2017)ከ https://t.me/Health_Library_1/1267 የቴሌግራም ሊንክ ላይ ማግኘ...
23/01/2026

የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር አዋጅ 🗞📘
(የፌደራል ነጋሪት ጋዜጣ አዋጅ ቁጥር 1362/2017)

https://t.me/Health_Library_1/1267 የቴሌግራም ሊንክ ላይ ማግኘትና ማንበብ ይችላሉ።

ከዚህ አዋጅ ከታች የተገለፁትንና ሌሎችንም የጤና ጉዳዮች ያውቁበታል።

🙌የተገልጋዮች እና ጤና ተቋማት መብት እና ግዴታዎች
🙌የጤና አገልግሎት መርሆች
🙌የህክምና አገልግሎት እና ቀበብሎሽ ስርዓት
🙌የጤና ዘርፍ የሰው ሃብት ልማትና አስተዳደር
:
:

የጤና ዘርፍ ሠራተኞች የማህበራዊ ጤና መድኅን አገልግሎት ተጠቃሚ ሆኑየጤና ዘርፍ ሠራተኞችና ቤተሰቦቻቸውን ተጠቃሚ የሚያደርግ የማህበራዊ ጤና መድህን አገልግሎት ትግበራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር...
23/01/2026

የጤና ዘርፍ ሠራተኞች የማህበራዊ ጤና መድኅን አገልግሎት ተጠቃሚ ሆኑ

የጤና ዘርፍ ሠራተኞችና ቤተሰቦቻቸውን ተጠቃሚ የሚያደርግ የማህበራዊ ጤና መድህን አገልግሎት ትግበራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡

የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ተስፋዬ ወርቁ እንዳሉት ÷ጤናማና አምራች ዜጋ በመፍጠር የሀገርን እድገት እውን ለማድረግ በርካታ ስትራቴጂዎችና ሪፎርሞች ተቀርጸው እየተተገበሩ ነው ፡፡

ሁሉን አቀፍ የጤና ሽፋን ለማሳካት እንዲቻል ከተቀረጹ የተለያዩ ስትራቴጂዎችና ፕሮግራሞች መካከል አንዱ የጤና መድኅን አገልግሎት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

በመደበኛ ክፍለ ኢኮኖሚ ለተሰማሩ ዜጎችና ለጡረታ ባለመብቶች የማህበራዊ የጤና መድኅን እንዲሁም መደበኛ ባልሆነው የኢኮኖሚ ዘርፍ ለተሰማሩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የማሕበረሰብ አቀፍ የጤና መድኅን ሥርዓት መቀረጹን አመልክተዋል፡፡

የማሕበረሰብ አቀፍ የጤና መድኅን ሥርዓትን ወደ ሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በማስፋፋት በ2017 ዓ.ም ከ13 ነጥብ 7 ሚሊየን በላይ እማ/አባወራዎች አባል ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል፡፡

በዚህም ከ63 ሚሊየን በላይ ዜጎችን የጤና መድኅን ሽፋን መስጠት የተቻለ ሲሆን÷ ከዚህ ውስጥ የ19 ሚሊየን ዜጎች ዓመታዊ የአባልነት መዋጮ በመንግሥት መሸፈኑን አብራርተዋል፡፡

በሌላ በኩል በመደበኛ ክፍለ ኢኮኖሚ ለተሰማሩ ዜጎችና የጡረታ ባለመብቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ የተቀረጸው የማህበራዊ የጤና መድኅን ሥርዓት ለመተግበር እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በዚህ መሰረትም የጤናው ዘርፍ የመንግሥት ሠራተኞች በስራቸው ባህርይ ምክንያት የጤና እክል ሲያጋጥማቸው የሕክምና አገልግሎት ወጪያቸው በመንግሥት ተሸፍኖ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ ሰፊ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰዋል፡፡

በመሆኑም አዲስ በወጣው የጤና አገልግሎት አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 1363 ላይ የጤና ዘርፍ የመንግሥት ሠራተኛ የጤና መድኅን አባልነት ሙሉ መዋጮ በመንግስት እንዲሸፈን ተደንግጓል ነው ያሉት።

ስለሆነም በአዋጁ መሰረት በጤናው ዘርፍ ተቀጥረው የሚሰሩ የመንግሥት ሠራተኞች የማሕበራዊ የጤና መድኅን አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን አብስረዋል፡፡

