Dejen Ketema Communication Office

Dejen Ketema Communication Office Serving communication service to the public

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና መሰጠት ተጀመረ።ሐምሌ 25/2015 ዓ.ም  የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በሁሉም የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ...
01/08/2023

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና መሰጠት ተጀመረ።
ሐምሌ 25/2015 ዓ.ም
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በሁሉም የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መሰጠት ተጀመረ።
በዛሬው ዕለት የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናቸውን እየወሰዱ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
#አሚኮ

"በወቅታዊ ሰላምና የጸጥታ ላይ የጋራ አረዳድ በመፍጠር የተጀመረው የሠላምና የልማት ሂደቱ እንዲጠናከር መሥራት ይገባል" ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር)ባሕር ዳር: ሐምሌ 25/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ...
01/08/2023

"በወቅታዊ ሰላምና የጸጥታ ላይ የጋራ አረዳድ በመፍጠር የተጀመረው የሠላምና የልማት ሂደቱ እንዲጠናከር መሥራት ይገባል" ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር)
ባሕር ዳር: ሐምሌ 25/2015 ዓ.ም (አሚኮ) ከአማራ ክልል የተወጣጡ የሃይማኖት አባቶች እና የአገር ሽማግሌዎች ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር እየተደረገ ነው፡፡
ከአማራ ክልል ከሁሉም ዞኖች የተወጣጡ የሃይማኖት አባቶች እና የአገር ሽማግሌዎች በወቅታዊ ሀገራዊና ክልላዊ ፖለቲካዊ ሁኔታዎች እንዲሁም በሠላምና ፀጥታ አዝማሚያዎች ላይ በባህር ዳር ከተማ እየመከሩ ነው።
ክልላዊ ወቅታዊ ፖለቲካዊ አዝማሚያዎችን እና የሠላምና የጸጥታ ሁኔታዎችን አመላካች መነሻ ሀሳብ በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) ቀርቧል።
የውይይት መድረኩ በወቅታዊ የሰላምና የጸጥታ ሁኔታዎችና አዝማሚያዎች ላይ የጋራ አረዳድ በመፍጠር የተጀመረው የሠላምና የልማት ሂደቱ እንዲጠናከር ፋይዳዉ የጎላ መሆኑ መሆኑ ተገልጿል።
በሰላም እና በውይይት እንጂ በጦር መሳሪያ የተፈታ ችግር አለመኖሩ የተገለጸ ሲሆን የአማራ ክልል ሕዝብ ጦርነት ሳይሆን ልማት የሚሻ ሕዝብ በመሆኑ ልማቱን ይበልጥ በማተኮር የሕዝቡት ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባልም ተብሏል።
Amhara Communications

ላይፍ ላይን አካዳሚ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት መስጠት ጀመረ ፡፡ **********************************************ደጀን ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ሀምሌ 19/2015 ዓ/...
26/07/2023

ላይፍ ላይን አካዳሚ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት መስጠት ጀመረ ፡፡
**********************************************
ደጀን ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ሀምሌ 19/2015 ዓ/ም
በደጀን ከተማ የተለያዩ ቅርንጫፎችን ከፍቶ የቅድመ መደበኛ ትምርት በመስጠት ላይ የሚገኘው ላይፍ ላይን አካዳሚ በ2015 በጀት ዓመት ሲያስተምራቸው የነበሩ ወ 40 ሴ 38 ድ 78 ቅድመ መደበኛ ተማሪዎችን በማስመረቅ ለመደበኛ ትምህርት ዝግጁ ማድረግ ችሎል ፡፡
አካዳሚው ለ17 ስራ ፈላጊዎች የስራ እድል ከመፍጠሩም ባሻገር በከተማዋ ሶስት ቅርንጫፎችን በመክፈት የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ከህፃናት እንጀምር የሚል መፈክርን አንግቦ የሚንቀሳቀሰው አካዳሚው በየአመቱ አቅም ላጡ እና ለድሀ ድሀ ህፃናት ነፃ የትምህርት እድል ከመስጠቱም ባሻገር ባለሁብቶችን በማስተባበር የአቅም ችግር ላለባቸው ህፃናት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እንዲያገኙ ያደርጋል በ20/15 የትምህርት ዘመን ለ16 ህፃናት ነፃ የትምህርት እድል መስጠቱን የገለፁልን የትምህርት ቤቱ ስራ አስኪያጅና ባለቤት አቶ ደስአለኝ ሙሉጌታ ናቸው ፡፡
አካዳሚው ከተመሰረተ 15 ዓመታትን ያስቆጠረ አንጋፋ አካዳሚ ሲሆን በርካታ ጎበዝና ጠንካራ በስነ ምግባር የታነፁ ተማሪዎችን ለቅድመ መደበኛ ዝግጁ አድርጓል ፡፡
ለ2016 ዓ/ም ተማሪዎችን ለትምህርት ዝግጁ ለማድረግ እና የእረፍት ሰዓታቸውን በዋዛ ፈዛዛ እንዳያሳልፉ በማለት የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቆ በማስተማር ላይ እንደሚገኝ የገለጹልን አቶ ደስአለኝ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል የሚገኙ ተማሪዎችን በቋንቋ ፣የአብነት ትምህርት እንዲሁም የህፃናት ማዋያን ጨምሮ በክረምቱ ወራት እንደሚሰጡ አቶ ደስአለኝ ተናግረዋል ፡፡
በመሆኑም በክረምቱ ወራት ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት በማምጣት እውቀት እንዲቀስሙ ማድረግ የወላጆች ሀላፊነት ሊሆን ይገባል ያሉት አቶ ደስአለኝ በ2016 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ከመደበኛ ትምህርት ባሻገር የአብነትና ግዕዝ ትምህርትንም በተጨማሪ መስጠት እንደሚጀምር እና ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል በመደበኛ ትምህርት ዕውቅና በመውሰድ ተማሪዎችን ለመቀበል ቅድመ ዝግጅቱን በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝና በቀጣይ ዓመት ከ1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል ትምህርት መስጠት እንደሚጀምር ገልፀዋል ፡፡
ለህፃናት ሁለንተናዊ ለውጥ ወላጆችና መምህራን ወሳኝ ናቸው ፡፡
ላይፍ ላይን አካዳሚ

ከአድማስ ባሻገር የመንግስት ሰራተኞች ንግድ ስራ አክስዮን ማህበር የመመስረቻ ጉባዔውን በማካሄድ ላይ ነው።*******ሐምሌ 18/2015ዓ.ም (ምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሙዩኒኬሽን) በምስራቅ ጎጃም...
25/07/2023

