Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital Laboratory

Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital Laboratory Debre brhan Comprehensive Specialized Hospital Laboratory Wish to give accurate Confidential Informa

Debre birhan Comprehensive Specialized Hospital is governmental Hospital under health Minister of Ethiopia, Amhara Region, which establish during Italian Invasion, in 1929 EC

ሆስፒታሉ ከወረቀት ንክኪ ነፃ የሆነ የህክምና ካርድ አገልግሎት በይፋ አስጀመረደብረብርሃን፤ሚያዚያ15/2017 ዓ.ም ፡-የደብረብርሃን ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ  ሆስፒታል ከወረቀት ንክኪ ነፃ...
24/04/2025

ሆስፒታሉ ከወረቀት ንክኪ ነፃ የሆነ የህክምና ካርድ አገልግሎት በይፋ አስጀመረ

ደብረብርሃን፤ሚያዚያ15/2017 ዓ.ም ፡-
የደብረብርሃን ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከወረቀት ንክኪ ነፃ የሆነ የህክምና ካርድ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አስታውቋል፡፡

አገልግሎቱን የደብረብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ የተከበሩ በድሉ ውብሸት ያስጀመሩት ሲሆን በመርሀ ግብሩ ላይ የክልል፣የከተማ፣የህብረተሰብ ተወካዮች፣የሆስፒታሉ የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተግኝተዋል።

የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጥላሁን ሙሉጌታ እንደገለጹት ሆስፒታላቸው ከወረቀት ንክኪ ነፃ የሆነ የህክምና ካርድ አገልግሎት ለመስጠት ሰፊ ቅድመ ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቶ ዛሬ በአውቶሜሽን ሙሉ በሙሉ ስራ ማስጀመሩን አንስተዋል፡፡

ስራው በቴክኖሎጂ መደገፉ ለታካሚዎች፣፣ለባለሙያዎችና ለሆስፒታሉ ጥቅሙ ከፍያለ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ረጂም የካርድ ሰልፍ የሚያስቀር፣የታካሚዎችን የቆይታ ጊዜ የሚያሳጥርና የካርድ ጠፋብኝ ቅሬታን የሚያስቀር እንዲሁም የተገልጋዮችን እርካታ የሚጨምር መሆኑን ለአብነት አብራርተዋል፡፡

ሲስተሙ ተቋማቸው በየዓመቱ ለህትመት የሚያወጣውን ወጪ ከመቀነሱም በላይ ተወዳዳሪ የጤና ተቋም ለመፍጠር እንደሚያስችለውም ጠቁመዋል፡

ሆስፒታሉ በ2016 ዓ.ም ብቻ ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ ለህትመት ማውጣቱን ጠቁመዋል።

ወደ ስራ የገባው አዲሱ ቴክኖሎጂ ከ23 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሆነበት መሆኑን ጠቅሰው በጤና ሚንስቴር፣በክልሉ ጤና ቢሮ፣በዶክተር ድረሴ እና በሆስፒታሉ መሸፈኑን አስታውቀዋል።

የደብረብርሃን ከተማ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በቀለ ገብሬ በበኩላቸው እንደገለጹት ሆስፒታሉ ከወረቀት ንክኪ ሙሉ በሙሉ ነፃ የሆነ የህክምና አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ለደብረብርሃን፣ለሰሜን ሸዋ ዞንና እና ለአጎራባች ክልል ህዝብ ትልቅ ብስራትና ጠቀሜታውም ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል።

ቴክኖሎጂው ካርድ ለማውጣት የሚወስደውን ጊዜ በመቀነስ፣እንግልትን በማስቀረት፣የሠራተኛውን የስራ ጫና በማቅለል ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ፋይዳው ከፍተኛ ነው ብለዋል።

ከወረቀት ንክኪ የህክምና አገልግሎት በደብረብርሃን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መጀመሩ ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል።

በከተማው በሚገኙ በሁሉም ጤና ተቋማት ለመተግበር እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