ትግበራውን ደረጃ በደረጃ በማስፋት ሁሉም የመንግስት ሠራተኞች እና የጡረታ ባለመብቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ ያላሰለሰ ጥረት እንደሚደረግም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡


#አብክመጤናቢሮ

20/01/2026

የአይን መነፅር አይነቶች እና ጠቀሜታቸዉ
____________

መነፅር (eye glasses) በፍሬም ውስጥ የተቀመጡ ሌንሶች ያሉት፣ የእይታ ችግርን ለማስተካከል፣ ለማሻሻል ወይም የዓይንን ጤና ከጎጂ ብርሀን እንዲሁም ከአደጋ ለመጠበቅ የሚያስችል ኦፕቲካል መሣሪያ ነው።

👉 የመነፅር አይነቶች እና ጠቀሜታቸዉ

1. የነጠላ እይታ ማስተካከያ መነፅሮች (Single Vision Eye Glasses)

የአንድን እይታ (የርቀት ወይም የቅርበት) ችግርን ለማስተካከል የሚያገለግሉ መነፅሮች ሲሆኑ ማነኛዉም ችግር በሀኪም የተረጋገጠ እና የታዘዘለት ሰዉ ብቻ ሊጠቀማቸዉ ይገባል፡፡

2. ባይፎካል መነፅሮች (Bifocal Eye Glasses)

አብዛኛዉን ጊዜ እድሜያቸዉ ከ40 አመት በላይ የሆኑ ሰዎች የሚጠቀሟቸዉ ለርቀት እና ቅርበት የማየት ችግር ማስተካከያ የሚያገለግሉ ሲሆኑ በግልፅ የሚታይ መስመር ያላቸዉ መነፅሮች ናቸዉ፡፡

3. ፕሮግሬሲቭ መነፅሮች (Progressive Eyeglasses)

በአንድ መነፅር ላይ ለርቀት፣ ለመካከለኛ ርቀት (ኮምፒውተር) እንዲሁም ለቅርበት (ለንባብ) እይታን ለማገዝ የሚያገለግሉ መነፅሮች ሲሆኑ በግልፅ የሚታይ መለያ መስመር የላቸዉም፡፡

4. የኮምፒዉተር መነፅሮች

ከስክሪን የሚመጣ ሰማያዊ ብርሃንን ወደ አይን እንዳይገባ በመከላከል የዓይንን ጤና የሚጠብቁ እና የአይን ድካምን የሚቀንሱ መነፅሮች ናቸዉ፡፡ ረጅም ሰዓት ኮምፒውተር፣ ስልክ ወይም ዲጂታል መሳሪያ ለሚጠቀሙ ሰዎች ያገለግላሉ፡፡

5. የደህንነት መነጽሮች (Safety/protective eye glasses)

ዓይንን ከጉዳት (ከኬሚካሎች፣ ከፍንጣሪ ነገሮች ወ.ዘ.ተ) ለመጠበቅ የሚያገለግሉ መነፅሮች ሲሆኑ ለግንባታ ሰራተኞች፣ ላብራቶሪ፣ ፋብሪካ፣ ኢንዱስትሪ ሰራተኞች በዋናነት ያገለግላሉ፡፡

6. የስፖርት መነጽሮች (Sports Eye Glasses)

በስፓርት ጊዜ ዓይንን ከጉዳት ለመጠበቅ የሚያገለግሉ ጠንካራ መነፅሮች ሲሆኑ አትሌቶች፣ ኳስ ተጫዋቾች ፣ዋናተኞች የሚጠቀሙዋቸዉ ናቸዉ፡፡

7. የፀሐይ (Sunglasses) እና ፎቶክሮማቲክ መነጽሮች (Photochromic eye Glasses)

እነዚህ መነፅሮች ጎጂ (UV) ጨረርን ለመከላከል የሚረዱ መነፅሮች ሲሆኑ ሁሉም ሰዉ በተለይ ፀሀያማ አካባቢዎች የሚኖሩ እንዲጠቀሟቸዉ ይመከራል፡፡

👉 በሀኪም ያልታዘዘ ወይም የሌላ ሰው መነፅር መጠቀም የሚያመጣዉ ጉዳት

▪ አጣርቶ ማየት አለመቻል
▪ የዓይን ድካም እና መዛል
▪ ራስ ምታት፣ማቅለሽለሽ
▪የአንገት እና የትከሻ ህመም
▪ የእይታ ችግሩ መባባስ
▪በህፃናት ላይ ደግሞ የእይታ እድገትን ያስተጓጉላል፣ አይን ሰነፍ ያደርጋል።

“ሁልጊዜም በሀኪም የታዘዘ መነፅር ብቻ ይጠቀሙ!!!”