ከአድማስ ባሻገር የመንግስት ሰራተኞች ንግድ ስራ አክስዮን ማህበር የመመስረቻ ጉባዔውን በማካሄድ ላይ ነው።
*******
ሐምሌ 18/2015ዓ.ም (ምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሙዩኒኬሽን) በምስራቅ ጎጃም ዞን የመንግስት ሰራተኞች የተቋቋመው ከአድማስ ባሻገር የመንግስት ሰራተኞች ንግድ ስራ አክስዮን ማህበር የመመስረቻ ጉባዔውን በማካሄድ ላይ ነው።
በምስረታ ጉባዔው ላይ የተገኙት የምስራቅ ጎጃም ዞን ብልጽግና ፓርቲ የፓለቲካ ዘርፍና ርዕዮተ ዓለም ግንባታ ዘርፍ ኀላፊ ወ/ሮ አትክልት አሳቤ አክሲዮን ማህበሩ በአጭር ጊዜ ተቋቁሞ በአጭር ጊዜ የመመስረቻ ጉባዔ ላይ እንዲደርስ ርብርብ ያደረጉ የመስራች ኮሚቴ አባላትን ጨምሮ ሌሎች የስራ ኀላፊዎችን ፣ተቋማትንና የአክሲዮን ማህበሩ አባላትን አመስግነዋል።
ከአድማስ ባሻገር የመንግስት ሰራተኞች ንግድ ስራ አክስዮን ማህበር በቀጣይ በሚሰማራበት ዘርፍ ውጤታማ ስራ በመስራት አባላቶቹን ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር የአካቢቢውን ኢኮኖሚ ለማሻሻል በትኩረት መስራት እንደሚገባ የተናገሩት ወ/ሮ አትክልት አክሲዮን ማህበሩ በስራ ሂደት የሚገጥሙት ችግሮች ለመፍታት በትኩረት እንደሚሰራ ጨምረው ገልፀዋል።
ከአድማስ ባሻገር የመንግስት ሰራተኞች ንግድ ስራ አክስዮን ማህበር የመስራች ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ መንግስቱ በለይ አክሲዮን ማህበሩ የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ እቅድ በማቀድ የኑሮ ውድነቱን ሊያረጋጉ በሚችሉ ውጤታማ ዘርፎች በመሰማራት አባላቱንና የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ ይሰራል ብለዋል።
አክሲዮን ማህበሩ በ618 ዓባላት መቋቋሙን የተናገሩት አቶ መንግስት በ23 ሽህ እጣዎች መቋቋሙን የኮሚቴው ሰብሳቢ ጨምረው ተናግረዋል።
የመመስረቻ ጉባዔውን እያካሄደ የሚገኘው ከአድማስ ባሻገር የመንግስት ሰራተኞች ንግድ ስራ አክስዮን ማህበር በጉባዔው የቦርድ አባላትን የማካሄድ ፣የአክስዮን የመመስረቻ ጽሁፉን የማጽደቅና በሌሎች ጉባዔዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል ።
በጉበዔው ላይ የአክስዮን ማህበሩ አባላት ፣ የፋይናንስ ተቋማትና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈውበታል።
East Gojjam Communication

በምስራቅ ጎጃም ዞን በትምህርት ዘርፉ ባለፉት ሁለትና ሶስት አመታት በተሰራ ውጤታማ ስራ አበረታች ውጤቶች ተመዝግቧል፡፡ባለፉት ሁለት አመታት በ1 ቢሊዬን 100 ሚሊዬን 259 ሽ 845 ብር በ...
19/07/2023

በምስራቅ ጎጃም ዞን በትምህርት ዘርፉ ባለፉት ሁለትና ሶስት አመታት በተሰራ ውጤታማ ስራ አበረታች ውጤቶች ተመዝግቧል፡፡
ባለፉት ሁለት አመታት በ1 ቢሊዬን 100 ሚሊዬን 259 ሽ 845 ብር በሚሆን ወጭ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች፣ መማሪያ ክፍሎች፣ ቤተ መጻህፍት፣ ቤተ ሙከራዎች ተገንብተዋል፡፡
መምሪያው የዚህ አመት የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ከፍተኛ ውጤት እንዲያስመዘግቡ አልሞ እየሰራ ነው፡፡
ሀገር በትውልድ፤ ትውልድ ደግሞ በትምህርት ይገነባል። ስለሆነም ለአንድ ሃገር እድገት ትምህርት የማይተካ ሚና አለው፡፡ ምክንያቱም ያለ ትምህርት የእድገት ማማ ላይ የወጣ ሃገር የለምና፡፡
የሃገራችን ትምህርት በበርካታ ምክንያቶች የቁልቅለት ጉዞ በመሄድ ላይ እንደ ነበር መናገር ለቀባሪ ማርዳት ነው፡፡
በመሆኑም የምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳደር የዞኑ ትምህርት እየሄደበታ ካለው እጅግ አደገኛ የቁልቁለት ጉዞ በመግታት ወደ ነበረበት ከፍታ ለመመለስና ችግሮቹ እንዲፈቱና ትምህርት ቤቶች ያሉባቸው መሰረታዊ ችግሮች እንዲፈቱ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ነው፡፡
ላለፉት አመታት በትምህርት ዘርፉ የተፈጠረውን መቀዛቀዝ በማነቃቃት ወደ ስራ ለማስገባት በርካታ የምክክር መድረኮችን ከአጋርና ባለድርሻ አካላት እንዲሁም ከሙያው ባለቤቶች ጋር በመፍጠር ችግሮችን የመለየትና በሚስተካከሉበት መንገድ መግባባት ተደርሷል፡፡ በዚህም በርካታ ውጤት ተመዝግበዋል፡፡
© በተፈጠረውን የንቅናቄ መድረክ ተከትሎ የትምህርት ቤቶች ደረጃ እንዲሻሻል ተደርጓል፡፡ ለአብነት፡-
~ በበጀት ዓመቱ 45 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች ደረጃ አንድ የነበሩ ሲሆን በተሰራዉ ስራ 29 ት/ቤቶች የደረጃ ሽግግር ማድረግ ችሏል፤
~ 36 ት/ቤቶች ወደ ደረጃ 3 እንዲሸጋገሩ አድርገናል፡፡
~ የት/ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል የነበረዉ የስራ ትጋት እጅግ አበረታች ነበር፤
~ 7 የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ወደ ደረጃ 3 እንዲገቡ አድርገናል፤
© የተናበበና የተቋሙን ችግር በራሱ አቅም ሊፈታ የሚችል ተቋም እየተገነባ ነው፤
© እያንዳንዱን ት/ቤትና ወረዳ ብሎም ዞኑን የመልካም ተሞክሮዎች መፍለቂያ ማዕከል እየሆነ ነው፤
© የትምህርት ውስጣዊ ብቃት ችግሮችን መፍታት ተችሏል፡፡
© በዘርፉ የተሰማሩ አካላት መነቃቃት ተፈጥሯል፡፡
© በዞኑ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ በአንድ ጀምበር ተማሪን የመመዝገብ ስራ በመፈጸም ግንባር ቀድም ዞን ሆኗል፡፡
© የተማሪዎች የነፍስ ወከፍ ገቢ 100 ፕርሰንት መመደብ ተችሏል፡፡
ትምህርት ቤቶች ውብና ማራኪ እንዲሆኑ ለማድረግና በተማሪ መማሪያ ክፍል ጥምርታ ማለትም የመማሪያ ክፍል እጥረት ምክንያት የነበረውን ችግር ለመቅረፍ በዚህ ሁለት አመት መሰረታዊ ለውጦች ተመዝግበዋል፡፡
በምስራቅ ጎጃም ዞን በ78 ትምህርት ቤቶች 78 ብሎክ 335 የመማሪያ ክፍሎች በ181 ሚሊዬን 498ሽ 481ብር በ2013 ዓ.ም ግንባታቸው ተጀምሮ በ2014 ዓ.ም ተጠናቀው ለአገልግሎት ውለዋል፡፡ የእነዚህ መማሪያ ክፍሎች መገንባት ከ16570 አዲስ ተማሪዎች የመማር እድል እንዲያገኙ ማድረግ ተችሏል፡፡ በተጨማሪም በ10 ሚሊዬን 155ሽ 000 ብር ቤተመጽሐፍት፤ ቤተሙከራ እና መጸዳጃ ቤት በመገንባት ለአገልግሎት ማዋል ተችሏል፡፡
በተመሳሳይ በ2014 በጀት አመት በዞኑ ያለውን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ችግር ለመቅረፍ 4 ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች በመገንባትና እንዲጠናቀቁ በማድረግ በዚህ አመት በአዲስ ስራ እንዲጀምሩ ማድረግ ተችሏል፡፡
በ2015 የትምህርት ዘመን መምሪያው ባካሄደው የንቅናቄ መድረክ በተደራጀና በከፍተኛ የህዝብ ንቅናቄ የትምህርት ቤቶችን ገጽታ ለመቀየር በእጅጉ ውጤታማ ስራ ተሰርቷል፡፡ ለአብነት ዞኑ በአንድ ትምህርት ቤት አንድ ብሎክ በሚል መሪ ቃል አቅዶ ለመስራት ባደረገው ጥረት በ2015 የትምህርት ዘመን በ441 ሚሊዬን 238ሽ 124 ብር 45 ሳንቲም በሆነ ወጭ በ140 ት/ቤት 208 ብሎክ እና 620 መማሪያ ክፍሎች ተገንብተዋል፡፡
መምሪያው የህብረተሰቡን እምቅ አቅም በመጠቀም በትምህርት ዘርፍ ያለውን ችግር ለመቅረፍ እቅድ አቅዶ ውጤታማ ስራ እየሰራ ነው፡፡ በ2015 በጀት አመት የትምህርት ዘመን በህብረተሰቡ ተሳትፎ በጥሬ ገንዘብ፣ በቁሳቁስ፣ በጉልበት በድምር 545 ሚሊዮን 319ሽ 743 ብር በመሰብሰብ የእቅዱን 189.7 %በማሳካት የትምህርት ቤቶችን ገጽታ በመቀየርና ቸግሮቹን በመፍታት የህብረተሰቡ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት ጥረት ተደርጓል፡፡
በትምህርት ዘርፍ ላይ የሚሰራው ስራ ውጤቱን በአጭር ጊዜ ለማየት ከባድ ቢሆንም የ8ኛና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የተሸለ ውጤት እንዲያመጡ ለማስቻል በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ ለአብነት
- ተማሪዎችን በትርፍ ጊዚያቸው እስከ ምሽቱ ድረስ ለሚያግዙ መምህራን ከ3.47 ሚሊዬን ብር በላይ ተመድቦ አገልግሎት ላይ ውሏል፡፡
- ቤተ መጻፍቶቹ ሳምንቱን ሙሉ እስከ ምሽቱ አራት ሰዓት ክፍት እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡
- ሞዴል ፈተና በዞንና በክልል ወጥቶ እንዲፈተኑ ተደርጓል፡፡
በመጭው ሃምሌ 19 /2015 የዞኑ 60 ትምህርት ቤቶች 24,518 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ያስፈትናል፡፡
የምስራቅ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ ለተፈታኝ ተማሪዎች መልካም እድል ይመኛል፡፡
East Gojjam Communication

ባለፉት አራት አመታት ለምስራቅ ጎጃም ዞን ለመንገድ ዘርፍ ከህዝብና ከመንግስት በተመደበ 5 ቢሊዬን 957ሚሊዬን፣ 819ሽ 367 ብር በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡የምስራቅ ጎጃም ዞን ትርፍ አ...
18/07/2023

ባለፉት አራት አመታት ለምስራቅ ጎጃም ዞን ለመንገድ ዘርፍ ከህዝብና ከመንግስት በተመደበ 5 ቢሊዬን 957ሚሊዬን፣ 819ሽ 367 ብር በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡
የምስራቅ ጎጃም ዞን ትርፍ አምራች ዞን ቢሆንም ቀበሌን ከቀበሌ የሚያገናኙ መንገዶች በተገቢው ያልተሟሉለት፣ ደረጃውን የጠበቀ አስፋልት በበቂ ሁኔታ ያልተገነባበት ዞን መሆኑን መግለጽ ለቀባሪ ማርዳት ነው፡፡
ይሁን እንጅ የህዝቡንና የወረዳ አስተዳደሩን አቅም በመጠቀም ችግሮችን ለመፍታት ጥረት በማድረግ የመንገድ ይገንባልን ጥያቄ እስከ ፌደራል ድረስ በማቅረብ መልስ እየተሰጠ ስራዎች እየተሰሩ ነው፡፡
ለአብነት በመንገድ ዘርፍ የነበረውን ችግር ለመፍታት ከ2011 እስከ 2015 የተሰሩትን ስራዎች በአብነት ለማንሳት ያህል፦
©ከአስፋልት መንገድ አኳያ👇
~ከደብረ ማርቆስ
-ደብረኤልያስ-ቁጭ-አየሁ-ዚገም 81.9 ኪ.ሜትር
~ ከሞጣ-ጃራገዶ-እስቴ 58 ኪ.ሜትር ያለዉ መንገድ በተቋራጭ ችግር ምክንያት የተቋረጠ ሲሆን ቀሪ ስራዉን ለማስጨረስ እየተሰራ ነዉ።
~ ከሞጣ- ስማዳ ዲዛይን እየተሰራለት ያለ 80 ኪ.ሜትር
~ ከደብረማርቆስ -አዲስ አበባ የፍጥነት መንገድ ዲዛይን እየተሰራለት ያለ
~ ከየውላ -ደብረ ኤልያስ 17 ኪ.ሜትር ዲዛይን እየተሰራለት ያለ
~ ከደብረ- ማርቆስ -ድጎ ሞጣ 119 ኪ.ሜትር ውል ተይዞ ወደ ስራ እየተገባ ያለ እና ሌሎችም ውጤታማ ስራዎች እየተሰሩ ነው፡፡ለነዚህ ፕሮጀክቶች 4ቢሊዮነ 544ሚሊዮን 666ሺ 910ብር ለፕሮጀክቶች ስራ ላይ እየዋለ ነዉ።
በሌላ በኩል በክልሉ መንገድ ኤጀንሲ፣ በዩራፕና በኢትዬጵያ መንገዶች አስተዳደር በጀት 👇
© አዲስ መንገድ 391.66
© ከፍተኛ ድልድይ 25
© ተንጠልጣይ ድልድይ 2
© መንገድ ጥገና 1963.29
© ስትራክቸር 308 በ891 ሚሊዬን 990ሽ 960 ብር ከ19 ሳንቲም መገንባት ተችሏል፡፡
በተመሳሳይ ዞኑ በወረዳና በህብረተሰብ ተሳትፎ በአምስት አመቱ ውስጥ 512 ሚሊዬን 675ሽ 950 ብር በመሰብሰብ
© 626.32 ኪ.ሜትር አዲስ መንገድ
© 4012 ኪ.ሜትር መንገድ ጥገና
© 267 አነስተኛ ስትራክቸሮች
© 11 ከ12 ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው ከፍተኛ ድልድዬች በመገንባት ከ57 በላይ ቀበሌዎችን ቀበሌን ከቀበሌና ቀበሌን ከወረዳ ማእከል ጋር ማገናኘት ተችሏል፡፡ በሌላ በኩል ከአሁን በፊት ለተሰሩና ቀጣይ ለሚሰሩ ፕሮጀክቶች 478 ኪ.ሜትር አዲስ መንገድና 11 ድልድዬች ዲዛይን ተሰርቶላቸዋል፡፡
East Gojjam Communication

በምስራቅ ጎጃም ዞን በደጀን ከተማ "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ ተካሄደ ፡፡ በችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ የቀበሌና የከተማ አመራሮች ፣የመንግስት ሰራ...
18/07/2023

በምስራቅ ጎጃም ዞን በደጀን ከተማ "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል የአንድ ጀንበር ችግኝ ተከላ ተካሄደ ፡፡
በችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ የቀበሌና የከተማ አመራሮች ፣የመንግስት ሰራተኞች ፣የወጣት አደረጃጀቶች እና የማህበረሰብ ተወካዮች ተሳትፈዋል ፡፡
ደጀን ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ሀምሌ 11/2015 ዓ/ም

የዓባይ ሸለቆን በረሃማነት ለመከላከል የተጀመረው የቆላ ቀርከሃ ልማት ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው*****የዓባይ ሸለቆን በረሃማነት ለመከላከል በአማራ ክልል ደጀን ወረዳ የተጀመረው የቆላ ቀር...
18/07/2023

የዓባይ ሸለቆን በረሃማነት ለመከላከል የተጀመረው የቆላ ቀርከሃ ልማት ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ ነው
*****
የዓባይ ሸለቆን በረሃማነት ለመከላከል በአማራ ክልል ደጀን ወረዳ የተጀመረው የቆላ ቀርከሃ ልማት ተጨባጭ ውጤት እያስገኘ መሆኑ ተገለጸ። የቀርከሃ ልማቱ የህዳሴ ግድብን ከደለል ለመከላከልም ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተጠቅሷል።
በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር እና በደጀን ወረዳ እየተተገበረ ላለው የቆላ ቀርከሃ ፕሮጀክት የዩኒቨርሲቲው አስተባባሪ አቶ ደምሳቸው ሽታው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የዓባይ ሸለቆ ከፍተኛ የሆነ የበረሃማነት መስፋፋት እየተከሰተ የህዝቡ የኑሩ ሁኔታ እየወረደና የገቢ ምንጫቸው እየቀነሰ መሄዱ፤ ተዳፋት የሆኑ ስፍራዎች ለእርሻ አገልግሎት በመዋላቸውና ይህም አካባቢውን ለጎርፍና የመሬት መንሸራተት አደጋ ተጋላጭ በማድረጉ፤ ጎርፉ በቀጥታ ወደ ዓባይ ወንዝ በመግባት ከፍተኛ ደለል እየፈጠረ በመሆኑ የቆላ ቀርከሃ ልማት በአካባቢው እንዲጀመር ምክንያት ሆኗል። ባለፉት ሦስት ዓመታት ትግበራውም የአካባቢው የደን ሽፋን እንዲጨምር ከማድረግ ጀምሮ ተጨባጭ ለውጥ እየታየ ነው።
ግብርናው የሰብል ምርትና የእንስሳት ሀብትን መጠቀምን ይጠይቃል ያሉት አቶ ደምሳቸው፤ በዚህ ሂደት ብቻ ሰው ከድህነት መውጣት እንደማይችልና የደን ሀብትን በጥምር መጠቀም እንደሚገባ ገልጸዋል። በደጀን ወረዳ ከሦስት ዓመታት በፊት ከኢትዮጵያ ደን ልማት ድርጅት ጋር በመተባበር የተጀመረው የቆላ ቀርከሃ ልማትም ይህንን ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። ምርቱ በአጭር ጊዜ የሚደርስና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ ተመርጦ ተግባራዊ መደረጉንም ተናግረዋል።
ፕሮጀክቱ ከተጀመረ ወዲህ የአካባቢውን ምርታማነት በመቀየር፤ የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል የአፈር መሸርሸርንና ደለልን በመከላከል ረገድ የታለመለትን ዓላማ በትክክል እያሳካ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ለአካባቢው ማህበረሰብ የገቢ ምንጭ ጭምር መሆኑንም ነው አቶ ደምሳቸው የገለጹት።
የህዳሴ ግድብን ከደለል መከላከል ካልተቻለ የሚጠበቀውን አገልግሎት ለማግኘት አስቸጋሪ እንደሆነ በመጠቆም፤ የቀርከሃ ልማቱ ሀገራዊ ፕሮጀክት ለሆነው ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ጭምር ተስፋ የተጣለበት እንደሆነ አቶ ደምሳቸው አመላክተዋል። የዓባይ ሸለቆን ሙሉ ለሙሉ ወደ ደንነት ለመለወጥ በሚደረገው ጥረት ውስጥ የተጀመረው የቀርከሃ ልማት ተጨባጭ ውጤት እያሳየ ይገኛል ነው ያሉት።
የህዝቡን የኑሮ ሁኔታን በማሻሻልና የአካባቢውን የአየር ሁኔታ በመቀየር የታላቁ ህዳሴ ግድብን ከደለል ለመከላከል አማራጭ የሆነው የአግሮ ፎረስት እንቅስቃሴ እንደሆነ ገልጸው፤ ይህም ግብርናን ከደን ሀብት ጋር በማቀናጀት መጠቀም መሆኑንና ይህንን ማድረግ በሚያስችል ሁኔታ የቆላ ቀርከሃ ልማትም በሰፊው ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
በ2013 ዓ.ም ፕሮጀክቱ ሲጀመር 65 ሄክታር በላይ የእርሻ መሬት ላይ እንዲሁም ስድስት ሄክታር በላይ የጋራ የግጦሽ መሬት ላይ የቆላ ቀርከሃ የተተከለ ሲሆን፤ ወደ ፊትም የደን ልማቱን ከማጠናከር ባሻገር ቀርከሃን መሠረት አድርጎ ለተቋቋሙ ፋብሪካዎች የግብዓት ምንጭ እንደሚሆንም ጠቅሰዋል። በህብረተሰቡ ዘንድ በሰፊው ተቀባይነትን እንዲያገኝ ማድረግና ልማቱን የማስፋፋት ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አንስተዋል። ችግኝ በነጻ ለአርሶ አደሮች በመስጠት የማስፋፋት ሥራው ይከናወናል ብለዋል።
ፕሮጀክቱ ሲጀመር ሰፊ ቦታ ለመሸፈን ታቅዶ የነበረ ሲሆን፤ ሆኖም ቀስ በቀስ ከህዝቡ ጋር የማላመድ ሥራ ያስፈልግ ስለነበር በጥቂት ሄክታር ላይ ማስጀመር መቻሉን ገልጸዋል። አካባቢውን ሞዴል የማድረግ ሥራ በመሠራቱ በርካታ ለውጦች መምጣቸውን አስታውቀዋል።
የቀርከሃ ልማት በሀገር አቀፍ ደረጃ ለተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር እንደ አንድ ዘርፈ ብዙ ተክል የአገሪቷን የደን ልማትና የህዝብን ኢኮኖሚ ከማጠናከር አንጻር አዎንታዊ ሚና እንዳለውም አቶ ደምሳቸው ገልጸዋል።
ምንጭ፡- ምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሙየኒኬሽን

"ዛሬ ካልሰራን ነገ ፍሬ መጠበቅ አንችልም!" ዶክተር ይልቃል ከፋለ************በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሐ ግብር  ተካሒዷል...
18/07/2023

"ዛሬ ካልሰራን ነገ ፍሬ መጠበቅ አንችልም!" ዶክተር ይልቃል ከፋለ
************
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሐ ግብር ተካሒዷል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የብልጽግና ፖርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ሌሎች የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በፕሮግራሙ ላይ መልእክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳደር ዶክተር ይልቃል ከፋለ የአረንጓዴ አሻራን ግብ ለማሳካት በአለፉት አራት ዓመታት በርካታ ሥራዎች በመሰራታቸው የተተከሉት ችግኞች ጸድቀዋል፣ በመጽደቃቸውም በአካባቢ በሥነ ምሕዳር ላይ ለውጥ አምጠተዋል ብለዋል፡፡
ነገን ዛሬ እንትከል ለአማራ ክልል ዘርፈ ብዙ መልእክት አለው ያሉት ርእሰ መስተዳደሩ በክልሉ ደረጃ በአንድ ጀንበር 260 ሚሊዮን ችግኞች እንደሚተከሉ ገልጸዋል፡፡
በአንድ ጀምበር ብቻ ተክሎ መተው ሳይሆን ቀጣይነት የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ማድረግ ያስፈልጋል ነው ያሉት ርእሰ መስተዳድሩ፡፡
በአማራ ክልል በተያዘው ክረምት 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ችግኞች እንደሚተከሉ ያነሱት ርእሰ መስተዳድሩ ዛሬ ሳንተክል ነገ ፍሬ መጠበቅ አንችልም፣ ዛሬ መሥራት ዛሬ መትከል አለብን ብለዋል፡፡
ለነገው ትውልድ ዛሬ መስራት ይገባል፤ የበቃና ሀገርን የሚረከብ ትውልድ ለመፍጠር የነገውን ወጣት ዛሬ ላይ ኮትኩተን ማሳደግ አለብን ያሉት ርእሰ መስተዳድሩ።
ርእሰ መስተዳድሩ የነገ ፍላጎታችን መሠረት የሚጣለው ዛሬ ነው፣ የነገ ሰላማችንና ልማታችን የሚመሠረተውም ዛሬ በምንሰራው ስራ ነው ብለዋል፡፡
የሰላም እጦት የሚያመጣው ቀውስ የሚታወቀው ሰላም የታጣ ጊዜ ነው ያሉት ርእሰ መስተዳድሩ የነገው ተስፋችን እንዲለምልም ሰላምን ለማስከበር ሁሉም ባለቤት ሆኖ የራሱን ጥረትና ርብርብ ማድረግ እንዳለበት አንስተዋል።
የሰላም እጦት የሚያመጣው ሰላም የታጣ ጊዜ ነው ያሉት ርእሰ መስተዳድሩ የነገው ተስፋችን እንዲለምልም ሰላምን ለማስከበር ሁሉም ባለቤት ሆኖ የራሱን ጥረትና ርብርብ ማድረግ እንዳለበት ገልጸዋል።
ሰላምን የምናስከብረው በመተባበር እና በአንድነት በመሆኑ ልዩነቶችን ወደ ግጭት ሳይሆን ወደ ውይይት እና ወደ ድርድር ማምጣት እንደሚገባ አንስተዋል፡፡
ዛሬ ላይ ያሉ ልዩነቶችን በውይይት እና በድርድር መፍታት የነገ ተስፋን የለመለመ እንደሚያደርገውም ገልጸው ለነገው ዛሬ መትከል አለብን ሲባል ለችግኝ ብቻ ሳይሆን ለሰላምም ነው ብለዋል
የነገ ልማታችን እና ፍላጎታችን ቀጣይነት እንዲኖረው፣ የተሟላ እንዲሆን ሰላማችን ለማስከበር የጋራ ርብርብ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ የሚያጋጥሙ ችግሮቻችን በተለመደው የባሕል አሰራር መሰረት ለመፍታት ወጣቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪ አስተላልፈዋል።
አንድነት ኃይል ነው፣ በመተባበር እና በአንድነት ከሠራን የማንፈታው ችግር የለምም፤ ችግራችን ለመፍታት በአንድ መቆም እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
Amhara Region President Office
East Gojjam Communication

  !አረንጓዴ ዐሻራ ዛሬ ላይ ሆነን ለመጪው ትውልድ የምናስቀምጠው የህይወት ዘመን አሻራችን ነው። አለምን እያስጨነቃት ያለውን የአየር ንብረት ለውጥን እና የአካባቢ መራቆትን ለመቋቋም የወጠነ...
14/07/2023

!
አረንጓዴ ዐሻራ ዛሬ ላይ ሆነን ለመጪው ትውልድ የምናስቀምጠው የህይወት ዘመን አሻራችን ነው። አለምን እያስጨነቃት ያለውን የአየር ንብረት ለውጥን እና የአካባቢ መራቆትን ለመቋቋም የወጠነ ሀገር በቀል አካሄዳችን ነው።
በሌላ በኩል ብዝሃ ህይወትን ከማስጠበቅ ባሻገር ለምግብ የሚውሉ ዕጽዋትን በመትከል የምግብ ዋስትናችንን የምናረጋግጥበት አንዱ መንገድ ነው።
ለዚህም ኢትዮጵያ ሐምሌ 10 በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ከጫፍ ጫፍ ህዝብን በማነቃነቅ ቅድመ ዝግጅት ጨርሳለች።
ኑ በጋራ እንትከል፣ የነገዋ ኢትዮጵያን እንገንባ !
#አረንጓዴአሻራ


East Gojjam Communication

የመንግሥት ሠራተኞችን የጤና መድኅን ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጅት ማድረጉን ጤና ቢሮ ገለጸ። ሐምሌ 07/2015 ዓ.ም (ምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሙዩኒኬሽን) በአማራ ክልል መደበኛ ባልኾኑ ሥራዎች የተ...
14/07/2023

የመንግሥት ሠራተኞችን የጤና መድኅን ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጅት ማድረጉን ጤና ቢሮ ገለጸ።
ሐምሌ 07/2015 ዓ.ም (ምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሙዩኒኬሽን) በአማራ ክልል መደበኛ ባልኾኑ ሥራዎች የተሰማሩ ዜጎች የማኅበረሰብ ዓቀፍ የጤና መድኅን አገልግሎት ተጠቃሚ ከኾኑ 12 ዓመታት ተቆጥሯል።
የመንግሥት ሠራተኞችን የጤና መድኅን ተጠቃሚ ለማድረግም ፍኖተ ካርታ ከተዘጋጀ ዓመታትን አስቆጥሯል።
ፍኖተ ካርታው በመላ ሀገሪቱ ያሉ የመንግሥት ሠራተኞችን የደመወዝ ክፍያና የኑሮ ሁኔታን ግምት ውስጥ ያስገባ ጥናትን መሠረት ያደረገ መኾኑን ከዚህ በፊት የኢትዮጵያ ጤና መድኅን አገልግሎት መግለጹ ይታወሳል።
መደበኛ በኾኑ የሥራ መስኮች የተሰማሩ ዜጎች አገልግሎቱን በቀላሉ እንዲያገኙ ታስቦ የተዘጋጀው የማኅበራዊ ጤና መድኅን አገልግሎት በዓዋጅና በደንብ ቢጸድቅም በሥራ ላይ እየዋለ አይደለም።
በአማራ ክልል ጤና ቢሮ የሃብት አሰባሰብ፣ አሥተዳደር እና አጋርነት ዳይሬክተር አዲሱ አበባው ቢሮው የማኅበረሰቡን የጤና መድኅን ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ የመንግሥት ሠራተኛውን የጤና መድኅን ተጠቃሚ ለማድረግ ያከናወነውን ሥራ አብራርተዋል።
ዳይሬክተሩ እንዳሉት የመንግሥት ሠራተኛው ከደመወዙ በወር ሦስት በመቶ፣ ሦስት በመቶ ደግሞ በመንግሥት ተሸፍኖ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲኾን የሚያስችል ዓዋጅ እና ደንብ ወጥቷል።
አገልግሎቱን ለማስጀመርም በክልሉ የሚገኘው የመንግሥት ሠራተኛና የቤተሠብ ብዛት እንዲሁም የደመወዝ መጠን መረጃ ተሠብስቧል፤ ከመንግሥት ሠራተኛው የሚሰበሰበውና በመንግሥት የሚሸፈነው በጀት መጠንም ተሠርቶ ቀርቧል፤ አገልግሎቱን ለመሥጠት የሚያስፈልገው መታወቂያም ተዘጋጅቷል፤ ጤና ተቋማትም አገልግሎቱን መስጠት እንዲችሉ በባለሙያ የማደራጀት እና ግብዓት የማሟላት ሥራ ተሠርቷል። አገልግሎቱን ከመንግሥት ተቋማት ባለፈ በግል የጤና ተቋማት ለመስጠት የሚያስችል ዓዋጅና ደንብም ወጥቷል ብለዋል።
ከፌዴራል መንግሥት በጀት እንደተለቀቀ አገልግሎቱን ለመጀመር ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ነው ዳይሬክተሩ የገለጹት ያለው አሚኮ ነው።
East Gojjam Communication

በአባይ ባንክ አክሲዮን  ማህበርና  በምስራቅ ጎጃም ዞን  አስተዳደር መካከል  ለሰራተኞች  የብድር አገልግሎት  ለመስጠት  የሚያስችል  የጋራ መግባቢያ  ሰነድ ተፈረመ ።****ሐምሌ 5 /20...
14/07/2023

በአባይ ባንክ አክሲዮን ማህበርና በምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳደር መካከል ለሰራተኞች የብድር አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈረመ ።
****
ሐምሌ 5 /2015 ዓ.ም ( ምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ )የመግባቢያ ሰነዱ የዞኑ አስተዳደር ከባንኩ የሚጠበቅበትን ሁኔታዎች ሲያሟላ እና ሰራተኞች ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውል ገንዘብ ከአባይ ባንክ አክሲዮን ማህበር ብድር እንዲሰጣቸው ጠይቀው ሲፈቀድላቸው።
በብድርና በመያዣ ውል መሠረት ከዕዳ አከፋፈል መጠን በተገናዘበና ከአባይ ባንክ ጋር በተደረሰው የጋራ መግባቢያ ሰነድ መሠረት ከተበዳሪ ሰራተኞች ደመወዝ እየተቀነሰ ብድሩ ለባንኩ እንዲከፈል የሚያሳውቅ የውል ግዴታ ነው ።
በመግባቢያ ሰነዱ ላይ ፊርማቸውን በማስቀመጥ የተዋዋሉት የምስራቅ ገጃም ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ መንበሩ ዘውዴ እንደገለፁት በምስራቅ ገጃም ዞን አስተዳደር በዞን ደረጃ የሚገኙ መምሪያዎችና ተቋማት ለሰራተኞች ለቤት ግንባታ ፣ ለቤት መግዣ ፣ ለመኪና መግዣና ለግል የስራ እንቅስቃሴ አገልግሎት የሚውል የባንክ ብድር አገልግሎት ማዕቀፍ ነው ብለዋል ።ባንኩ የብድር ተጠቃሚዎች ጥያቄ እንደተጠናቀቀ ለተጠቃሚዎች ፈጣን አገልግሎት እንዲሰጥም አያይዘው አሳስበዋል ።
በውል ስምምነቱ ላይ የተገኙት የምስራቅ ጎጃም ዞን ገንዘብ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሞኝነት ንብረት እንደተናገሩት አባይ ባንክ አክሲዮን ማህበር የአካባቢውን ልማት ለማፋጠን እየሰራ ያለ ባንክ መሆኑን አብራርተው ለዞን መንግስት ሰራተኞች የብድር አገልገሎት በማመቻቸቱም ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። በብድሩ ቋሚ የሆኑ የመንግስት ሰራተኞች የባንኩን የብድር መስፈርት ሲያሟሉ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አቶ ሞኝነት ገልፀው መምረያዎች ተጠቃሚ ሰራተኞችን በመመልመል እና የአባይ ባንክ አክሲዮን ማህበርም ዕዳ የከፈሉና ያልከፈሉ ሰራተኞችን በየጊዜው ማሳወቅ አለባቸው ብለዋል ።
በአሁኑ ወቅት የመንግስት ሰራተኞች በግላቸው እንኳን ቤት ሊገዙ ይቅርና የቤት ኪራይ ለመክፈል እየተቸገሩ ነው ያሉት ደግሞ አቶ ሞላ ፀጋ የአባይ ባንክ አክሲዮን ማህበር ደብረ ማርቆስ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ሲሆኑ ባንኩ ያመቻቸው የብድር አገልግሎት ሰራተኞች በስራ ቦታቸው ተረጋግተው እንዲሰሩ እንደሚያስችላቸው ሀሳብ ካቀረቡ በኋላ ባንኩ ሶስት ዓይነት የብድር አገልግሎት በውል ስምምነቱ እንዳቀረበ አስረድተዋል ።
የመጀመሪያው እስከ 25 ዓመት ድረስ የሚቆይ የቤት መግዣ ብድር ሲሆን ሁለተኛው ከ10 -12 ዓመት የሚቆይ የተሽከርካሪ መግዣ እና ሦስተኛው ደግሞ እስከ 5 ዓመት የሚቆይ የቤት ቁሳቁስ ማሟያ (እስከ 500 ሺህ ብር ድረስ ) ብድር መመቻቸቱን አቶ ሞላ አስታውቀዋል ።
ባንኩ ያመቻቸው የብድር ወለድ 7 በመቶ መሆኑንና የምስራቅ ገጃም ዞን አስተዳደርም የተለያዩ የገንዘብ ተቀማጭ በባንኩ እንደሚሆንም ታውቋል ።
የዞኑ የመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ በአባይ ባንክ አማካኝነት እየተፈፀመ መሆኑንም በዚህ አጋጣሚ መግለፅ እንወዳለን ።
East Gojjam Communication

የደጀን ከተማ ም/ቤት ጉባኤ አካሄደ ፡፡ ***********************ደጀን ከተማ ኮሙዩኒኬሽን የደጀን ከተማ ም/ቤት 10ኛ ዓመት 4ኛ ዙር 4ኛ መደበኛ ጉባኤ አካሄደ ፡፡ በወረዳው ፖ...
11/07/2023

የደጀን ከተማ ም/ቤት ጉባኤ አካሄደ ፡፡
***********************
ደጀን ከተማ ኮሙዩኒኬሽን
የደጀን ከተማ ም/ቤት 10ኛ ዓመት 4ኛ ዙር 4ኛ መደበኛ ጉባኤ አካሄደ ፡፡
በወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት አባላት ላይ በደረሰው አደጋ ምክንያት ህይወታቸው ላጡ አመራሮች የህሊና ፀሎት በማድረግ ጉባኤው የተጀመረ ሲሆን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደጀን ከተማ ም/ቤት አፈ ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ውባየሁ ንጉሴ ናቸው ወ/ሮ ውባየሁ ንጉሴ ከሀላፊነት እንዲነሱ የተደረገበት አግባብ የም/ቤት አሰራርን ያልጠበቀ በመሆኑ ወደ ስራ እንዲመለሱ ተደርጓል፡፡
ጉባኤው በውሎው የ2015 ዓ/ም የሴክተሮች ዓመታዊ ሪፖርት ግምገማና ሹመት አፅድቋል ፡፡
የሴክተሮችን ዓመታዊ የስራ እንቅስቃሴ ሪፖርት ያቀረቡት የደጀን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አበጀ አላምረው ናቸው የቀረበውን ሪፖርት መሰረት በማድረግ በምክር ቤት አባላት የሴክተሮች እቅድ አፈፃፀም የተገመገመ ሲሆን ዝቅተኛ አፈፃፀም የታየባቸው ሴክተሮች በቀጣይ ዓመት የተሻለ ስራ እንዲሰሩ በምክር ቤቱ አባላት ሀሳብ ተሰጥቶባቸዋል ፡፡
በመጨረሻም የደጀን ከተማ ም/ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ውባየሁ ንጉሴ እንደተናገሩት ም/ቤቱን በቅንነትና በታማኝነት ሳገለግል ቆይቻለሁ ከዚህ በኋላ ግን በገዛ ፍቃዴ ራሴን ከሀላፊነት ያገለልኩ በመሆኑ በምትኩ እኔን ተክቶ ሊሰራ የሚችል ሰው እንዲተካበት ሲሉ ምክር ቤቱን በትህትና ጠይቀዋል ፡፡
በመሆኑም የምክር ቤቱ ሁለተኛ አጀንዳ የነበረው ሹመት ማፅደቅ ሲሆን
1. የደጀን ከተማ ም/ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ሰላማዊት ሹመት
2. የደጀን ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ብዙነህ ፈጠነ
3. የደጀን ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ስፖርት ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ እንዳይላሉ ምንውዩ በእጩነት የቀረቡ ሲሆን በምክር ቤቱ ሙሉ ድምጽ ፀድቋል ፡፡
በመጨረሻም ወ/ሮ ውባየሁ ንጉሴ የደጀን ከተማ ም/ቤት አፈ ጉባኤ ሁነው ለተመረጡት ወ/ሮ ሰላማዊት ሹመት የስልጣን ርክክብ አድርገው ጉባኤው ተጠናቋል ፡፡

   ==========ከሀምሌ 19- 23/2015 ዓ.ም ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከእስራኤል ሐገር ከሚመጡ ከፍተኛ የቀዶ ህክምና ባለሞያዎች ጋር በመተባበር በዘመናዊ መሳሪያ የታገዘ ከ...
07/07/2023


==========
ከሀምሌ 19- 23/2015 ዓ.ም ጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከእስራኤል ሐገር ከሚመጡ ከፍተኛ የቀዶ ህክምና ባለሞያዎች ጋር በመተባበር በዘመናዊ መሳሪያ የታገዘ ከፍተኛ የቀዶ ህክምና (Laparoscopic Surgery) አገልግሎት ይሰጣል::
አገልግሎት የሚሰጥባቸው ዘርፎች
------------------------------------------
1. የሐሞት ጠጠር ቀዶ ህክምና (Laparascopic cholecystectomy)
2. የጉረሮ ካንሰር እና ሌሎች የጉረሮ ህመሞች ቀዶ ህክምና (Esophageal disease and other related pathologies surgery)
3. የጨጓራ ካንሰር እና ሌሎች ተያያዥ የጤና ችግሮች ቀዶ ህክምና (Gastric cancer and other gastric pathologies surgery)
4. የቆሽት፣ የሐሞት ቱቦ እና የጣፊያ ቀዶ ህክምና (Hepatopancreaticobiliary surgery) እና
5. የአንጀት ካንሰር እና ተያያዥ የጤና ችግሮች ቀዶ ህክምና (Colorectal and other related diseases surgery) ናቸው::
ስለሆነም ችግሩ ያለባችሁ ህሙማን ወደ ሆስፒታሉ በመምጣት የአግልግሎቱ ተጠቃሚ ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እንሳተላልፋለን::
የጋራ ጥረት ለማኅበረሰብ ጤንነት!
መረጃው የተገኘው ከጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
East Gojjam Communication

የ2016 በጀት ዓመት አጠቃላይ በጀት 801 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ኾኖ በምክር ቤቱ ጸደቀ፡፡ ******ሰኔ 29/2015 ዓ.ም (ምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሙዩኒኬሽን) 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር...
07/07/2023

የ2016 በጀት ዓመት አጠቃላይ በጀት 801 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ኾኖ በምክር ቤቱ ጸደቀ፡፡
******
ሰኔ 29/2015 ዓ.ም (ምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሙዩኒኬሽን) 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 28ኛ መደበኛ ጉባዔ የ2016 የፌዴራል መንግሥት በጀት ዓዋጅ ቁጥር 1297/2015 ኾኖ ጸድቋል፡፡ የ2016 በጀት ዓመት በጀት 801 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ኾኖ ጸድቋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በተገኙበት የ2015 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2016 በጀት ትኩረት ላይ ያደረገው ጉባዔው የ2016 በጀት ዓመትን ዓመታዊ በጀት አጽድቋል፡፡
ካለፈው በጀት ዓመት አጠቃላይ በጀት ጋር ሲነጻጸር 1 ነጥብ 9 በመቶ ብልጫ ያለውን የ2016 በጀት የምክር ቤት አባላቱ ተወያይተው በአንድ ተቃውሞ በአብላጫ ድምጽ ጸድቋል ሲል የዘገበው አሚኮ ነው፡፡
East Gojjam Communication