የደብረብርሃን ከተማ ስማርት ሲቲ ዕቅድ ይኽ ዓይነት የዲጂታላይዜሽን ትግበራ ስራውን እንደሚያፋጥነው አመልክተዋል።

ስራው እንዲሳካ በማስተባበር ተቋማቸውና በየደረጃው የሚመለከታቸው አካላት ላበረከቱት አስተዋጽኦ፣እንዲሁም የሙያና የግብዓት ድጋፍ ያደረጉ ተቋማትንና ግለሰቦች አመስግነዋል።

የደብረብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባና የሆስፒታሉ የቦርድ ሰብሳቢ የተከበሩ በድሉ ውብሸት እንደተናገሩት ዲጂታላይዜሽን አገልግሎት አሰጣጥ በማቀላጠፍ የመልካም አስተዳደር ችግር መፍቻ አንዱ መሳሪያ መሆኑን አንስተዋል።

ዘመኑ የሚጠይቀውን በቴክኖሎጂ ተደግፎ ፈጣንና ቀልጣፋ የህክምና አገልግሎት ለህብረተሰቡ መስጠት መቻል ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል።

ጤና ጣቢያዎችና ሆስፒታሎች ወደ ዲጂታል ቴክኖሎጂ መግባታቸው ተገቢና አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው ስራው ወደፊትም ውጤታማ ሆኖ እንዲዘልቅ ሁሉም የየድርሻውን ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ ከንቲባ በድሉ አሳስበዋል።

ስራው በውጤታማነት እንዲጠናቀቅ ያደረጉ አካላትን ሁሉ አመስግነዋል።
Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital
Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital Laboratory

17/04/2025
17/04/2025

With Amhara Public Health Institute/APHI/ – I'm on a streak! I've been a top fan for 5 months in a row. 🎉

28/03/2025

With Amhara Public Health Institute/APHI/ – I'm on a streak! I've been a top fan for 4 months in a row. 🎉

18/03/2025

የብቃት ምዘና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
___________

ጤና ሚኒስቴር በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተና ለመፈተን በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ የጤና ባለሙያዎች የፈተና ምዝገባው ከየካቲት 24 - መጋቢት 07/2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ መግለፃችን ይታወሳል። ነገር ግን አንዳንድ ተመራቂዎች የቴምፖራሪ ዲግሪ ያልደረሰላቸው መሆኑንና ምዝገባው እንዲራዘምላቸው በተደጋጋሚ መጠየቃቸው ይታወቃል። ስለሆነም ምዝገባው እስከ መጋቢት 10/2017 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን እየገለጽን ለምዝገባው ቴምፖራሪ ዲግሪ መያዝ ግዴታ መሆኑን እናሳስባለን።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: https://t.me/M0H_EThiopia

13/02/2025

ከደብረ ብርሃን ደም ባንክ ጋር በመተባበር የደም ልገሳ ፕሮግራም በሆስፒታሉ ግቢ እየተካሄደ ይገኛል ።
ደም በመለገስ ህይወት እንዲያድኑ ተጋብዘዋል።

አስደሳች ዜና ለመላዉ ህብረተስብ በሙሉ፦ የደብረ ብርሃን ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከcure blindness project(CBP) ከሚባል ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ከመጋቢት...
13/02/2025

አስደሳች ዜና

ለመላዉ ህብረተስብ በሙሉ፦

የደብረ ብርሃን ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከcure blindness project(CBP) ከሚባል ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ከመጋቢት 22-27/017 ዓም ድረስ ለተከታታይ ስድስት ቀናት የሚቆይ የነጻ የአይን ሞራ ግርዶሽ እና የአይን ቆብ ቅንደላ ህክምና ስለሚያካሂድ የህክምናዉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከዉዲሁ መልእክታችንን እያስተላለፍን በተቀመጠው ልየታ ፕሮግራም በቀጣይ የሚሰራ ይሆናል፡፡

06/06/2017
ደብረ ብርሃን

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል አደረሳችሁ በዓሉ የሠላም ; የጤና እንዲሆንላችሁ እንመኛለን ።መልካም የገና በዓል
06/01/2025

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ
እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል አደረሳችሁ
በዓሉ የሠላም ; የጤና እንዲሆንላችሁ እንመኛለን ።
መልካም የገና በዓል