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6VAB

የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ የሰው ሃብት ቢሮ በተወሰኑ የስራ መደቦች ላይ የሰው ሃይል ስምሪት እንዲፈፀም መፍቀዱን አሳውቋል። የጤና ተቋም ሰራተኞችን ስምሪት እንደሚጨምርም በዝርዝሩ አመላክቷል።
18/01/2026

የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ የሰው ሃብት ቢሮ በተወሰኑ የስራ መደቦች ላይ የሰው ሃይል ስምሪት እንዲፈፀም መፍቀዱን አሳውቋል። የጤና ተቋም ሰራተኞችን ስምሪት እንደሚጨምርም በዝርዝሩ አመላክቷል።

ህዳሴ ጤና ጣቢያ ላይ የተጠናቀቀ የማስፋፊያ ግንባታ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ።=====================09/05/2018ዓ.ም (የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ)ህዳ...
17/01/2026

ህዳሴ ጤና ጣቢያ ላይ የተጠናቀቀ የማስፋፊያ ግንባታ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ።
=====================
09/05/2018ዓ.ም
(የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ)

ህዳሴ ጤና ጣቢያ በደብረ ማርቆስ ከተማ ከ2001ዓ.ም ጀምሮ ለህብረተሰቡ የጤና አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም ነው።

በጊዜ ሂደት ተቋሙ ጥገና እና ማስፋፊያ ግንባታ ያስፈለገው በመሆኑ እና የተጀመሩ ግንባታዎች (ካርድ ክፍል እና መፀ/ቤት) በወቅቱ ባለመጠናቀቃቸው በተቋሙ የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ እንቅፋት ሁኖ ቆይቷል።

በ2017 በጀት አመት የተጀመሩ ግንባታዎችን ለማጠናቀቅ ከአልማ እና ህብረተሰብ ተሳትፎ 1,000,000ብር ተመድቦ ስራውን የሚያሰራ አሰሪ ኮሚቴ በማቋቋም ወደ ስራ ተገብቷል።

ስራውን በተቋቋመው አሰሪ ኮሚቴ እና በጤና ጣቢያው ሰራተኞች ትብብር ከተቀመጠለት ጊዜ ቀድሞ የአይነት እና ጉልበት ወጭውን ሳይጨምር በ510,000ብር በመጨረስ አስረክቧል።

በተነሳሽነቱ የቀጠለው አሰሪ ኮሚቴ በተረፈው 410,000ብር ተጨማሪ ባለሶስት ክፍል ለማስገንባት አስፈቅዶ ስራውን ጀመረ፤ በ2018 በጀት አመት የከተማ አስተዳደሩ 700,000ብር በመመደብ ግንባታው በተያዘለት ጊዜ እንዲያልቅ በማድረግ በቀን 09/05/2018ዓ.ም አሰሪ ኮሚቴው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን መርቆ አስረክቧል።

ጤና ጣቢያው ላይ ከዚህ ግንባታ ተጨማሪ የውስጥ ለውስጥ ስራዎችን በመስራት ውብ እና ፅዱ ማድረግ ተችሏል።

በርክክቡ ወቅት የተገኙት አቶ አበባው ግዛቸው (የአልማ ሰብሳቢ) ስራውን በተመጣጣኝ ወጭ እና በአጭር ጊዜ ማጠናቀቅ በመቻሉ አሰሪ ኮሚቴውን፣ የጤና ጣቢያውን ማኔጅመንት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት አመስግነዋል፤ በቀጣይም ይህን ተሞክሮ በመቀመር ተቋሙ ላይ ተጨማሪ ማስፋፊያ ግንባታዎችን በመስራት አገልግሎቶችን ማስፋት እንደሚገባ አሳስበዋል።

Address

Ethiopia, Amhara Region
Debra Markos

Telephone

+251587711940

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Markos city administration health office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Debre Markos city administration health office:

Share