ከደጀን ወረዳ አስተዳደር የተሰጠ የሃዘን መግለጫበትናንትናው እለት ማለትም ሰኔ 26/2ዐ15 ዓ/ም ከቀኑ 8፡ዐዐ ሰዓት አካባቢ በደጀን ወረዳ ኩራር ቀበሌ ደምበዛ ጎጥ የሚሰጠውን የ8ኛ ክልላዊ...
04/07/2023

ከደጀን ወረዳ አስተዳደር የተሰጠ የሃዘን መግለጫ
በትናንትናው እለት ማለትም ሰኔ 26/2ዐ15 ዓ/ም ከቀኑ 8፡ዐዐ ሰዓት አካባቢ በደጀን ወረዳ ኩራር ቀበሌ ደምበዛ ጎጥ የሚሰጠውን የ8ኛ ክልላዊ ፈተና የጸጥታ ስራ ለመከታተል በወጡበት የደጀን ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ዘውዱ ታደለ እና የወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት የወንጀል መከላከል ክፍል ኃላፊ የሆኑት ም/ኢንስፔክተር ወርቁ ሽመልስ ላይ ለጊዜው ማንነቱ ባልታወቀ አካል በደረሰባቸው ጥቃት የህይወት መሥዋዕትነት ከፍለዋል፡፡ አብሯቸው መኪና በማሽከርከር ላይ የነበረ አንድ የፖሊስ አባል ቆስሎ ህክምና እየተደርገለት ይገኛል፡፡
የደጀን ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት ለህዝብ ሰላምና ደህንነትን ለማስጠበቅ ብለው ለስራ በወጡበት ማንነቱ ባልታወቀ አካል መስዋዕት በሆኑ የህዝብ ልጆች አስተዳደር ምክርቤቱ ጥልቅ ሃዘን የተሰማው መሆኑን ይገልፃል፡፡
የደጀን ወረዳ አስተዳደር የእነዚህን ጀግና ህዝብ ልጆችን ህይወት የቀጠፉ ወንጀለኞችን ከጸጥታ ሃይላችንና ከመላ ህዝባችን ጋር በመሆን በአጭር ጊዜ ለህግ ለማቅረብ ጠንክሮ የሚሰራ መሆኑን እየገለጸ የህዝብ ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ሲሉ መስዋዕት የሆኑ የፀጥታ አካላት ቤተሰቦችን አስተዳደሩ እንደራሱ አድርጐ የሚንከባከብና የሚደግፍ መሆኑን ይገልፃል፡፡
የደጀን ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት
Dejen Woreda Government Communication Affairs office

በምስራቅ ጎጃም ዞን በደጀን ከተማ ትምህርት ቤቶች የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በመሰጠት ላይ ይገኛል ፡፡ *******************************************በምስራቅ ጎጃ...
03/07/2023

በምስራቅ ጎጃም ዞን በደጀን ከተማ ትምህርት ቤቶች የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በመሰጠት ላይ ይገኛል ፡፡
*******************************************
በምስራቅ ጎጃም ዞን በደጀን ከተማ ትምህርት ቤቶች የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በመሰጠት ላይ ይገኛል ፡፡ ደጀን 01 (ጁንየር ) ት/ቤት ወንድ 68 ሴት 74 ድምር 142 ተማሪዎችን እንዲሁም አንድ ልዩ ፍላጎት ተማሪ ደጀን 02 ት/ቤት ወንድ 70 ሴ 81 በድምሩ 151 በአጠቃላይ በሁለቱ ት/ቤቶች 293 ተማሪዎች ለፈተና መቅረባቸውን እና የጠዋቱ የፈተና መርሀ ግብር በሰላም መጠናቀቁን የትምህርት ቤቶች ርዕሳነ መምህራን ተናግረዋል ፡፡
ደጀን ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ሰኔ 26/2015 ዓ/ም

በደጀን ከተማ አስተዳደር ለአመራርና ለብልፅግና አባላቶች ስልጠና መስጠት ተጀመረ ። **************************ደጀን ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ሰኔ 26/2015 ዓ/ም "መፍጠንና መፍጠ...
03/07/2023

በደጀን ከተማ አስተዳደር ለአመራርና ለብልፅግና አባላቶች ስልጠና መስጠት ተጀመረ ።
**************************
ደጀን ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ሰኔ 26/2015 ዓ/ም
"መፍጠንና መፍጠር የወል እውነቶችን የማፅናት ቀጣይ የትግል ምዕራፍ " በሚል መሪ ቃል በደጀን ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት አዘጋጅነት የብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ባስቀመጣቸው አቅጣጫዎች እና ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታዎች ፈተናዎችን እንዴት እንሻገራለን በሚሉና መሰል ሀሳቦች ላይ ስልጠና መስጠት ተጀምሯል ፡፡
በስልጠናው የከተማና የቀበሌ አመራሮች ፣ በከተማ አስተዳደሩ የሚገኙ የመንግስት ሰራተኛ የብልፅግና ፓርቲ አባላት እና በከተማ አስተዳደሩ የሚገኙ የመሰረታዊ ፓርቲ አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል ፡፡
ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የደጀን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አበጀ አላምረው ሲሆኑ እንደ ሀገርም ሆነ እንደ ክልል በየግዜው እያጋጠሙን ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ከመቸውም ግዜ በላይ በህብረትና በአብሮነት ከችግር መውጫ መንገዶችን በመፍጠር ከተጋረጡብን ችግሮች ለመውጣት በመፍጠን በጋራ ህዝቡና አመራሩ እጅና ጓንት በመሆን የምንጓዝበት ወቅት ሊሆን ይገባል ያሉት ከንቲባው ስልጠናውን ለመውሰድ የተገኛችሁ አካላት ትኩረት በመስጠት ሀገሪቱ ብሎም ክልላችን ያለበትን አንፃራ ሁኔታ በመረዳት የክልሉን ሰላም ለማስጠበቅና የመልማት ጥያቄን ለመመለስ ለአመራሩ የሚተው ተግባር ባለመሆኑ የሁሉንም ርብርብ የሚጠይቅ ተግባር በመሆኑ ስልጠናውን በትኩረት በመከታተል ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በመግባት ክልልሉን ከጋጠመው ችግር ማውጣት ስለሚገባ ስልጠናውን በትኩረት እንድትከታተሉ በማለት ፕሮግራሙን በይፋ አስጀምረዋል ፡፡
የስልጠና ሰነድን የደጀን ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ግርማ ጌታነህ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ ፡፡ ስልጠናውም የሁለት ቀናት የጊዜ ቅይታ እንደሚኖረው ተገልጿል ፡፡

Address

Dejen Town
Dejen

Telephone

+251587760079

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dejen Ketema Communication Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Share on Facebook Share on Twitter Share on LinkedIn
Share on Pinterest Share on Reddit Share via Email
Share on WhatsApp Share on Instagram Share on Telegram