የደብረ ብርሃን ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ማኔጅመንት ለላቦራቶሪ አገልግሎት ዲፓርትመንት እና ሠራተኞች  የእውቅና እና የምስጋና ፕሮግራም አካሄደ ህዳር 18/2017 ደብ ላብራቶሪ ዲ...
28/11/2024

የደብረ ብርሃን ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ማኔጅመንት ለላቦራቶሪ አገልግሎት ዲፓርትመንት እና ሠራተኞች የእውቅና እና የምስጋና ፕሮግራም አካሄደ
ህዳር 18/2017
ደብ
ላብራቶሪ ዲፓርትመንቱ በ ISO 15189 አለም አቀፍ ስታንዳርድ በጅን ኤክስፐርት የቲቢ ምርመራ አክሪዲቴሽን እውቅና በማግኘቱ እና በአማራ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባዘጋጀው 3ኛው ክልላዊ የላቦራቶሪ ፌስታል የሠርተፊኬትና ዋንጫ 🏆 ተሸላሚ በመሆኑ ሆስፒታሉ ለላቦራቶሪ ባለሙያዎች የምስጋና ፕሮግራም እና ውይይት አካሂዷል ። በውይይቱ ባለሙያዎች ; ማኔጅመንት አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው የሆስፒታሉ ሠራተኞች ተገኝተዋል ።
ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የሆስፒታሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አስማረ ሣሙኤል በዚህ አስቸጋሪ ወቅት የተሻለ አፈጻጸም በማምጣቱ ለሠራተኞች እና ድጋፍ ላደረጉ አጋር አካላት ምስጋና አቅርበው በቀጣይ ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት መስራት ; ቀጣይነት እንዲኖረው ማድረግ እና እውቅናውን ወደ ሌሎች ምርመራዎች ማስፋት እንዳለብን አሳስበው ማኔጅመንቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እና ክትትል ያደርጋል ብለዋል።
የውይይት መነሻ ሀሳብ ያቀረቡት የዲፖርትመንቱ አስተባባሪ አቶ ጌታው አለማየሁ በ2016 የነበሩ ዋና ዋና ተግባራት ; በአክሪዲቴሽን ወቅት የነበሩ አሠራሮች ; እንዲሁ ከላብራቶሪው ምን ይጠበቃል በሚል የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫ አቅርበዋል ።
በውይይቱ የተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ
ስለነበራቸው አስዋጽኦ ለሠራተኞች የምስክር ወረቀት የተሠጠ ሲሆን ለአጋር አካላት ምስጋና ቀርቧል።

በድጋሚ ከጎናቸው በመሆን ድጋፍ ላደረጋችሁት ሁሉ እናመሠግናለን

"" ጥራት ያለው የላቦራቶሪ አገልግሎት ለተሻለ ህክምና "

የደብረ ብርሃን ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ላብራቶሪ በ3ኛው ክልል አቀፍ የላቦራቶሪ ፌስቲባል ላይ እውቅና ተሰጠው። ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ በተካሄደው 3ኛው ክ...
10/11/2024

የደብረ ብርሃን ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ላብራቶሪ በ3ኛው ክልል አቀፍ የላቦራቶሪ ፌስቲባል ላይ እውቅና ተሰጠው።

ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም
በባህር ዳር ከተማ በተካሄደው 3ኛው ክልላዊ የላቦራቶሪ ፌስቲቫል ሆስፒታሉ በ2016 ዓ.ም ላስመዘገበው የISO 15189:2012፤ የቲቢ ጅን ኤክስፐርት (Gene Xpert MTB RIF assay) ምርመራ accreditation የዋንጫ እና የሠርተፊኬት ሽልማት ከአማራ ህብተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ተሰጠው።

ለዚህ ውጤት መምጣ የበኩላችሁን አስተዋፅዖ ላበረከታችሁ ። የሆስፒታሉ የማኔጅመንት አባላት፣ የላቦራቶሪ ባለሙያዎች፣ የደብ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ አመራሮች ፣ APHI ፤ EPHI እና ሌሎችም በሆስፒታሉ ስም እያመሠገንን
እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን።
Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital Laboratory

(Getaw Alemayehu )

09/11/2024

Address

Debre Birhan Shewa
Debre Birhan
08

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital Laboratory posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital Laboratory:

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram